cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

አዲስ ምልከታ🌍

+ አዲስ የሳይንስ እይታ + አዲስ አስተሳሰብ + አዲስ እውቀት + ሃይማኖት + ፖለቲካ + ኢኮኖሚ + ሙዚቃ # የኢትዮጵያ ትንሳኤ

Більше
Рекламні дописи
1 603Підписники
-124 години
+307 днів
+20130 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

"ሲቀርብም ከተማይቱን አይቶ አለቀሰላት፥ እንዲህ እያለ። ለሰላምሽ የሚሆነውን በዚህ ቀን አንቺስ ስንኳ ብታውቂ፤ አሁን ግን ከዓይንሽ ተሰውሮአል። ወራት ይመጣብሻልና፥ ጠላቶችሽም ቅጥር ይቀጥሩብሻል ይከቡሻልም በየበኵሉም ያስጨንቁሻል፤ አንቺንም በአንቺም ውስጥ የሚኖሩትን ልጆችሽን ወደ ታች ይጥላሉ፥ በአንቺ ውስጥም ድንጋይ በድንጋይ ላይ አይተዉም፥ የመጐብኘትሽን ዘመን አላወቅሽምና።" የሉቃስ ወንጌል 19 : 41-44
Показати все...
1
📚 ድርሳነ ማሕየዊ (ይህ መጽሐፎ፦ የጌታችንን መከራውን፣ ሕማሙን፣ ስቃዩንና ሞቱን የሚያወሳ ድርሳን ሲሆን ይልቁንም በዚህ የሕማማት ወቅት ልንማጸንበት ይገባናል።) ፩- ድርሳነ ማሕየዊን በሰሞነ ሕማማት ብቻ ሳይሆን የጌታን መከራ እና ውለታ እያሰበ አርብ አርብ ቀን የሚጸልየው ‹‹በነፍሱም በሥጋውም ይከብራል፤ በመንግሥተ ሰማያትም እድል ፈንታው ጽዋዕ ተርታው ጌታችንን ከገነዙት ከኒቆዲሞስ እና ከዮሴፍ ጋር ይሆናል›› ፪- እንዲሁም ‹‹በሰባቱ ጊዜያት የሚጸልየው ሰው ቢኖር በነፍሱም በሥጋው ፈጽሞ ይከብራል፡፡ በመንግሥተ ሰማያትም እድል ፈንታው ጽዋዕ ተርታው እስከ ሰባ ዘመን ድረስ በየቀኑ የጌታውን መከራ እያሰባ ካለቀሰ ከጌታ ባለሟል ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ይሆናል›› የሚል ታላቅ ቃልኪ ኪዳን አለው፡  አራቱ ወንጌላውያንና ጌታችን የመከራውን ነገር ያስተማራቸው ኤልሳቤጥ፣ መልቴዳ እና በርዜዳ የጻፉትን ድርሳነ ማሕየዊን በመጸለይ የጌታን ሕማም ልናስብ እና ከቃል ኪዳኑ በረከት ልንሳተፍ ይገባናል፡፡ ድርሳነ ማሕየዊ ልክ እንደ ውዳሴ ማርያም ከሰኞ እስከ እሑድ የተከፋፈለ በመሆኑ ለመጸለይ አይከብድም፡፡
Показати все...
አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥እጅግ ደስ ይበልሽ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥እልል በዪ እንሆ፥ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው ትሑትም ሆኖ በአህያም፥በአህያዪቱ ግልገል በውርንጫዪቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል። ትንቢተ ዘካርያስ 9፥9
Показати все...
ሰላምሽ ዛሬ ነው ሰላምሽ ዛሬ ነው እየሩሳሌም ወደአንች መጥቷልና አምላክ ዘላአለም/2/  ሆሣእና በአርያም እያሉ ዘመሩ  ሕፃናት በኢየሩሳሌም  አንቺ ቤተልሄም የዳዊት ከተማ የሕዝቦችሽ ብርሃን መጣልሽ በግርማ/2 / ኪሩቤል መንበሩን የሚሸከሙለት መስቀል ተሸከመ ሊሆነን መድኃኒት /2 / የኢየሱስን ሕማም ደናግልም አይተው እያለቀሱለት ሄዱ ተከትለው /2/ 
Показати все...
