ru
Feedback
Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር

Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር

Открыть в Telegram

Welcome to Ethio Radar, a professional news analysis platform brought to you by a dedicated team of experienced journalist. stay informed,stay on radar! እንኳን ወደ ኢትዮ ራዳር ቻናል መጡ,ሀሳብ፣አስተያየት፣ መረጃ ለማጋራት ማስታወቂያ ለማሰራት በ @Ethioradarr01 ያናግሩን

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር

Канал Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር (@ethioradarinfo) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 56 958 подписчиков, занимая 169 место в категории Маркетинг и PR и 558 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 56 958 подписчиков.

Согласно последним данным от 26 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -1 366, а за последние 24 часа — -193, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 2.05%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 0.84% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 1 172 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 479 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 3.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
Welcome to Ethio Radar, a professional news analysis platform brought to you by a dedicated team of experienced journalist. stay informed,stay on radar! እንኳን ወደ ኢትዮ ራዳር ቻናል መጡ,ሀሳብ፣አስተያየት፣ መረጃ ለማጋራት ማስታወቂያ ለማሰራት በ @Ethioradarr01 ያናግሩን

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 27 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Маркетинг и PR.

56 958
Подписчики
-19324 часа
-1 0727 дней
-1 36630 день
Архив постов
ቴምር ፕሮፐርቲስ #Temir_Properties 💥 አዲስ የቤት ባለቤት የሚሆኑበት ወርቃማ ዕድል በሳርቤት አደባባይ! #09-90-22-09-02 በከተማዋ እምብርት ሳርቤት አደባባይ ላይ እጅግ ዘመናዊና ምቹ የሆኑ የመኖሪያ አፓርትመንቶችን ለሽያጭ አቅርቧል። ✨  3B + G + 23 👉 100% ሙሉ ክፍያ =30% ልዩ ቅናሽ 👉20% ቅድመ ክፍያ — ቀሪውን በሒደት የሚከፍሉበት ምቹ ሁኔታ። ✅ የካሬ አማራጮች: 🔥ባለ 1 መኝታ: 73 ካሬ               👍ጠቅላላ ዋጋ=8,760,000               👍ቅ/ክፍያ(20%) =1,752,000               ✅ሙሉ ለሚከፍል =6,132,000     ➡️: 93 ካሬ               👍ጠቅላላ ዋጋ=11,160,000               👍ቅ/ክፍያ(20%) =2,232,000               ✅ሙሉ ለሚከፍል =7,812,000 🔥ባለ 2 መኝታ:  102 ካሬ               👍ጠቅላላ ዋጋ=12,240,000               👍ቅ/ክፍያ(20%) =2,448,000               ✅ሙሉ ለሚከፍል =8,568,000      ➡️: 112 ካሬ               👍ጠቅላላ ዋጋ=13,450,000               👍ቅ/ክፍያ(20%) =2,688,000               ✅ሙሉ ለሚከፍል =9,408,000 🔥ባለ 3 መኝታ: 134               👍ጠቅላላ ዋጋ=16,080,000               👍ቅ/ክፍያ(20%) =3,216,000              ✅ሙሉ ለሚከፍል=11,256,000 ➡️: 151 ካሬ               👍ጠቅላላ ዋጋ=18,120,000               👍ቅ/ክፍያ(20%) =3,624,000              ✅ሙሉ ለሚከፍል=12,684,000       ➡️: 175ካሬ               👍ጠቅላላ ዋጋ=21,000,000               👍ቅ/ክፍያ(20%) =4,200,000              ✅ሙሉ ለሚከፍል=14,700,000 ➡️ ከ30% በላይ ሲከፍሉ ከ15-20% ቅናሽ እናደርጋለን። 🔑  በ3 ዓመት ውስጥ የሚረከቡት         ⏩ ማሳሰቢያ: ምንም አይነት የዋጋ ጭማሪ አናደርግም! ☎️09-38-04-99-22

