Ethiopian Business Network
Открыть в Telegram
የኢትዮጵያ ብቸኛ የስራ ፈጠራ መድረክ! ማንኛውንም ፕሮጀክት፣ ሃሳብ ለህዝብ በማድረስ አዳዲስ ድርጅቶችን ለማቋቋም የነፃ እገዛ እናደርጋለን! ያነጋግሩን!
Больше4 539
Подписчики
-324 часа
Нет данных7 дней
+430 день
Загрузка данных...
Похожие каналы
Облако тегов
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Входящие и исходящие упоминания
---
---
---
---
---
---
Привлечение подписчиков
июль '26
июль '26
+17
в 0 каналах
июнь '26
+85
в 0 каналах
Get PRO
май '26
+62
в 0 каналах
Get PRO
апрель '26
+46
в 0 каналах
Get PRO
март '26
+31
в 0 каналах
Get PRO
февраль '26
+14
в 0 каналах
Get PRO
январь '26
+18
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '25
+15
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '25
+20
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '25
+141
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '25
+21
в 0 каналах
Get PRO
август '25
+155
в 0 каналах
Get PRO
июль '25
+28
в 0 каналах
Get PRO
июнь '25
+31
в 0 каналах
Get PRO
май '25
+28
в 0 каналах
Get PRO
апрель '25
+22
в 0 каналах
Get PRO
март '25
+47
в 0 каналах
Get PRO
февраль '25
+90
в 0 каналах
Get PRO
январь '25
+58
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '24
+49
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '24
+312
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '24
+33
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '24
+19
в 0 каналах
Get PRO
август '24
+44
в 0 каналах
Get PRO
июль '24
+36
в 0 каналах
Get PRO
июнь '24
+35
в 0 каналах
Get PRO
май '24
+21
в 0 каналах
Get PRO
апрель '24
+14
в 0 каналах
Get PRO
март '24
+19
в 0 каналах
Get PRO
февраль '24
+40
в 0 каналах
Get PRO
январь '24
+11
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '23
+22
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '23
+21
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '23
+18
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '23
+21
в 0 каналах
Get PRO
август '23
+13
в 0 каналах
Get PRO
июль '23
+34
в 0 каналах
Get PRO
июнь '23
+16
в 0 каналах
Get PRO
май '23
+23
в 0 каналах
Get PRO
апрель '23
+47
в 0 каналах
Get PRO
март '23
+155
в 0 каналах
Get PRO
