Kirkos curriculm
前往频道在 Telegram
3 806
订阅者
-124 小时
+47 天
+3630 天
帖子存档
3 806
ለሁሉም የምንግስት እና የግል 1ኛ ደረጃ ትቤቶች የ2019 ዓ.ም የሬድዮ ትምህርት ፕሮግራም ስለሆነ በጥብቅ ዲሲፕሊን ተግባራዊ ይደረግ፡፡
3 806
ሰላም ለመንግስት እና የግል 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች
ከ2019 ዓ.ም ጀምሮ በ2ኛ ዙር እንዲተገበሩ የተለዩ 11 የስራና ተግባር ትምህርት የሙያ ዓይነቶች ስለሆኑ ለተማሪዎች ግንዛቤ ተፈጥሮ እንዲመርጡ ይደረግ፡፡
3 806
ሀገር አቀፍ የሒሳብ ትምህርትና ውድድር መርሀ ግብር
🤝 የAI PLUS ONE MINUTE እና የትምህርት ቤታችሁ አጋርነት ግብዣ
ለ፡ የትምህርት ቤት ዳይሬክተር / አመራር
ክቡራን የትምህርት ቤት አመራሮች፣
የተማሪዎችን የሒሳብ እውቀት፣ አስተሳሰብ፣ ችግር መፍታትና የውድድር ብቃት ለማሳደግ የተዘጋጀው AI PLUS ONE MINUTE መርሀ ግብር ከትምህርት ቤታችሁ ጋር በአጋርነት ለመስራት በክብር ይጋብዛል።
📚 LEARN → PRACTICE → MEASURE → COMPETE → EXCEL
👩🎓 3ኛ–8ኛ ክፍል | TEXTBOOK-BASED
🔹 ሳምንታዊ ትምህርት — የሳምንቱ ትምህርት በደረጃው ተዘጋጅቶ በቪዲዮ በየተማሪው Telegram ይላካል።
🔹 የቅዳሜ ልምምድ — በTelegram ይከናወናል።
🔹 ወርሃዊ ፈተና — በTelegram ይከናወናል።
🔹 🤖 AI የውጤት ግምገማና ክትትል
🏆 የውድድር መንገድ
SCHOOL → CITY ROUND 1 → CITY ROUND 2 → NATIONAL
በትምህርት ቤት ደረጃ የሚያልፉ ተማሪዎች በከተማ ደረጃ ሁለት ዙር ይወዳደራሉ፤ የተሻሉ ተማሪዎችም ወደ ሀገር አቀፍ ውድድር ያልፋሉ።
💰 የሳምንታዊ ክፍያ 20 ብር/ተማሪ
➡️ የከተማ ውድድር፡ ክፍያው በወቅቱ ይወሰናል
➡️ ሀገር አቀፍ ውድድር፡ ነፃ
👤 የት/ቤት አስተባባሪ፡ ትምህርት ቤቱ አንድ አስተባባሪ ይመድባል፤ ለፕሮግራሙ አፈጻጸም በት/ቤት ደረጃ የሚያስፈልጉ የሰው ኃይል ክፍያዎች AI PLUS ONE MINUTE PLC በሕጋዊ አሠራር ይሸፍናል።
🤝 አጋርነት ለመጀመር፦
ትምህርት ቤታችሁ በመርሀ ግብሩ ለመሳተፍ ፈቃደኛ ከሆነ ያሳውቁን።
ከዚያ በኋላ የአጋርነቱን ዝርዝር ኃላፊነቶች፣ የአፈጻጸም ሂደት፣ የክፍያ አሰራርና ሌሎች ውሎችን የሚያካትት MOU ይቀርብላችኋል።
🌍 ETHIOPIA TO THE WORLD
ከበደ አጥናፉ
ዋና ስራ አስኪያጅ | AI PLUS ONE MINUTE
“ከአስተሳሰብ ወደ ማሸነፍ”
3 806
ሀገር አቀፍ የአባከስ ስልጠና እና ውድድር መርሀ ግብር
ለ፡ የትምህርት ቤት ዳይሬክተር / አመራር
🤝 ጉዳዩ፡ የAI PLUS ONE MINUTE እና የትምህርት ቤታችሁ አጋርነት ግብዣ
AI PLUS ONE MINUTE ተማሪዎች አባከስን በነፃ እንዲያገኙ በማድረግ፣ በየሳምንቱ ሳይቆራረጥ ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ የአባከስ ስልጠና በእጅግ ዝቅተኛ ዋጋ ለመስጠት እና ተማሪዎችን ከSCHOOL → CITY → NATIONAL ደረጃ ለማድረስ የተዘጋጀ ሀገር አቀፍ መርሀ ግብር ነው።
👧👦 የተሳታፊ ደረጃ፡ 1ኛ–4ኛ ክፍል
📚 የመርሀ ግብሩ ሂደት
TRAIN → PRACTICE → SPEED → EXAM → COMPETE → EXCEL
🔹 🧮 አባከስ — በነፃ