photo content

በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን በወረቀት የሚወስዱ ተማሪዎች ወደ መቐለ ዩኒቨርሲቲ ግቢዎች መግባት መጀመራቸውን የዩኒቨርሲቲው ምንጮች አስታውቀዋል። ​ወደ ተመደቡበት ግቢ ለሚገቡት ተፈታ
በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን በወረቀት የሚወስዱ ተማሪዎች ወደ መቐለ ዩኒቨርሲቲ ግቢዎች መግባት መጀመራቸውን የዩኒቨርሲቲው ምንጮች አስታውቀዋል። ​ወደ ተመደቡበት ግቢ ለሚገቡት ተፈታኞች እስከ ነገ ድረስ አቀባበል የሚደረግላቸው ሲሆን፣ ስለ ፈተናው ሂደት አስፈላጊው ገለፃና ማብራሪያ ከተሰጣቸው በኋላ ከሐምሌ 22 እስከ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት ቀናት ውስጥ ፈተናውን እንደሚወስዱ ተገልጿል። ​ሕወሓት ከሳምንታት በፊት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን በራሴ ፈተና አውጥቼ እፈትናለሁ፣ እንዲሁም ዩኒቨርሲቲ እመድባለሁ ሲል የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ተማሪዎቹ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና ለመካፈል ወደ ዩኒቨርሲቲው መግባት ጀምረዋል። ​#ethioradar

የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በጅማ ከተማ በሚገኘው ሔርማታ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ሲሆን፣ ተማሪ ሙአዝ ቢላል የተባለው ተከሳሽ የሚማርበትን ክፍል ሲረብሽ ቆይቶ በመስኮት በኩል ዘሎ ወ
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በጅማ ከተማ በሚገኘው ሔርማታ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ሲሆን፣ ተማሪ ሙአዝ ቢላል የተባለው ተከሳሽ የሚማርበትን ክፍል ሲረብሽ ቆይቶ በመስኮት በኩል ዘሎ ወደ ውጭ ይወጣል። ​ይህን የተመለከተው የክፍሉ አለቃ ተማሪ ሙሳብ መሀመድ ድርጊቱ ትክክል እንዳልሆነ በመንገርና በመቆጣት የተሰጠውን ኃላፊነት ይወጣል። በዚህ ምክንያት በተማሪዎቹ መካከል ግጭት የተፈጠረ ሲሆን፣ "ልትናገረኝ አይገባም" በማለት የተበሳጨው ተማሪ ሙአዝ ቢላል፣ አስቀድሞ ደብቆ ይዞት የገባውን ጩቤ በመመዘዝ የክፍል አለቃውን ተማሪ ሙሳብ መሀመድን በያዘው ስለት ወግቶ ሕይወቱ እንዲያልፍ አድርጓል። ​ወንጀሉን የፈጸመው ተማሪ በፖሊስ በቁጥጥር ሥር ውሎ ምርመራ ሲጣራበት የቆየ ሲሆን፣ ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የጅማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተማሪ ሙአዝ ቢላል ጥፋተኛ መሆኑን በማረጋገጥ በ15 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል። #ethioradar