февраль '23
+2 484
в 0 каналах
Get PRO
январь '23
+6 408
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '22
+96
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '22
+66
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '22
+82
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '22
+78
в 0 каналах
Get PRO
август '22
+115
в 0 каналах
Get PRO
июль '22
+37
в 0 каналах
Get PRO
июнь '22
+65
в 0 каналах
Get PRO
май '22
+554
в 0 каналах
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 07 июля | +1 | |||
| 06 июля | +1 | |||
| 05 июля | +4 | |||
| 04 июля | +2 | |||
| 03 июля | +5 | |||
| 02 июля | +1 | |||
| 01 июля | +3 |
Посты канала
"ኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ሥራ ቢኖርም ሰራተኛ ማግኘት በጣም ከባድ ሆኗል" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
#FastMereja I ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ሥራ ቢኖርም ሰራተኛ ማግኘት በጣም ከባድ ሆኗል አሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፥ ወላጆች ከከተማ ውጪ የሚሰሩ ሥራዎችን ወጣቶች እንዲሞክሯቸው ማበረታታት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡
ለአብነትም በግንባታ ላይ በሚገኘው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በቂ የሰው ኃይል ማግኘት አዳጋች መሆኑን ነው ያስረዱት፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ የቤት ሰራተኝነት ሥራን የሚሰሩ ሰዎች ቁጥር እጅግ ጥቂት መሆኑን ጠቁመው፥ ለተመሳሳይ ሥራ ከሀገር የሚወጡ ዜጎች ቁጥር ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡
ከሀገር የወጡ ወጣቶች በቀን ለ16 ሰዓታት ያህል ሰርተው ራሳቸውን ሲለውጡ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ወጣቶች ግን ጊዜን በአግባቡ የመጠቀም ክፍተት እንዳለባቸው ነው የገለጹት፡፡
በሁለት እና ሶስት የሥራ ፈረቃዎች በመስራት አቅምን ማሳደግና መተጋገዝ ካልተቻለ የኑሮ ውድነት ከዚህ በላይ ሊሆን አንደሚችል አመልክተዋል፡፡
#ፖለቲካ
| 2 | የካናዳ ቪዛ
ካናዳ በብዛት ቪዛ ከምትከለክላቸው 9 አገራት ኢትዮጵያን 7ተኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠች:: | 417 |
| 3 | የኡጋንዳው "ራንቸርስ ፋይነስቲ" ወደ ኢትዮጵያ የሥጋ ምርቶችን መላክ ጀመረ
የኡጋንዳው የሥጋ ማቀነባበሪያ ኩባንያ "ራንቸርስ ፋይነስቲ" የመጀመሪያውን የተቀነባበረ የበሬ ሥጋ ምርት ወደ ኢትዮጵያ መላክ መጀመሩን አስታውቋል።
ኩባንያው በወር 20 ቶን የሚደርስ ስቴክ፣ ሶሴጅ እና ሌሎች የሥጋ ምርቶችን ለኢትዮጵያው "ዳይመንድ ሆቴል እና ሬስቶራንት ግሩፕ" ለማቅረብ ስምምነት ተፈራርሟል።
የፕሬዚዳንቱ የግብርና አማካሪ ዶክተር ሂላሪ ሙሶኬ በሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደገለጹት፤ ይህ ዕርምጃ የኡጋንዳን ኢኮኖሚ ለማሳደግ የሚረዳው የ"እሴት መጨመር" ስትራቴጂ አካል ነው።
