fa
Feedback
Kirkos curriculm

Kirkos curriculm

رفتن به کانال در Telegram

ለትምህርት ጥራት እንተጋለን We strive for the quality of education

نمایش بیشتر
3 631
مشترکین
+324 ساعت
+127 روز
+1730 روز
آرشیو پست ها
በደብዳቤው መሠረት ይፈጸም።
+1
በደብዳቤው መሠረት ይፈጸም።

ዋንኛ የትውልድ ግንባታ ማዕከል በሆኑት ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በስነ ምግባር ታንጸው እንዲያድጉና ተሰጥኦቸውን ለይተው በልምምድ እንዲያሳድጉ የዚህ አይነቱ ውድድር ትልቅ እድል እንዳለውም ነው ከመድረኩ የተነሳው። በተማሪዎቹ መካከል ከፍተኛ የሆነ ውድድር ተካሄዶ የምስራቅ ጎህ 2ኛ ደረጃ ወክለው በመጡ ተማሪዎች አሸናፊነት ተጠናቋል። የውድድሩ አዘጋጆች የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፍትህ ጽ/ቤትና ትምህርት ጽ/ቤት መሆናቸው በውድድሩ ፍጻሜ መድረክ ላይ ገልጿል

በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በትምህርት ቤቶች መካከል ሲካሄድ የነበረው ምስለ ችሎት የፍጻሜ ውድድር በምስራቅ ጎህ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አሸናፊነት ፍጻሜውን አግኝቷል፡፡ ***** ግንቦት 28/2018 ዓ
+6
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በትምህርት ቤቶች መካከል ሲካሄድ የነበረው ምስለ ችሎት የፍጻሜ ውድድር በምስራቅ ጎህ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አሸናፊነት ፍጻሜውን አግኝቷል፡፡ ***** ግንቦት 28/2018 ዓ.ም በክፍለ ከተማው በሚገኙ አራት 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል ሲካሄድ የነበረው የተማሪዎች የምስለ ህግ ውድድር ለፍጻሜ በደረሱት አብዮት ቅርስና ምስራቅ ጎህ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ከፍተኛ የሆነ ፉክክር ተደርጎ በምስራቅ ጎህ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አሸናፊነት ፍጻሜውን አግኝቷል፡፡ ተማሪዎች ህግ አዋቂ እንዲሆኑና ለሚገጥማቸው ክርክር በምክንያት መሞገት እንዲችሉ ብሎም ሃሳብን በሃሳብ የማሸነፍ ልምምድ እንዲያዳብሩ አላማ ያደረገው ይህ ውድድር በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዳዮች ላይ በተለያየ ዙር ምስለ ችሎት ተሰይሞ ክርክር እንዲያደርጉ መደረጉንም ከአዘጋጆቹ ለመረዳት ተችሏል፡፡ በዚህም በቤት ውስጥ የህጻናት የጉልበት ብዝበዛ የልዩ ድጋፍ /Afermative action/ እና የእኩልነት መብትን እንዲሁም በማህበራዊ ሚድያ አጠቃቀም ዙሪያ ላይ ህጉ ምን ይላል በሚለው ጉዳይ ዙሪያ በማጠንጠን ተማሪዎቹ ሰፊ የህግ እውቀት እንዲያገኙ የሚያስችል ክርክር እንዲያደርጉ መደረጉንም ከመድረኩ ተገልጿል፡፡ በተነሱ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሲከራከሩም በትምህርት ቤት እንዲሁም በመኖሪያ አካባቢያቸው ለሚገጥሟቸው ችግሮች ከህግ አንጻር እንዴት መፍታት እንዳለባቸው ከመረዳታቸው ባሻገር ለወላጅ ቤተሰቦቻቸውም እገዛ የሚያደርጉበት እውቀት ባለቤት እንዲሆኑም መንገድ የከፈተ ዝግጅት እንደነበረ ተነግሯል፡፡ ሌላኛው የምስለ ችሎት ውድድሩ ዓላማ ከተማሪዎቹ መካከል የተሻለ እውቀትና ፍላጎት ያላቸው አቃቢ ህጎችና ዳኞች እንዲሁም የህግ እውቀት ያለው ትውልድ መፍጠርን ታሳቢ ያደረገ ነውም ተብሏል።