ፍቅርና ይቅርባይነት ​ዛሬ በሰይፉ ሾው ላይ የቀረበው የሀብታሙ እና የቤተልሔም ታሪክ፣ በብዙዎች ልብ ውስጥ ትልቅ ትምህርት እና ተስፋን ያጫረ እውነተኛ የፍቅር ምስክርነት ሆኖ አልፏል። ​በተለይም ቤ
ፍቅርና ይቅርባይነት ​ዛሬ በሰይፉ ሾው ላይ የቀረበው የሀብታሙ እና የቤተልሔም ታሪክ፣ በብዙዎች ልብ ውስጥ ትልቅ ትምህርት እና ተስፋን ያጫረ እውነተኛ የፍቅር ምስክርነት ሆኖ አልፏል። ​በተለይም ቤተልሔም ልጅ በሚወለድበትና የእናትነትን ፈተና በምትወጣበት ያንን ሁሉ መከራና ስቃይ ብቻዋን አልፋ፣ ዛሬ ላይ በልቧ ምንም ዓይነት ቅሬታ ሳይያዝ ይቅርታን መታደሏ ምን ያህል ታላቅና የሰፋ ደግ ልብ እንዳላት ያሳየበት አጋጣሚ ነበር።«ለዓይን አያሳየኝ» በሚባልበት በዚህ ዘመን፣ እንዲህ ዓይነት አርቆ አሳቢነት፣ አስተዋይነት እና የይቅር ባይነት መንፈስ ማሳየት የእውነተኛ ፍቅር መገለጫ መሆኑ ተገልጿል። ​በሌላ በኩል ሀብታሙ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት በዚያ አስቸጋሪ ወቅት አጠገቧ ባይኖርም፣ ዛሬ ላይ ስህተቱን አምኖ ይቅርታ ለመጠየቅ መደፈሩ እና በቤተልሔም ይቅር ባይነት የተከናወነው እርቅ እውነተኛ ፍቅር በፈተናዎች ውስጥ አልፎ እንደሚጸና አስመስክሯል። ​ለዚህ ውብ አጋጣሚ እና እርቅ መሳካት፣ ሁለት በፍቅር የተሳሰሩ ልቦችን በማገናኘትና ውብ ቤተሰብን መልሶ በመገንባት በኩል ትልቁን አስተዋጽኦ ላደረገው ለሰይፉ ፋንታሁን ከፍተኛ ምስጋናና ክብር ተቸሮታል።​ሁለቱም ጠንክረው፣ እጅ ለእጅ ተያይዘው ልጃቸውን በፍቅርና በደስታ የሚያሳድጉበት መልካም ጊዜ እንዲሆንላቸው አድናቂዎቻቸውና ተከታታዮቻቸው መልካም ምኞታቸውን ገልጸውላቸዋል። #ethioradar

አዲስሳይት 👉Studio 32ካሬ ✅1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ ✅2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና ✅3 መኝታ ከ 112ካሬ ጀምሮ 👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት 👉
አዲስሳይት 👉Studio 32ካሬ ✅1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ ✅2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና ✅3 መኝታ ከ 112ካሬ ጀምሮ 👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት 👉100% ለሚከፍሉ እስከ 35% ቅናሽ 👉4B+4SB+18 የሆነ ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርትመንት 👉 በመገናኛ ጫካ ፕሮጀክት ከቴምር ሪልስቴት 💥 የንግድ ሱቆች ⨳ #ቡልጋሪያ ላይ ከ900ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣ ⨳ #ፒያሳ ላይ ከ1.4ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣ ⨳ #ቃሊቲገላን ላይ ከ500ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ።     #ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ ለበለጠ መረጃ ይደውሉ        👇👇👇👇👇👇 ☎️09-38-04-99-22 ☎️09-90-22-09-02

በሀገራዊ የምክክር መድረክ ላይ የተሳተፉ ንዑሳን ቡድኖች የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ፣ አርማ እና መዝሙር እንዲሁም የክልሎች ምልክቶችን በተመለከተ በርካታ አማራጭ ሃሳቦችን አቅርበዋል። ​በፖለቲካ ፓርቲ
በሀገራዊ የምክክር መድረክ ላይ የተሳተፉ ንዑሳን ቡድኖች የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ፣ አርማ እና መዝሙር እንዲሁም የክልሎች ምልክቶችን በተመለከተ በርካታ አማራጭ ሃሳቦችን አቅርበዋል። ​በፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ተወካይ አቶ ፈይሰል አብዱላዚዝ እንደገለጹት፣ በአረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ቀለማት ላይ አጠቃላይ ስምምነት ቢኖርም በአርማውና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ግን የሚከተሉት ዋና ዋና ሃሳቦች ተነስተዋል፦ ​የአርማ አማራጮች፦ አሁን ያለው የኮከብ አርማ ተነስቶ እንደ አሜሪካ ባንዲራ የሁሉም ብሔረሰቦች አርማ እንዲቀመጥ፣ ወይም የሰላም ምልክት የሆነችው «እርግብ» እንድትሆን፣ አሊያም ሁሉንም ክልሎች ሊወክል የሚችል አዲስ አርማ እንዲዘጋጅ ሀሳብ ቀርቧል። ​የክልል ባንዲራ፦ ከሀገሪቱ አንድ ሰንደቅ ዓላማ ውጭ ሌላ መኖር የለበትም የሚል ሀሳብ የተነሳ ሲሆን፣ ክልሎችም ተመሳሳይ የሶስቱን ቀለማት ባንዲራ በመጠቀም የየራሳቸውን አርማ ብቻ እንዲጨምሩበት ተመክሯል። ​ብሔራዊ መዝሙር፦ የአሁኑ ሀገራዊ መዝሙር እንዲቀጥል እና የክልሎች መዝሙር ደግሞ ይዘቱ «ጠብ አጫሪ» እንዳይሆን መደረግ እንዳለበት ስምምነት ላይ ተደርሷል። ​እነዚህ በንዑሳን ቡድኖች የጸደቁ አጀንዳዎች በመቀጠል 250 አባላት ወዳሉት አጠቃላይ የውይይት ቡድን ተሸጋግረው ተጨማሪ ውይይት እንደሚደረግባቸው ታውቋል። #ethioradar

​በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት (ELMIS) ፕሮጀክት ኃላፊ እና የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ዋና ሥራ ፈጻሚን ጨምሮ በርካታ ከፍተኛ አመራሮች በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር
​በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት (ELMIS) ፕሮጀክት ኃላፊ እና የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ዋና ሥራ ፈጻሚን ጨምሮ በርካታ ከፍተኛ አመራሮች በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ። ​ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት፦ ​📌 በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት እና በ ELMIS ሲስተም ላይ የመረጃ ማጥፋት ወንጀል፤ ​📌 በከባድ ሙስና እና በሕገ-ወጥ የሰው ዝውውር መሳተፍ፤ ​📌 የመንግሥትን የውጭ ምንዛሬ ለግል ጥቅም በማዋል ወንጀሎች ተጠርጥረው መሆኑ ታውቋል። ​በአሁኑ ወቅት በፌደራል ፖሊስ አማካኝነት በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ እና በጥፋቱ ተጠራጣሪዎች ላይ ከፍተኛ የምርመራ ሂደት እየተካሄደ ይገኛል። #ethioradar

​የፌደራል ሲቪል ሠርቪስ ኮሚሽን ሁሉም የሲቪል ሠርቪስ መስሪያ ቤቶች የሠራተኞቻቸውን ማስረጃዎች በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ አረጋግጠው እንዲያጠናቅቁ አሳሰበ። ​ኮሚሽኑ ዛሬ በጉዳዩ ዙሪያ ባካሄደው
​የፌደራል ሲቪል ሠርቪስ ኮሚሽን ሁሉም የሲቪል ሠርቪስ መስሪያ ቤቶች የሠራተኞቻቸውን ማስረጃዎች በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ አረጋግጠው እንዲያጠናቅቁ አሳሰበ። ​ኮሚሽኑ ዛሬ በጉዳዩ ዙሪያ ባካሄደው የውይይት መድረክ ላይ እንዳስታወቀው፤ እስከ አሁን ያሉ "የተሳሳቱ" የመንግሥት ሠራተኞች መረጃዎች መንግሥት አስተማማኝ የሆነ የሠራተኛ መረጃ እንዳይኖረው ማድረጋቸው አልፎ፣ ለትክክለኛ ሠራተኞች ብቻ ደሞዝ የመክፈል ሂደቱን እንቅፋት ሆኖበታል። ​ይህንን አሰራር ሙሉ በሙሉ ዘመናዊና ግልጽ ለማድረግ ሲባል፣ ኮሚሽኑ በዘረጋው አዲስ ዲጂታል ሥርዓት መሠረት ለእያንዳንዱ የመንግሥት ሠራተኛ ልዩ የመለያ ቁጥር የሚሰጥ ይሆናል። ​የሲቪል ሠርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ ማንኛውም የመንግሥት መሥሪያ ቤት የሠራተኞቹን መረጃዎችና ማስረጃዎች በፍጥነት ወደ ዲጂታል ሥርዓት በማስገባት የተቋሙን የመረጃ ጥራት እንዲያረጋግጥ አጥብቀው አሳስበዋል። #ethioradar

