Kirkos curriculm
Відкрити в Telegram
3 638
Підписники
-124 години
+77 днів
+2330 день
Архів дописів
3 638
Repost from Addis Abeba Education Bureau
+1
የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ዛሬ ከሰዓት የ2018 ዓ/ም የ8ኛ ክፍል ተፈታኞችን ውጤት ይፋ ያደረገ ሲሆን ማለፊያ ውጤቱ 50% ለአካል ጉዳተኞች 45 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን መወሰኑን ገልጿል።
የትምህርት ቢሮው መረጃ በሚያሳየው መሰረት ለፈተና ከተቀመጡ 85 ሺሕ 737 ተማሪዎች መካከል 82 ሺሕ 193 (95.85%) የሚሆኑት 50 እና ከዚያ በላይ ማለፊያ ውጤት አምጥተዋል።
ከተፈታኞቹ መካከል 3 ሺሕ 544 የሚሆኑት ማለፊያ ውጤት አላመጡም።
የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት 96.25 ሲሆን ይህን ያመጣውን አንድ ተማሪ ነው።
60 ተፈታኞች 93% ውጤት አምጥተዋል።
1 ሺሕ 316 ተፈታኞች 90% እና ከዚያ በላይ ውጤት ማምጣታቸው ታውቋል።
የዘንድሮው ውጤት ከአምናው ጋር ሲነጻጸር ምን ይመስላል ?
በ2017 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱት 70 ሺሕ 525 ተፈታኞች፣ 50 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጡት 62 ሺሕ 639 (88.8%) ሲሆኑ፣ 7 ሺሕ 886 ተፈታኞች ማለፊያ ውጤት አላመጡም ነበር።
የዘንድሮ የተፈታኞች ብዛት ከአምናው በ15 ሺሕ 212 የጨመረ ሲሆን፣ ማለፊያ ውጤት ያላመጡ ተፈታኞች ደግሞ፣ ከአምናው በ4 ሺሕ 342 ቀንሷል።
ዘንድሮ የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት 96.25 በአንድ ተማሪ ብቻ ሲሆን፣ በ2017 ዓ/ም ግን 113 ተማሪዎች 94% ውጤት አምጥተው ነበር።
በአንጻሩ፣ ዘንድሮ 90% እና በላይ ያመጡት ተፈታኞች 1 ሺሕ 316 ተማሪዎች ሲሆኑ፣ በ2017 ደግሞ ይህን ውጤት ያመጡት 712 ተማሪዎች ናቸው። በዚህም የዘንድሮው የ604 ብልጫ አለው።
በተያያዘ መረጃ፣ ዘንድሮ ተማሪዎቻቸውን ካስፈተኑ 669 ትምህርት ቤቶች ውስጥ 441ዱ 100% ተማሪዎቻቸውን አሳልፈዋል። እንዲሁም በከተማ ደረጃ ከ93% በላይ ከፍተኛ ውጤት ያመጡት 60 ተማሪዎች ናቸው።
3 638
+1
#Grade12
#NationalExam
የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበት የጊዜ ሰሌዳ ይፋ ሆነ።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል።
በዚሁ መሠረት በኦንላይን (Computer-based Testing (CBT) የሚፈተኑ ተፈታኞች በስድስት ዙር የሚፈተኑ ሲሆን ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ይፈተናሉ። ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የሚፈተኑ ይሆናል።
ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተፈታኞች የተፈጥሮ ሳይንስ በሶስተኛ ዙር ላይ የሚፈተኑ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ በአራተኛ ዙር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚፈተኑ ይሆናል።
(ዝርዝሩን ከላይ ይመልከቱ)
@tikvahethiopia
3 638