3👍 1
አንዳንዶቻችሁ flat earthን ማመን ምን ይጠቅመኛል ትላላችሁ። ነገር ግን አስፈላጊነቱ አልታያችሁም። ፍላት ኧርዝ የአምስት መቶ ዓመታትን የሳይንስ፣ የሃይማኖት፣ የፖለቲካ እና የርዕዮተ ዓለም አካሄድ የሚቀለብስ (reverse የሚያደርግ) ነው። ይህንን ነው መረዳት ያለባችሁ። በflat earth የሚያምን ሰው በኢቮሉሽን ሊያምን አይችልም። በቢግ ባንግ ሊያምን አይችልም። በፈጣሪ አለማመን አይችልም። ብዙዎች ክርስቲያን ሆነው ነገር ግን ሃይማኖታቸውን በቀጥታ የሚጻረሩትን የuniverse እና evolution ሀሳቦችን ይቀበላሉ። ሁለቱ ነገሮች (ሃይማኖት እና ኢቭሉሽን) ፍጹም ተቃራኒ እንደሆኑ አያስተውሉም፤ ማስተዋልም አይፈልጉም። ነገር ግን ጉዳዩ በሳይንስ ብቻ የሚወሰን አይደለም። ለሃይማኖት፣ ለፍልስፍና፣ ለፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ጭምር ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነ ርዕስ ነው እያነሳን ያለነው። ይህን ለማስረዳት እንዲመቸን አንድ ወቅት ኦባማ የተናገረውን ንግግር ልጥቀስላችሁ፦ "My entire politics is premised on the fact that we are these tiny organisms on this little speck floating in the middle of space,"  "የፖለቲካ አስተሳሰቤ በሙሉ መሠረት የሚያደርገው፦ 'እኛ በአንዲት ዩኒቨርስ ውስጥ የምትንሳፈፍ ትንሽዬ ነጥብ ላይ የምንኖር ጥቃቅን እንስሳት ነን' በሚለው ሀሳብ ላይ ነው" አያችሁ። ዩኒቨርስ የሚባል ነገር ከሌለ፣ ምድር ዝግ አካል ከሆነች፣ እኛ በህዋ ውስጥ የምንንሳፈፍ ጥቃቅን አካላት ካልሆንን፣ የኦባማ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለሙ በሙሉ ይፈራርሳል ማለት ነው። እና አንተ የምታደንቀው ፖለቲከኛ በዚህ የሚያምን ከሆነ አንተም በሱ ታምናለህ። ሁሉም ነገር አጋጣሚ ነው ብለህ ታስባለህ። ወደዚህ ዓለም የመጣሁት በዓላማ (purpose) አደለም ብለህ ወደማሰብ ትደርሳለህ። ፈጣሪህ የእውነት ዩኒቨርስን ከፈጠረ፣ ለምንድነው ፀሐይን ከምድር ይልቅ ትልቅ ያደረጋት? ፀሐይ የተፈጠረችው ለአዳም ብርሃን እንድትሆነው አደለም? የት ሀገር ነው አምፖሉ ከቤቱ ሲበልጥ ያየነው? አምፖሉ ነው ቤቱን መዞር ያለበት፣ ወይስ ቤቱ ነው አምፖሉን መዞር ያለበት? ቤቱን ተሸክሞ አንዲት ሻማን የሚዞር ሰው አይታችሁ ታውቃላችሁ? ፈጣሪ ዓለም ለመፍጠር 4 ቢሊዮን ዓመት ያስፈልገዋል? ሰባት ቀን በቂው አይደለም? እስኪ መልሱልኝ። እግዚአብሔር ዓለም የፈጠረው በሰባት ቀን ነው ወይስ በአራት ቢሊዮን ዓመት ነው? ፈጣሪ አንድ ትሪሊዮን የምድር አይነት ፕላኔቶችን ለምን ይሠራል? ምን ያረጉለታል? አንዷ ምድር አትበቃም? ይህች ምድር ላንተ ነው የተፈጠረችው? ነው ወይስ አይደለም? ላንተ ከተፈጠረች ለምን ፀሐይን እንድትዞር አደረጋት? ላንተ ከፈጠራት የዓለም ሁሉ ማዕከል መሆን አለባት ወይስ የለባትም? እግዚአብሔር የሚወድህ ልጁ ነህ ወይስ አይደለህም? መልስህ አዎ ከሆነ አንተን ለመፍጠር ቀድሞ ጦጣ እና ዳይኖሰር መፍጠር ያስፈልገዋል? በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠርክ ፍጡር ነህ ወይስ አይደለህም? ከሆንክ እንዴት ከዝንጀሮ መጥቻሁ ብለህ ታስባለህ? አእምሮ ያለው ሰው እንደሚጠፉ እንስሶች መሰለ። እንዳለ ነብዩ ዳዊት። እንስሳዊነት የተጠናወተውን የዘመኑን ሳይንስ ተከትለህ አትጥፋ ወገኔ።
Показати все...