አንድ ኪሎ ጥሬ ሥጋ ወደ 4 ዶላር ሲሸጥ፣ ተቀነባብሮ ሲላክ ግን ዋጋው እስከ 50 ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ጠቅሰው፣ ይህም ለአገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እንደሚያስገኝ ገልጸዋል።
#ቅዳሜገበያ
#etbusinessview
#Ethiopia | 483 |
| 4 | በቤንዚን የሚንቀሳቀስ የ ' Sandstorm S24 ' ፒክአፕ ተሽከርካሪን ወደ ሙሉ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ በተሳካ ሁኔታ መቀየሩን የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የኢንጂነሪንግ ኮሌጅ አሳውቋል።
ፕሮጀክቱ በዩኒቨርሲቲው የአውቶሞቲቭ ኢንጂነሪንግ ተመራማሪዎች የተመራ ሲሆን ተሽከርካሪውን የመከላከያ ሎጀስቲክስ ዋና መምሪያ ነው የሰጠው።
ተሽከርካሪው እስከ 400 ኪሎ ሜትር የመንገድ ጉዞ እንደሚያደርግ፣ የአሠራር ወጪን በ88 በመቶ እንደሚቀንስ፣ ዜሮ የጭስ ልቀት እንደሚያስመዘግብ እና የፕሮጀክቱ ወጪ ከ4 እስከ 5 ዓመታት ውስጥ ሊመለስ እንደሚችል ተገልጿል።
በፕሮጀክቱ ፦
👉 70 ኪሎዋት PMSM ኤሌክትሪክ ሞተር፣
👉 65 ኪሎዋት ሰዓት ሊቲየም-አዮን ባትሪ፣
👉 3.3 ኪሎዋት AC/DC ቻርጂንግ ስርዓት እና Regenerative Braking ቴክኖሎጂ መተግበሩ ተመላክቷል።
ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ/ም | 490 |
| 5 | አስቸኳይ ማሳሰቢያ ሰጠ‼
የስም ዝውውር ያላደረጉ የንብረት ባለቤቶች በአስቸኳይ እንዲያጠናቅቁ ተጠይቋል።
ከማንኛውም አካል መሬትና ቤት ገዝተው እስካሁን የስም ንብረት ዝውውር ያላደረጉ እና የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ በስማቸው ያልቀየሩ ባለንብረቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ ሂደቱን እንዲያጠናቅቁ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስቸኳይ ማሳሰቢያ አስተላለፈ።የቢሮው ኃላፊ አቶ መኮንን ያኢ ባስተላለፉት ጥሪ፡-
📌የስም ዝውውር በወቅቱ አለመደረጉ ንብረት የገዙ ወገኖችን ለከፍተኛ የህግና የንብረት መብት እገዳ አደጋ እያጋለጠ ይገኛል።
📌 በመሆኑም ባለንብረቶች መብታቸውን ለማስከበር በአስቸኳይ ወደ መሬት ተቋማት በመቅረብ ካርታቸውን በስማቸው እንዲያዞሩ በጥብቅ አሳስበዋል። | 446 |
| 6 | በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ ከባድ ውጊያ ተቀሰቀሰ‼
የሱዳን ጦር ኃይል ከኢትዮጵያ ቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ጋር የምታዋስነውን ስልታዊ የድንበር ከተማ ኩርሙክን ለመቆጣጠር መጠነ-ሰፊ የአየርና የምድር ጥቃት መክፈቱን አናዶሉ የጦር ምንጮችን ጠቅሶ ዘገበ።
ከተማዋ ካለፈው መጋቢት ጀምሮ በፈጣን ድጋፍ ኃይል (RSF) እና በአጋሩ SPLM-N ቁጥጥር ስር የነበረች ሲሆን፣ አሁን የተቀሰቀሰው ከባድ ውጊያና የድሮን መረጋገጥ ግጭቱ ወደ ጎረቤት ሀገር ኢትዮጵያ ሊሻገር ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል። | 500 |
| 7 | ሲሚንቶ‼️
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኘውና በጠቅላይ ሚንስትሩ ተመርቆ ስራ ከጀመረ አመታትን ያስቆጠረው የመንግስት እና የግል ሽርክና የሆነው ግዙፉ የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በደላሎች እየተፈተነ ይገኛል።