🔹 🎥 በየሳምንቱ የተቀረፀ የስልጠና ቪዲዮ በTelegram ይላካል።
🔹 📖 የመለማመጃ ስራዎች እና ጥያቄዎች በTelegram ይቀርባሉ።
🔹 ⏱️ ተማሪዎች ፍጥነት፣ ትክክለኛነትና ትኩረት እንዲያዳብሩ በቀጣይነት ይለማመዳሉ።
🔹 🧪 የወርሃዊ ፈተና በTelegram በ ONLINE ይከናወናል።
🔹 🤖 ውጤቶች በAI ይገመገማሉ፣ የተማሪዎችም እድገት ይከታተላል።
📖 የመለማመጃ መጽሐፍ
ለተማሪዎች የሚቀርበው የተደራጀና ከፍተኛ ጥራት ያለው የመለማመጃ መጽሐፍ ዝርዝር አተገባበርና የክፍያ ሁኔታ በMOU ውስጥ ይካተታል።
🏆 የውድድር መንገድ
SCHOOL → CITY → NATIONAL
ተማሪዎች በውጤታቸው መሠረት ከትምህርት ቤት ደረጃ ወደ ከተማ እና ከዚያም ወደ ሀገር አቀፍ ውድድር ይሸጋገራሉ።
💰 ዋና ክፍያ፡ 20 ብር / ተማሪ / ሳምንት
ለ 3ተኛ እና 4ተኛ ክፍሎች ልዩ ጥቅም ተዘጋጅቶአል በMOU ላይ ተካቷል።
🏫 የትምህርት ቤቱ ሚና
ትምህርት ቤቱ አንድ አስተባባሪ ይመድባል። በመርሀ ግብሩ አፈጻጸም የሚያስፈልጉ የሰው ኃይል ክፍያዎች AI PLUS ONE MINUTE PLC በሕጋዊ አሰራር ይሸፍናል።
🤝 ትምህርት ቤታችሁ በመርሀ ግብሩ ለመሳተፍ ፈቃደኛ ከሆነ ያሳውቁን።
ከዚያም ዝርዝር የአተገባበር፣ የኃላፊነት፣ የክፍያ፣ የመጽሐፍ አቅርቦት እና ሌሎች የስምምነት ጉዳዮች በMOU ይወሰናሉ።
🌍 ETHIOPIA TO THE WORLD
ከበደ አጥናፉ
ዋና ስራ አስኪያጅ
AI PLUS ONE MINUTE
✨ “ከአስተሳሰብ ወደ ማሸነፍ”
3 806
ቀን 11/12/2018 ዓም
ለሁሉም 1ኛ እና 2ኛ ደረጀ የመንግስት እና የግል ት/ቤቶች
ከክልል በተለያዩ ምክንያት ወደ አዲስ አበባ መጥተው በ2019 ዓም ለመማር የመመመጡ ተማሪዎች በምዝገባ ወቅት የሚያጋጥማችሁ ችግር ካለ በየቀኑ ከላይ በያያዘው ቅጽ መሠረት ሞልታችሁ እንድትልኩልን እናሳውቃለን።
3 806
📚 ትምህርት የነገ መሣሪያ
መጽሐፍ በእጄ፣ ሕልም በልቤ፣
እውቀት ነው ብርሃን በመንገዴ።
ዛሬ ብታገል ለትምህርት ብዬ፣
ነገን እገነባለሁ በእጄ ይዤ።
መሣሪያ ሳይሆን ብዕር እንድይዝ፣
በእውቀት ኃይል ዓለምን እንድለውጥ።
ትምህርት ይሁን ጋሻዬ ለነገ፣
ተስፋ ይሁን ብርሃኔ በሕይወቴ።
“የእውቀት ኃይል ከማንኛውም መሣሪያ ይበልጣል።”
3 806
ቀን 05/12/2018 ዓም
በጣም አስቸኳይ
ለሁሉም 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶቾ በሁለተኛ ዙር ከትምህርት ሚ/ር በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት 11 የሙያ መስኮች የ11ኛ ክፍል ተማሪዎች እንዲመርጡ ግንዛቤ ፈጥራችሁ የመድረክ ሪፖርት በፎቶ አስደግፋችሁ ሀሙስ ነሀሴ 1/2018 ዓም በሀርድ እና ሶፍት ኮፒ እንድታሳውቁን።
የስርዓተ ትምህርት ትግበራና ክትትል ብድን
ግልባጭ:-
ለአቶ ሰማኝ አስታጥቄ
3 806
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከ2019 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በ11ኛ ክፍል ተግባራዊ የሚደረጉ 11 የሥራና ተግባር የሙያ ዓይነቶችን ይፋ በማድረግ የክልልና የከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች የመምህራን ቅጥርን ጨምሮ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ መመሪያ አስተላለፈ።
አዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ የሙያ ትምህርትን ለማካተት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት፣
በሁለተኛው ዙር ለሚተገበሩት በእነዚህ 11 የሙያ ዓይነቶች የመርሐ ትምህርት፣ የተማሪ ሞጁል እና የመምህራን መምሪያ ዝግጅት መጠናቀቁ ተገልጿል።
ከ2019 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረጉት 11 የሙያ
ዓይነቶች፦
ብረታ ብረት ሥራ ቴክኖሎጂ
አውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ
አልባሳት ቴክኖሎጂ
ህንፃ ኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋት
ቧንቧ ስራ
ሶፍትዌር ማበልጸግ
ሰብል አመራረት
ጤና ክብካቤ አገልግሎት
ሆቴል አገልግሎት
ፀጉር ሥራና ውበት አገልግሎት
ምግብ ዝግጅት
3 806
Repost from Addis Abeba Education Bureau
+1
የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ዛሬ ከሰዓት የ2018 ዓ/ም የ8ኛ ክፍል ተፈታኞችን ውጤት ይፋ ያደረገ ሲሆን ማለፊያ ውጤቱ 50% ለአካል ጉዳተኞች 45 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን መወሰኑን ገልጿል።
የትምህርት ቢሮው መረጃ በሚያሳየው መሰረት ለፈተና ከተቀመጡ 85 ሺሕ 737 ተማሪዎች መካከል 82 ሺሕ 193 (95.85%) የሚሆኑት 50 እና ከዚያ በላይ ማለፊያ ውጤት አምጥተዋል።
ከተፈታኞቹ መካከል 3 ሺሕ 544 የሚሆኑት ማለፊያ ውጤት አላመጡም።
የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት 96.25 ሲሆን ይህን ያመጣውን አንድ ተማሪ ነው።
60 ተፈታኞች 93% ውጤት አምጥተዋል።
1 ሺሕ 316 ተፈታኞች 90% እና ከዚያ በላይ ውጤት ማምጣታቸው ታውቋል።
የዘንድሮው ውጤት ከአምናው ጋር ሲነጻጸር ምን ይመስላል ?
በ2017 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱት 70 ሺሕ 525 ተፈታኞች፣ 50 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጡት 62 ሺሕ 639 (88.8%) ሲሆኑ፣ 7 ሺሕ 886 ተፈታኞች ማለፊያ ውጤት አላመጡም ነበር።
የዘንድሮ የተፈታኞች ብዛት ከአምናው በ15 ሺሕ 212 የጨመረ ሲሆን፣ ማለፊያ ውጤት ያላመጡ ተፈታኞች ደግሞ፣ ከአምናው በ4 ሺሕ 342 ቀንሷል።
ዘንድሮ የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት 96.25 በአንድ ተማሪ ብቻ ሲሆን፣ በ2017 ዓ/ም ግን 113 ተማሪዎች 94% ውጤት አምጥተው ነበር።
በአንጻሩ፣ ዘንድሮ 90% እና በላይ ያመጡት ተፈታኞች 1 ሺሕ 316 ተማሪዎች ሲሆኑ፣ በ2017 ደግሞ ይህን ውጤት ያመጡት 712 ተማሪዎች ናቸው። በዚህም የዘንድሮው የ604 ብልጫ አለው።
በተያያዘ መረጃ፣ ዘንድሮ ተማሪዎቻቸውን ካስፈተኑ 669 ትምህርት ቤቶች ውስጥ 441ዱ 100% ተማሪዎቻቸውን አሳልፈዋል። እንዲሁም በከተማ ደረጃ ከ93% በላይ ከፍተኛ ውጤት ያመጡት 60 ተማሪዎች ናቸው።