👍 7 1🫡 1
ይህ የምትመለከቱት በአሜሪካ ባሕር ሃይል የተሰራ "Rail Gun" የተሰኘ እጅግ አደገኛ የጦር መሳርያ ነው። መሳርያው ኤሌክትሮ-ማግኔቲዝምን በመጠቀም የሚሰራ ሲሆን ጥይቱን በ8270 feet/s ወይም 2700 ሜትር በሰከንድ በሆነ ፍጥነት መተኮስ ይችላል። ይህም Mach 8 ወይም የድምጽን ፍጥነት 8 እጥፍ እንደማለት ነው። መሳርያው እስከ 100 ማይል ማለትም 160 ኪሎሜትር ርቀት ያሉ ኢላማዎችን መምታት የሚችል ሲሆን የባሕር ሃይሉ መርከቦች ላይ ተጠምዶ ሙከራ ተደርጎበታል። ታዲያ ይህ መሳርያ ምድር ዝርግ (flat) እንደሆነች ያረጋግጥልናል። እንዴት? መልሱን ቀጥለን እንይ።
Показати все...
👍 1
ምድር ድቡልቡል ወይም ኳስ ቅርጽ ያላት ከሆነች፣ ካለንበት ቦታ ሆነን ወደፊት ስናይ ምድሪቱ ወደታችን እየወረደች፣ እየወረደች ትመጣለች። ከዚያም ከኛ ሙሉ በሙሉ ትሸፈናለች። ይህንን የሚያደርገው ደግሞ ክቡ ቅርጿ ነው። (ማለትም ምድር ድቡልቡል ከሆነች ያ አይነት ነገር መከሰት አለበት) በዚህም ምክንያት ከኛ እጅግ ርቀው የሚገኙ አካላት በትልቁ ይሸፈናሉ፣ አንዳንድ ነገሮችን እንዲያውም በፍጹም አናያቸውም። ምክንያቱም ከርቩ እንደ ጉብታ ሆኖ በኛና በዚያ አካል መሃል ስለሚቀመጥ። ስለዚህ ይከልለናል። ይህ የሚሆነው አይናችን በቀጥታ (እስትሬት) ያለ ነገርን ብቻ ስለሚያይ ነው። የዚህ ምክንያቱ ደግሞ ብርሃን ቀጥታ መስመር ይዞ ስለሚሄድ ነው። በተመሳሳይ መልኩም፣ ከላይ ያነሳነው መሳርያ ቀጥታ መስመር ይዞ ነው የሚሄደው። ስለዚህ በሱ ስትሬት ያለ 160 ኪሎሜትር ርቆ የሚሄድን አካል ነው መምታት ያለበት። ነገር ግን ምድር ድቡልቡል ከሆነች ይህ በፍጹም ሊፈጠር አይችልም። ግሎብ ላይ ነገሮች ርቀው ሲሄዱ ምን ያህል ከኛ ይሸፈናሉ የሚለው በፎርሙላ ተሰርቶ አለ። በዚህ ፎርሙላ መሠረት 100 ማይል ወይም 160 ኪሎሜትር ርቀው የሚገኙ አካላት በ2 ኪሎሜትር ከፍታ ይሸፈናሉ። ማለትም ግሎብ ምድር ላይ 160 ኪሎሜትር ላይ ያለ አካል ለማየት ከፈለግን ያ አካል ቁመቱ 2 ኪሎሜትር መሆን አለበት፣ ምክንያቱም የምድር ከርቭ ያንን ያህል ነገሮች ስለሚሸፍን። ስለዚህ ከላይ ያለውን መሳርያ እናስበው። እንዴት ነው 160 ኪሎሜትር ያለ ታርጌት ሊመታ የሚችለው? በዓለም ላይ ከተሰሩ ነገሮች ውስጥ 2 ኪሎሜትር ቁመት ያለው ነገር የለም። ደግሞ መሳርያው ለመርከቦች ታስቦ ነው የተሰራው። ስለዚህ እንዴት ሊሰራ ይችላል? ስለዚህ ምድር ግሎብ አይደለችም ማለት ነው።
Показати все...