ከወራት በፊት ከ1200-1500 ብር ይሸጥ የነበረው ይህ ሲሚንቶ አሁን ላይ ዋጋው በእጥፍ ጨምሮ ደብረብርሃን ከተማ ላይ እስከ 2500 ብር እየተሸጠ ይገኛል። ፋብሪካው እየተቋቋመበት ቦታ ለሚ ላይ 1900 ብር እየተሸጠ ይገኛል።
የሲሚንቶ አስመጪዎች እና ነጋዴዎች አሁን ከፋብሪካው ሲሚንቶ ለማግኘት አስቸጋሪ መሆኑን እና በደላላ መሆኑን ገልፀውልናል።
ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ስራ ከጀመረ ጀምሮ የሀገሪቱን የሲሚንቶ እጥረት በመቅረፍ እና ገበያውን በማረጋጋት እረገድ አስተዋጽኦው የጎላ ቢሆንም አሁን በደላሎች እየተፈተነ በመሆኑን የሚመለከተው አካል መፍትሔ ቢሰጥበት መልካም ነው። | 534 |
| 8 | በአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ቁጥጥር አዋጅን ተከትሎ ተከራዮች «ቤት ልቀቁ» የሚል ጫና እየበረታባቸው መሆኑን ገለጹ::
በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የተለያዩ የኮንዶሚኒየም ሳይቶች የሚኖሩ ነባር ተከራዮች፣ አዲሱን የቤት ኪራይ ቁጥጥር አዋጅ ተገን በማድረግ በአከራዮች አማካኝነት «ቤት ልቀቁ» የሚል ከፍተኛ ጫና እና ማስጠንቀቂያ እየደረሳቸው መሆኑን በምሬት በመግለጽ ላይ ናቸው። መንግሥት በቅርቡ ባወጣው አዋጅ መሠረት በአከራይና ተከራይ መካከል የሚደረገው የዋጋ ጭማሪ በተወሰነ ልክ ብቻ መሆን እንዳለበት ቢደነግግም፣ በርካታ አከራዮች ግን በተቀመጠው ሕጋዊ የዋጋ ገደብ መሠረት ማከራየት ስላልፈለጉ ነባር ተከራዮችን አስወጥቶ በአዲስና ከፍ ባለ ዋጋ ለሌሎች ማከራየትን እንደ ዋነኛ አማራጭ እየወሰዱት ይገኛል።
ተከራዮች እንደሚሉት ከሆነ፣ አከራዮች ይህንን ሕጋዊ የዋጋ ገደብ ለመሸሽና ተከራዮችን ለማስገደድ የተለያዩ ምክንያቶችን በመደርደር ላይ ናቸው። «ራሴ ልገባበት ነው» ወይም «እህቴ/ወንድሜ ሊኖሩበት ነው» የሚሉ የቤተሰብ ሰበቦችን በማቅረብ ተከራዮች በአስቸኳይ እንዲለቁ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ተነግሯል። በተለይም የሰኔ ወር መጠናቀቅን ተገን በማድረግ፣ አሮጌውን ውል ለማደስ ፈቃደኛ ያልሆኑና አዲስ ተከራይ በከፍተኛ ዋጋ ለማስገባት የሚፈልጉ አከራዮች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎችን ለእንግልትና ለቀውስ እየዳረገ ነው።
በከተማዋ የተፈጠረው ይኸው ሕገ-ወጥ አሠራርና ጫና ከቁጥጥር ውጪ ከመሆኑ በፊት፣ የሚመለከተው የመንግሥት አካል በአስቸኳይ ጣልቃ እንዲገባና መፍትሔ እንዲሰጣቸው ተከራዮች ጠይቀዋል፡፡ | 561 |
| 9 | ለጣሊያን ሀገር የሥራ ዕድል የምዝገባ ጥሪ ቀርቧል።
📌እንዳትታለሉ አንብቡት - ሼር
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በገባው የሁለትዮሽ ስምምነት መሰረት በህጋዊ የውጪ ሀገር ሥራ ስምሪት ፕሮግራም በጣሊያን ሀገር በሆቴልና መስተንግዶ (Hospitality) ዘርፍ የሰው ኃይል ይፈለጋል።
የዜጎችን መብት፣ ደህንነት እና ጥቅም በማስጠበቅ ህጋዊ በሆነ መንገድ ወደ ጣሊያን ሄደው መስራት የሚፈልጉ አመልካቾች እንዲያመለክቱ እናሳውቃለን።
🏨 የሥራ መደቦች፦
🔹ጸሐፊ(Commis de Rang / F&B Server) – 19 ቦታዎች
🔹 የፅዳት ሰራተኛ (Room Attendant / Housekeeping) – 20 ቦታዎች
🔹 ረዳት ሼፍ (Commis Chef) – 13 ቦታዎች
🔹 የእቃ አጣቢ (Kitchen Steward / Dishwasher) – 11 ቦታዎች
🔹 የወለል ረዳት (Floor Porter / Houseperson) – 3 ቦታዎች
🔹 የቢሮ አስተናጋጅ (Front Office Agent / Receptionist) – 4 ቦታዎች
🔹 የጥገና ቴክኒሺያን (Maintenance Technician) – 1 ቦታ
🔹 የስፓ ቴራፒስት / የማሳጅ ባለሙያ (Spa Therapist / Masseuse) – 1 ቦታ