ቀን 20/09/2018 ዓም የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የ2018 ዓም የ6ኛ: 8ኛ እና 12ኛ ዓም የፈተና ቅድመ ዝግጅት አስመልክቶ ኦረንቴሽን ተሰጠ።
+2
ቀን 20/09/2018 ዓም የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የ2018 ዓም የ6ኛ: 8ኛ እና 12ኛ ዓም የፈተና ቅድመ ዝግጅት አስመልክቶ ኦረንቴሽን ተሰጠ።

photo content

ቀን 18/09/2017 ዓም የተከለሰ የትምህርት ካላንደር
+1
ቀን 18/09/2017 ዓም የተከለሰ የትምህርት ካላንደር

photo content

+5
መጠመሪያ ፖርሽን.xlsx0.15 KB

አስቸኳይ መረጃ.
አስቸኳይ መረጃ.

መረጃው እጅግ ቢዘገይ ግንቦት 21 ቀን 2018ዓ.ም መቅረብ አለበት

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡ (ግንቦት 13/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2
+2
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡ (ግንቦት 13/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና እና የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡ በዚህ መሰረትም ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ሰኔ 8 ፣ 9 እና 10/2018 ዓ.ም እንዲሁም የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚሰጥ ይሆናል፡፡ ከሰኔ 8 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሚሰጠው በዚህ ከተማ አቀፍ ፈተና በ6ኛ ከፍል 84,882 ተማሪዎች 199 የመፈተኛ ጣቢያዎች እንዲሁም በ8ኛ ከፍል 86,808 ተማሪዎች 201 የመፈተኛ ጣቢያዎች ፈተናዉን ለመውሰድ ተመዝግበዋል፡፡

ፈተናው በ6 ዙር እንደሚሰጥና በማህበራዊ ሳይንስ በሶስት ዙር በተመሳሳይ በተፈጥሮ ሳይንስ ደግሞ በሶስት ዙር በመሆኑ አንድ ኮምፒዩተር ስድስት ተማሪን ያስተናግዳል ነው ያሉት።   ተማሪዎች የፈተና ስርዓቱን እንዲለማመዱና ትምህርት ቤቶች እና ወላጆች ለተፈታኝ ተማሪዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉም አስገንዝበዋል።   ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በ667 የፈተና ማዕከላት እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጻል፡፡ (ግንቦት 11/2018 ዓ.ም)
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በ667 የፈተና ማዕከላት እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጻል፡፡   (ግንቦት 11/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና በ667 የፈተና ማዕከላት ላይ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አሳውቋል፡፡   የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) እንደገለጹት  የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናን በ97 ዩኒቨርሲቲዎች እና በ570 የክልልና የከተማ አስተዳደሮች ማዕከላት ላይ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።   ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ፈተና መደበኛ ተማሪዎችን ጨምሮ በሁሉም ፕሮግራሞች በተፈጥሮ ሳይንስ 306 ሺህ 964 እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ 257 ሺህ 255 በድምሩ 564 ሺህ 219 ተማሪዎች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡     ፈተናውን በሙሉ አቅም በበይነ መረብ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ፤ በተለያዩ ምክንያቶች ቁጥራቸው አነስተኛ የሆኑ በወረቀት የሚፈተኑ ተማሪዎች እንደሚኖሩም ጠቁመዋል።   በየክልሎች ፣ በከተማ አስተዳደሮች እና የፈተና ማዕከላት ያለው አቅም የተለያየ ቢሆንም በርካታ ኮምፒዩተሮች ለፈተና ዝግጁ እየተደረጉ እንደሚገኙ አመልክተዋል።     ከባለፈው አርብ ጀምሮ ለተፈታኞች የበይነ መረብ የሙከራ ፈተና መሰጠት መጀመሩን አንስተዋል።

የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች የሚለማመዱባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆኑ። (ግንቦት 6/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን
የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች የሚለማመዱባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆኑ። (ግንቦት 6/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች የሚለማመዱባቸው አድራሻዎች ይፋ አድርጋል። የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን በበይነ መረብ (CBT) ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን ሁሉም ተፈታኞች በተደለደሉበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር ትይዩ ባለው ማስፈንጠሪያ በመጠቀም USER Name በሚለው ላይ የፈተና አዳራሽ መግቢያ ካርድ ላይ ያለውን አድሚሽን ቁጥር በማስገባት እና Pass word በሚለው ላይ 1234 በማስገባት በዴስክቶፕ ኮምፕዩተር፣ በላፕቶፕ ኮምፕዩተር፣ በታብሌት፣ በስልክና በመሰል የኤልክትሮኒክስ መሣሪያዎች ማንኛውንም ዓይነት ኢንተርኔት አማራጭ በመጠቀም ከግንቦት 07/2018 ዓ/ም ከጥዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከፈተናው ድረስ መለማመመድ ይችላሉ ተብላል። ተፈታኞች አዲሚሽን ካርድ ከየትምህርት ቤቶቻቸው ማግኘት የሚችሉ ሲሆን በየጊዜው የተለያዩ የሚለማመዱባቸውን ፈተናዎች በተከታታይ የሚሰጥ መሆኑን ፈተናዎች አገልግሎት ገልፃል። ስለሆነም መምህራን ፣ የትምህርት ቤት አመራርና ወላጆች ተፈታኞቹ እንዲለማመዱ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንዲያደርጉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ጥሪ አቅርባል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

ራስን ማሻሻል፤ የሕይወት ትልቁ ኢንቨስትመንት ነው ================== በሕይወት ውስጥ ትልቁ ስኬት ከሌሎች ሰዎች መበለጥ ሳይሆን፣ ትናንት ከነበርንበት ማንነት ዛሬ የተሻለ ሆኖ መገኘት ነው
ራስን ማሻሻል፤ የሕይወት ትልቁ ኢንቨስትመንት ነው ================== በሕይወት ውስጥ ትልቁ ስኬት ከሌሎች ሰዎች መበለጥ ሳይሆን፣ ትናንት ከነበርንበት ማንነት ዛሬ የተሻለ ሆኖ መገኘት ነው። ራስን ማሻሻል የአንድ ቀን ሥራ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ጉዞ ነው። ራስህን/ሽን ለማሻሻል የሚረዱ ጥቅት እርምጃዎች፦ 1️⃣ ቀጣይነት ያለው ትምህርት (Continuous Learning)፦ እውቀት ማለቂያ የለውም። በየቀኑ አዲስ ነገር ለማወቅ ጥረት አድርግ/ጊ። መጽሐፍ ማንበብ፣ አዳዲስ ክህሎቶችን መልመድና ከሰዎች ተሞክሮ መማር አእምሮህን/ሽን ያሰፋዋል። 2️⃣ ምቹ ቀጠናን መልቀቅ (Leave the Comfort Zone)፦ እድገት የሚመጣው ፈተና ባለበት ቦታ ነው። አዳዲስ ነገሮችን ከመሞከር አትፍራ/ሪ። ስህተት ብትሰራ/ሪ እንኳን ያ ስህተት ለበለጠ እድገትህ/ሽ መሰላል ይሆንሃል/ሻል። 3️⃣ ጊዜንና ልምድን መመርመር፦ በየቀኑ መጨረሻ ላይ "ዛሬ ምን ተማርኩ? ምንስ አሻሻልኩ?" ብለህ/ሽ ራስህን/ሽን ጠይቅ/ቂ። መጥፎ ልምዶችን በመልካም ልምዶች መተካት የማንነት ለውጥ መጀመሪያ ነው። 4️⃣ አዎንታዊ አከባቢን መፍጠር፦ የሚያሳንሱህን ሳይሆን የሚያሳድጉህን፣ የሚተቹህን ሳይሆን የሚያበረታቱህን ሰዎች ቅረብ/ቢ። የምትውልበት አከባቢና የምታያቸው ነገሮች አንተን/አንቺን የመቅረጽ ትልቅ ኃይል አላቸው። ማጠቃለያ፦ ራስህን/ሽን ለማሻሻል የምታደርገው ጥረት ውጤቱ ወዲያው ባይታይም፣ በሂደት ግን ማንም ሊነጥቅህ/ሽ የማይችለው ትልቅ ሀብት ይሆንሃል/ሻል። ዛሬ ለራስህ/ሽ የምትሰጠው ዋጋ የነገ ማንነትህን/ሽን ይወስነዋል። "ትልቁ ስራ ራስን መስራት ነው!"

photo content
+4

photo content

photo content

photo content