👍 8 1🙏 1
Yuval Noah Harari: When the flood comes elite will build an ark and leave the rest to drown Harari, whose middle name happens to be Noah, has a long history of warning about the “technological Noah’s Ark” he believes is destined to save the 'elite' while leaving the rest of humanity to die in a mass casualty event.
Показати все...
👍 1
በአሁኑ ጊዜ ነገሮች ከመበለሻሸታቸው የተነሳ ሰዎች ስላለው ሁኔታ መናገር ሁሉ አይፈልጉም። በአደባባይ የውስጣቸውን ሀሳብ አይናገሩም ይልቁንስ ተቀባይነት ያለውን ውሸት ይዋሻሉ። ይህ ወደ ፋሺስት ስርአት መግባታችንን ነው የሚያሳየው። በፋሺዝም ስርአት ገዢው ውሸት ነው። ሰዎች በራሳቸው ፈቃድ እውነትን ከመናገር ራሳቸውን ያቅባሉ። ውሸትን ለመናገር ይፈጥናሉ። ደፍሮ እውነትን መናገር እንደ ትልቅ ወንጀል ይቆጠራል። አምላክን የመናገር ያህል ይወሰዳል። እጅግ አደገኛ ስርአት ነው። ወደዚህ ስርአት የመግባታችን ምክንያቱ ደግሞ ውሸትን የሚወዱ ሰዎች መብዛታቸው ነው። እነሱ ሲበራከቱ ለአገዛዙ መንገድን ይጠርጋሉ። የሀሳብ ፖሊስ ይሆኑታል። ከዚያ አንተ የሆነች ነገር ስትል አፍ አፍህን ይሉሃል። ሁሉም ቦታ ይህ ሲደጋገምብህ ዝም ማለትን፣ መዋሸትን እየለመድክ ትመጣለህ። ዶስቶዬቭስኪ እንዳለው ሰዎችን ላለማስከፋት ተብሎ እውነትን ከመናገር የሚታቀቡበት ጊዜ ደርሷል። ፋሺዝም ማለት ይሄ ነው። የፈጣሪ ያለህ ያስብላል።
Показати все...
👍 16 2
አሁን ያለው የሀገራችን ሁኔታ ያሳስባል። ወደ አንዱ ማጥ ገባን ብለን ስንገረም ከዛም የባሰ ሌላ ገደል ይጠብቀናል። ነገር ተበላሸ ብለን ተገርመን ሳንጨርስ ከዛም በላይ ተበላሽቶ እናያለን። ሀገሪቷ በኢኮኖሚም፣ በፖለቲካም በሁሉም ነገር እየዘቀጠች፣ እየዘቀጠች እየሄደች ነው። መንግስት ያለውን ብር በጦርነት ጨርሶታል። ከዛ ብር ሲያጥረው የኛኑ ብር ከባንክ ስናወጣና ስንልክ መቁረጥ ጀመረ። ግብር ከአቅም በላይ መጠየቅ ጀመረ... አንዱን ጦርነት ሲጨርስ ደግሞ ሌላ ጦርነት ገባ። እንደሱ ቢሆን በዚኛው ጦርነት... ምንም ምንም እንዳይተርፍ አድርጎ ቀብሮ ያዳፍነን ነበር። ሴማውያን ብሎ የሰየማቸውን ህዝቦች ተራ በተራ እያጨደ ጠራርጎ ሊያጠፋ ነበር። በሱ ቤት እግዚአብሔር የለም። እግዚአብሔር ግን መኖሩን አሳየው። ተራ ገበሬዎችን፣ የደርግ ጊዜ ክላሽ ብቻ የነበራቸው...