📌 የማመልከቻ መስፈርቶች
✅ ከስራው ጋር ተያያዥ የስራ ልምድ ያላቸው ተመራጭ ናቸው።
✅ ለአብዛኛዎቹ የስራ መደቦች የእንግሊዝኛ እና/ወይም የጣሊያንኛ ቋንቋ እውቀት ያስፈልጋል።
✅ ለአንዳንድ የሙያ መደቦች ተዛማጅ የሙያ ማረጋገጫ ወይም የሆቴል እና መስተንግዶ ትምህርት ተመራጭ ነው።
📅 የሥራ ቆይታ
አብዛኛዎቹ የስራ መደቦች ለ2026/2027 የክረምት የቱሪዝም ወቅት የሚቀጠሩ ሲሆን፣ አንዳንድ የስራ መደቦች ዓመቱን ሙሉ ወይም በበጋና በክረምት ወቅት የሚሰሩ ናቸው።
✅ ለመመዝገብ
1.Labor ID ካሎት በተሰጠው የማመልከቻ ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ያመልክቱ።
2.Labor ID ከሌሎት የሚከተሉትን ሂደቶች ይከተሉ፦
1. በ lmis.gov.et ይመዝገቡ።
በአቅራቢያዎ ባለ የአንድ ማዕከል (ወረዳ ወይም ቀበሌ) በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ ይስጡ እና የሰራተኛነት መለያ ቁጥር (Labor ID) ይያዙ።
1. Labor ID ካገኙ በኋላ በተሰጠው የማመልከቻ ማስፈንጠሪያ https://forms.lmis.gov.et/italy-hotel/ ገብተው መረጃዎትን በትክክል ሞልተው ያመልክቱ።
ማሳሰቢያ
📌ምዝገባም ሆነ ስምሪቲ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ ብቻ የሚከናወን ሲሆን ሚኒስቴሩ ለየትኛውም አካል ውክልናም ሆነ ፈቃድ አለመስጠቱን እንገልፃለን።
📌ምንም አይነት ክፍያም የለውም ብሏል የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር።
#WasuMohammed | 844 |
| 10 | Нет текста... | 492 |
| 11 | #IMF
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ለኢትዮጵያ የ464 ሚሊዮን ዶላር ተጫማሪ ብድር ማጽደቁን አሳወቀ።
👉 ሁለተኛ ዙር የዋጋ ንረት ጫናዎች ከተከሰቱ ብሔራዊ ባንክ ፖሊሲውን ይበልጥ ለማጥበቅ ዝግጁ መሆን እንደሚኖርበትም አሳስቧል።
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ስራ አስፈፃሚ ቦርድ ለኢትዮጵያ የተፈቀደውን የተራዘመ የብድር አገልግሎት (ECF) አምስተኛ ግምገማ ማጠናቀቁን አስታወቀ።
ቦርዱ ግምገማውን ተከትሎ ኢትዮጵያ የ464 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ክፍያ እንድታገኝ ወስኗል።
ይህ አዲስ ክፍያ ኢትዮጵያ እስካሁን ከድርጅቱ ያገኘችውን ጠቅላላ የገንዘብ መጠን ወደ 2.647 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ያደረገው ሲሆን፤ ሀገሪቱ የክፍያ ሚዛኗን እንድታስተካክልና የበጀት ፋይናንስ ፍላጎቷን እንድታሟላ ይረዳታል ተብሏል።
በመግለጫው ላይ እንደተጠቀሰው፣ የኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ አፈጻጸም ጠንካራ ቢሆንም በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ጦርነት በኢኮኖሚው ላይ ጫና ፈጥሯል።
በተለይም የነዳጅ ዋጋ መጨመር ያስከተለውን የፋይናንስ ጫና ለመቋቋም እንዲቻል፣ በፕሮግራሙ ስር ወደፊት ሊለቀቅ ከነበረው ገንዘብ ውስጥ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋው ቀድሞ እንዲለቀቅ (rephasing) ተደርጓል።
የገንዘብ ድርጅቱ ቦርድ ኢትዮጵያ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም (HGER) በኩል ያስመዘገበችውን ውጤት አድንቋል።
በሪፎርሙ አማካኝነት የወጪ ንግድ ማደጉ፣ የታክስ ገቢ አሰባሰብ መሻሻሉ እና የውጭ ምንዛሬ ክምችት መጨመሩ ለኢኮኖሚው ጥንካሬ ማሳያዎች መሆናቸው ገልጿል።