ሰላም እንዴት ናቹ የመኪና ስምሪት ይህ ነው ከዚህ የሽፌሮቹ ስልክ በሠውስድ አድራሻቹ በመለዋወጥ ሰኞ ከሊቱ 11:00 ሰአት ፖሊስ ጣብያ መድረስ ይጠበቅባችዋል።የመኪና አስተባባሪ ሁናቹ በአግባቡ ሰው ወደ አማካይ ቦታ እንዲወጣ በአግባቡ ማስተባበር ይኖርባችዋል።
3 638
ዋንኛ የትውልድ ግንባታ ማዕከል በሆኑት ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በስነ ምግባር ታንጸው እንዲያድጉና ተሰጥኦቸውን ለይተው በልምምድ እንዲያሳድጉ የዚህ አይነቱ ውድድር ትልቅ እድል እንዳለውም ነው ከመድረኩ የተነሳው።
በተማሪዎቹ መካከል ከፍተኛ የሆነ ውድድር ተካሄዶ የምስራቅ ጎህ 2ኛ ደረጃ ወክለው በመጡ ተማሪዎች አሸናፊነት ተጠናቋል።
የውድድሩ አዘጋጆች የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፍትህ ጽ/ቤትና ትምህርት ጽ/ቤት መሆናቸው በውድድሩ ፍጻሜ መድረክ ላይ ገልጿል
3 638
+6
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በትምህርት ቤቶች መካከል ሲካሄድ የነበረው ምስለ ችሎት የፍጻሜ ውድድር በምስራቅ ጎህ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አሸናፊነት ፍጻሜውን አግኝቷል፡፡
*****
ግንቦት 28/2018 ዓ.ም
በክፍለ ከተማው በሚገኙ አራት 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል ሲካሄድ የነበረው የተማሪዎች የምስለ ህግ ውድድር ለፍጻሜ በደረሱት አብዮት ቅርስና ምስራቅ ጎህ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ከፍተኛ የሆነ ፉክክር ተደርጎ በምስራቅ ጎህ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አሸናፊነት ፍጻሜውን አግኝቷል፡፡
ተማሪዎች ህግ አዋቂ እንዲሆኑና ለሚገጥማቸው ክርክር በምክንያት መሞገት እንዲችሉ ብሎም ሃሳብን በሃሳብ የማሸነፍ ልምምድ እንዲያዳብሩ አላማ ያደረገው ይህ ውድድር በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዳዮች ላይ በተለያየ ዙር ምስለ ችሎት ተሰይሞ ክርክር እንዲያደርጉ መደረጉንም ከአዘጋጆቹ ለመረዳት ተችሏል፡፡
በዚህም በቤት ውስጥ የህጻናት የጉልበት ብዝበዛ የልዩ ድጋፍ /Afermative action/ እና የእኩልነት መብትን እንዲሁም በማህበራዊ ሚድያ አጠቃቀም ዙሪያ ላይ ህጉ ምን ይላል በሚለው ጉዳይ ዙሪያ በማጠንጠን ተማሪዎቹ ሰፊ የህግ እውቀት እንዲያገኙ የሚያስችል ክርክር እንዲያደርጉ መደረጉንም ከመድረኩ ተገልጿል፡፡
በተነሱ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሲከራከሩም በትምህርት ቤት እንዲሁም በመኖሪያ አካባቢያቸው ለሚገጥሟቸው ችግሮች ከህግ አንጻር እንዴት መፍታት እንዳለባቸው ከመረዳታቸው ባሻገር ለወላጅ ቤተሰቦቻቸውም እገዛ የሚያደርጉበት እውቀት ባለቤት እንዲሆኑም መንገድ የከፈተ ዝግጅት እንደነበረ ተነግሯል፡፡
ሌላኛው የምስለ ችሎት ውድድሩ ዓላማ ከተማሪዎቹ መካከል የተሻለ እውቀትና ፍላጎት ያላቸው አቃቢ ህጎችና ዳኞች እንዲሁም የህግ እውቀት ያለው ትውልድ መፍጠርን ታሳቢ ያደረገ ነውም ተብሏል።
3 638
+2
ቀን 20/09/2018 ዓም
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የ2018 ዓም የ6ኛ: 8ኛ እና 12ኛ ዓም የፈተና ቅድመ ዝግጅት አስመልክቶ ኦረንቴሽን ተሰጠ።
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