እየተደራጁ፣ ወደ አንድ እየመጡ... ጥቁር ክላሽ፣ ዲሽቃ፣ መድፍ...እያሉ ወደ ሌላ ደረጃ እየመጡ ነው። መከላከያው ኮለኔሎችና ጄነራሎችን ጭምር እያጣ ነው... ያለውን ሃይል እና ገንዘብ ሁሉ አሟጦ ወደዛ እየላከ፣ የላከውም እየከሰመ ነው። በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን ምንም እንዳልተፈጠረ ልማት፣ ብልጽግና..ወዘተ እያለ ስብከቱ አልቀረም.. በዋናው ከተማ የአክሲዮን ገበያ፣ ካፒታል ማርኬት፣ እስታርት አፕ የመሳሰሉ ደመቅ ደመቅ ያሉ ሀሳቦችን እያሰማ ነው። የውጪ ድርጅቶች ወደ ውስጥ እንዲገቡ፣ የቴሌን የአየር መንገድን አክሲዮን እንዲገዙ፣ ጤፍ ቡና ሰሊጥ እንዲነግዱ መንገድ እየከፈተ ነው። ያ እድገት፣ ብልጽግና፣ መሰልጠንን ያመጣል ተብሎ ታስቧል። ግን ያ ለደሃው ምን ይጨምርለታል? እንኳን ደሃውን፣ ደፋ ቀና ብሎ ጉልት የሚሸጠውም አሁን ህይወቱ አደጋ ላይ ነው። እንዴት ነው ዘመናዊ ትምርህት ያልተማረ፣ የፋይናንስ እውቀት ያልቀሰመ ደሃ ከፈረንጅ ነጋዴ ጋ የሚወዳደረው? አይችልምኮ። አይመጣጠንም። ደሃውን ከድህነቱ የሚያወጣ ነገር አደለም ይሄ። ይልቅስ "ዘመናዊ ሁን ከጊዜው ጋ ተጓዝ፣ መጓዝ ካልቻልክ ትበላለህ" ነው እየተባለ ያለው። ትበላለህ በቃ። ደሃ ሆንክ አልሆንክ ጣጣው አደለም። survival of the fittest ነው። ዳርዊኒዝም በተግባር ሊተገበር ነው በቃ። አቅም ያለው ብልጥ የሆነው አምልጦ ይወጣል። ዶላርና ክሪፕቶ እየነገደ ሚሊዬነር ይሆናል። ምስኪኑ ደሃ ደግሞ በቃ በረሃብ ያልቃል። አለፍ ሲልም ባርያ ይሆናል። ሌላ outcome የለውም። በቃ ለደሃ ያለው ቦታ ይህ ነው። "ደሃ ተበደለ ፍርድ ተጓደለ" የሚለው የጥንቱ አባባል አሁን አይሰራም። "የታባቱ ለምን ድራሹ አይጠፋም" ነው የአሁኑ ፖሊሲ። በቃ ሀብታም መሆን አለብህ። ሰርተህ ለፍተህ ሊሆን ይችላል፣ ወይም ክሪፕቶ ነግደህ ሊሆን ይችላል፣ ወይ ቲክቶክ ሰርተህ፣ ወይም ደግሞ ዋሽተህ ሰርቀህ አጭበርብረህ ሊሆን ይችላል እስካልተያዝክ ድረስ... ብቻ የሆነ ነገር ይኑርህ። አንተ ታመልጣለህ። ሌላው እንደ ኖህ ዘመን ጎርፍ ቢወስደው አንተ አምልጠሃል ስለሱ አይመለከትህም። አሁን ላይ እየመጣ ያለው አስተሳሰብ እንዲህ አይነት ነው። ፈረንጆቹ ያሰቡልን የ eugenics ድግስ ሊተገበር ነው፣ ልንጠፋ...በቃ በነሱ ቤት እግዚአብሔር የለም...ደሃ ያልቃል ይጠፋል....
Показати все...
👍 11