በተጨማሪም መንግስት ከውጭ አበዳሪዎችና ከዩሮ ቦንድ (Eurobond) ባለቤቶች ጋር እያደረገ ያለው የዕዳ ሽግሽግ ድርድር ውጤት እያሳየ መሆኑ በመግለጫው ተመልክቷል።
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ምክትል ዋና ዳይሬክተር ናይጄል ክላርክ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የዋጋ ንረትን ለመግታት እየተገበረ ያለው ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ ተገቢ መሆኑን ገልጸው፣ እርምጃው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።
የዋጋ ንረት ስጋቶችን (inflation expectations) ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን ማስቀጠል አሁንም ተገቢ ነው ያለው ድርጅቱ ብሔራዊ ባንክም ሁለተኛ ዙር የዋጋ ንረት ጫናዎች ከተከሰቱ ፖሊሲውን ይበልጥ ለማጥበቅ ዝግጁ መሆን ይኖርበታል ሲልም አሳስቧል።
ባንኩ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግና በባንኮች መካከል ጤናማ ውድድር እንዲኖር እየወሰዳቸው ያሉ እርምጃዎች የሚበረታቱ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ድጎማን በሂደት በማንሳት ለልማትና ለማህበራዊ አገልግሎቶች የሚውል ተጨማሪ በጀት መፍጠር እንደሚገባ ያመለከተው መግለጫው፤ በዚህ ሂደት ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች እንዳይጎዱ አስፈላጊው ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባ አጽንዖት ሰጥቷል።
ብሔራዊ ባንኩ በወርቅ ግብይት ገበያ ውስጥ ያለውን ቀጥተኛ ተሳትፎ የሚያቆምበትንና ከገበያው የሚወጣበትን ግልጽና ስልታዊ እቅድ ማውጣት እንዳለበትም አመላክቷል።
የብሔራዊ ባንክን ገለልተኝነትና የፖሊሲ ማስፈጸም አቅም ለማሳደግ፤ አዳዲስ ገለልተኛ የቦርድ አባላትን መሾምና የባንኩን የካፒታል አቅም ማጠናከር (Recapitalization) አስፈላጊ መሆኑንም በመግለጫው ገልጿል። | 529 |
| 12 | Нет текста... | 566 |
| 13 | ቢሾፍቱ አየር ማረፊያ ጎርፍ ጉዳት አድርሳል::
ለተፈናቃይ አርሶአደሮች የተሰራው መኖሪያ መንደር ላይ ጎርፍ ገብቶ ጉዳት ማድረሱ እየተገለፅ ነው:: | 617 |
| 14 | ከሪል እስቴት አልሚዎች እና ከግለሰቦች በሰነዶች ማረጋገጫ ንብረት ገዝተው ወደመሬት ተቋማት በመቅረብ ስም ያላዞሩና የይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጫ ያልያዙ ባለንብረቶች ሂደቱን እንዲያጠናቅቁ ጥሪ ቀረበ
ቀደም ባለ ጊዜ በመሬት ላይ ያረፈን ንብረት ተሻሽጠው (ሸጠው/ገዝተው) እስካሁን የስመ-ንብረት ዝውውር ያላደረጉ (የይዞታ ማረጋገጫ) ያልያዙ አካላት በአጭር ጊዜ ሂደቱን እንዲያጠናቅቁ ጥሪ ቀረበ። የከተማ አስተዳደሩ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ መኮንን ያኢ ከኤ ኤም ኤን ዲጂታል ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት የስመ ንብረት ዝውውሩ በወቅቱ አለመደረግ ንብረት ገዝተው ነገር ግን የንብረት ባለቤት ማረጋገጫ ያልያዙ ወገኖች ለጉዳት እየዳረገ ነው ብለዋል።
የቢሮ ኃላፊው ስለ ስመ ንብረት ዝውውር ምንነት ሲናገሩም አንድ ሰው ያፈራውን ንብረት (Property) በራሱ ለሌላ ሶስተኛ ወገን የሚያስተላልፍበት ስርዓት መሆኑን ጠቅሰው የመጨረሻው ግቡም የይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጫን መያዝ ነው ብለዋል። ነገር ግን በተለያየ ምክንያት ይሄንን ሳያደርጉ የቀሩ እና የሚቀሩ አካላት መኖራቸውን የጠቆሙት ኃላፊው ከዚህ በፊት ሽያጭ ተሻሽጠው (ገዝተው/ሸጠው) ነገር ግን የስም ዝውውር / የይዞታ ካርታ በስማቸው ያላወጡ ባለንብረቶች ለአደጋ እንዳይጋለጡ በማሰብ መንግስት በአጠረ ጊዜ ሂደቱን እንዲያጠናቅቁ ጥሪ ያቀርባል ብለዋል። | 581 |
| 15 | Studying in the U.S. Information Session
July 9, 2:00 PM – 4:00 PM
Satchmo Center, U.S. Embassy
Sign-up to attend this event - https://forms.gle/8BrDfYc1cZXoaXBs8
Access to the Satchmo Center is by membership only, please register at https://jazzio.land/register . Screenshot your QR code and present it along with your ID. | 623 |
| 16 | ዱባይ ለኢትዮጵያውያን ማስጠንቀቂያ‼️
የዱባይ ፖሊስ በኢትዮጵያውያን ላይ የመጨረሻ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጠ‼️
በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በዲጂታል መድረኮች በሚያደርጓቸው እንቅስቃሴዎች ላይ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የዱባይ ፖሊስ እና የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤት ጥብቅ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል። ይህ ማስጠንቀቂያ የተሰጠው በትውልድ ኢትዮጵያውያን መካከል በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እየተደረጉ ያሉ አንዳንድ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከል ነው።
የዱባይ ፖሊስ እና የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤት በጋራ ባዘጋጁት መድረክ እንደተገለጸው፣ በአረብ ኤምሬቶች የሳይበር ወንጀል ህግ መሰረት የሚከተሉት ድርጊቶች ከፍተኛ ቅጣት እንደሚያስከትሉ ተገልጿል፦
📌 የጥላቻ ንግግር: በማህበረሰቡ መካከል መከፋፈልን፣ ጥላቻን እና ንቀትን የሚያንጸባርቁ የብሄር ፖለቲካ ቅስቀሳዎችን ሶሻል ሚዲያ ላይ መለጠፍ።
📌 ስድብ እና ስም ማጥፋት: ግለሰቦችን ወይም ተቋማትን በቪዲዮ፣ በጽሁፍ ወይም በኮሜንት መዝለፍ እና ስም ማጥፋት ህግ የተከለከለ ነው።
📌 ያለ ፈቃድ መረጃ ማውጣት: የግለሰቦችን ግላዊነት የሚነኩ ምስሎችን፣ ቪዲዮዎችን ወይም መረጃዎችን ያለ ፈቃድ ማሰራጨት በህግ የሚያስቀጣ ነው።
📌 የገንዘብ ማሰባሰብ: ያለ መንግስት ፈቃድ በማህበራዊ ሚዲያ በኩል በስምምነት ገንዘብ ማሰባሰብ በኢምሬትስ ህግ የተከለከለ ነው። | 684 |
| 17 | ሥራ-ፈት የሚያበዛ መመሪያ ሊስተካከል ይገባል!
በየሰፈሩና መንደሩ ያሉ የንግድ ቤቶችና ሱቆች እየጠፉ ነው።
አትክልት ቤት ስትሄድ ተዘግቷል፣ ሱቅ ተዘግቷል፣ ስጋ ቤት ተዘግቷል። አሃ! ምቾት ነሳችሁን እኮ?
አንዲት ዕቃ ፍለጋ ሩቅ እየተጓዝን ነው። ለትንሽ ለትልቁ ሩቅ መጓዝ ልክ አይደለም።
⛔መኖሪያ ቤት መነገጃ አይደለም፤
🚫ያላለቀ ቤት ለንግድ አይከራይም፤
ለካስ የሱቆች መጥፋት ምክንያቶች የላይኞቹ መመሪያዎች ናቸው። መነገድ የፈለገ የመኖሪያ ቤቶችን አገልግሎት ወደ ንግድ ቤት ቀይሩ ይላሉ።
የቅያሬው ዋጋ ቀላል አይደለም። ሚሊዮኖች ይጠይቃል። ያንን መቀየር ነገም ችግር አለው። ቤቱ ሲሸጥ 15% Capital Gain Tax ያስከፍላል። ህዝቡም ይህንን አልፈልግም ብሎ ለንግድ ቤት ያከራያቸውን ነጋዴዎች ከቤቱ እያስወጣ ነው። ችግር መጺዑ ማለት ነው።
የንግድ ፈቃድ እድሳት ላይ ሥራ የሚያቆም ብዙ ነው። ተዘጋጅ!
ስማ! ስማ! ንግድ ስታስቆም ሥራ-ፈት እያበዛህ ነው። ማህበረሰቡም እየተቸገረ ነው።
ከመኖሪያ ቤት ላይ 30% ድረስ ለንግድ ቤት ማከራየት ይቻላል የተባለው ቀረ እንዴ? ያ የተፈቀደው እስከ ግንቦት 30 ብቻ ነበር?
ሥራ-ፈት የሚያበዛ መመሪያ ሊስተካከል ይገባል። | 635 |
| 18 | Abay Bank has become the fifth company to list on Ethiopia’s Securities Exchange, marking another milestone in the country’s financial reforms.
The listing strengthens market liquidity and transparency without raising new capital.
More banks are expected to join as Ethiopia expands its young stock market.
The ESX aims to grow to 50 listed companies by 2030, boosting long-term investment. | 650 |
| 19 | 100 ሺህ የኤሌክትሪክ መኪናዎች እና የኢንሹራንስ ዘርፉ አዲሱ ቀውስ
በኢትዮጵያ የነዳጅ ተሽከርካሪዎች ላይ የተጣለውን ገደብ ተከትሎ ወደ 100,000 የሚጠጉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EVs) ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ቢሆንም፣ ከፍተኛ የጥገና ወጪያቸው ግን የሀገር ውስጥ የኢንሹራንስ ኩባንያዎችን ከባድ ፈተና ውስጥ ጥሏል።
የኢቪ መኪናዎች መበራከት በነዳጅ ዘመን መመሪያዎች ለሚመራው የኢንሹራንስ ዘርፍ አዲስ ቀውስ ፈጥሯል።
የኢቪ መኪናዎች ዋነኛ የቴክኒክ ስጋት እስከ 50 በመቶ የሚሆነውን የተሽከርካሪውን አጠቃላይ ዋጋ የሚይዘው ባትሪ ነው።
በአሁኑ ወቅት በሀገር ውስጥ ልዩ የባትሪ ጥገና መሠረተ-ልማት እና ባለሙያ ባለመኖሩ ምክንያት፣ በትናንሽ አደጋዎች እንኳ ባትሪው ሲጎዳ መኪናው ሙሉ በሙሉ እንደወደመ እንዲቆጠር እያደረገ ነው።
ይህንን ከፍተኛ ስጋት ለመቀነስ ኢንሹራንሶች አዳዲስ አሰራሮችን ተግባራዊ እያደረጉ ይገኛሉ፦
የተጠቃሚ ድርሻ ማሳደግ፦ የኢቪ ባለቤቶች ከአደጋ በኋላ የሚከፍሉትን የወጪ ድርሻ (claim expense) ከነባሩ 10 በመቶ ወደ 15 በመቶ አሳድገዋል።
የባትሪ ወጪ ተጋሪነት፦ ተሽከርካሪው ሙሉ በሙሉ ጠፍቷል በሚባልበት ጊዜ የባትሪውን መተኪያ ወጪ ከ25 እስከ 30 በመቶ የሚሆነውን ባለቤቱ እራሱ እንዲሸፍን እያስገደዱ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ በሀገሪቱ ያለው የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና የስፔር ፓርትስ አቅርቦት እጥረት የኢንሹራንስ ክፍያ ይገባኛል ጥያቄ (claims) ሂደቱን እጅግ አወሳስቦታል።
በዚህም ምክንያት የላቁ የኢቪ ሞዴሎች ይፋዊ ወኪል (dealer) የሌላቸው ሲሆን፣ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በኮንትሮባንድ ወይም በደንበኞች የግል ጥረት በሚገቡ እቃዎች ላይ ጥገኞች ሆነዋል።
የሞተር ኢንሹራንስ ከሀገር ውስጥ የኢንሹራንስ ኢንዱስትሪ 36 ቢሊዮን ብር ጠቅላላ ገቢ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆነውን የሚሸፍን እና ከተከፈሉ የጉዳት ካሳዎች 54 በመቶውን የሚይዝ በመሆኑ፣ ይህ አዲሱ የኢቪ ቀውስ በዘርፉ ላይ ከፍተኛ የገንዘብ ጫና እየፈጠረ ይገኛል።
ምንጭ: አዲስ ፎርቹን | 678 |
| 20 | Нет текста... | 607 |
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