አዲስሳይት 👉Studio 32ካሬ ✅1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ ✅2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና ✅3 መኝታ ከ 112ካሬ ጀምሮ 👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት 👉100% ለሚከፍሉ እስከ 35% ቅናሽ 👉4B+4SB+18 የሆነ ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርትመንት 👉 በመገናኛ ጫካ ፕሮጀክት ከቴምር ሪልስቴት 💥 የንግድ ሱቆች ⨳ #ቡልጋሪያ ላይ ከ900ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣ ⨳ #ፒያሳ ላይ ከ1.4ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣ ⨳ #ቃሊቲገላን ላይ ከ500ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ።     #ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ ለበለጠ መረጃ ይደውሉ        👇👇👇👇👇👇 ☎️09-38-04-99-22 ☎️09-90-22-09-02

አንጋፋዋ አርቲስት ከዚህ አለም በሞት ተለይታለች አንጋፋዋ ድምጻዊት፣ የግጥምና ዜማ ደራሲ ሳጅን አልማዝ ተፈራ ባደረባት ሕመም በሕክምና ስትረዳ ቆይታ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት
አንጋፋዋ አርቲስት ከዚህ አለም በሞት ተለይታለች አንጋፋዋ ድምጻዊት፣ የግጥምና ዜማ ደራሲ ሳጅን አልማዝ ተፈራ ባደረባት ሕመም በሕክምና ስትረዳ ቆይታ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች። ​የሕይወት ታሪክ እና የሙዚቃ ጉዞ፦ ድምጻዊት አልማዝ ተፈራ በነገሌ ቦረና ተወልዳ ያደገች ሲሆን፣ ትምህርቷን በይርጋለም ከተማ ተከታትላለች። በመቀጠልም በጅማ ፖሊስ ኦኬስትራ ባንድ ከምስረታው ጀምሮ ለበርካታ ዓመታት በድምጻዊነት፣ በግጥምና ዜማ ደራሲነት እንዲሁም በጃዝ ሙዚቃ ተጫዋችነት ከፍተኛ አገልግሎት አበርክታለች። ​በሙዚቃ ዘመኗ ሶስት አልበሞችን ለአድማጭ ያደረሰች ሲሆን፦ ​የመጀመሪያ አልበም (1978 ዓ.ም)፦ በጅማው መንዝ ሙዚቃ ቤት የታተመና ‘ጅማ ላይ ነው ቤቱ’፣ ‘አካል መውደድ’ እና ‘የፍቅር ጽገሬዳ’ የመሳሰሉ ተወዳጅ ዜማዎችን ያካተተ ነበር። ​ሁለተኛ አልበም (1982 ዓ.ም)፦ በዚሁ መንዝ ሙዚቃ ቤት ታትሞ ለአድማጭ ደርሷል። ​ሦስተኛ አልበም (1993 ዓ.ም)፦ ወደ አዲስ አበባ በመዛወር በፖሊስ ኦኬስትራ ውስጥ ማገልገል በጀመረችበት ወቅት በአፍሪካ ኤሌክትሮኒክስ አሳታሚነት የቀረበ ነው። ​ከራሷ አልበሞችና ነጠላ ዜማዎች በተጨማሪ፣ በድርሰት ብቃቷ ለሌሎች ድምጻውያንም ተወዳጅ ሥራዎችን አበርክታለች። ከእነዚህም መካከል የአንጋፋዋ ድምጻዊት ሒሩት በቀለን ‘እንደ ንጋት ጮራ’፣ ‘የባቄላ አበባ’ እና ‘ቃልኪዳን አክባሪ’ የተሰኙ ዘፈኖችን ግጥምና ዜማ ደርሳለች። ​የሁለት ሴት ልጆች እናት የነበረችው የአርቲስት ሳጅን አልማዝ ተፈራ ሥርዓተ ቀብር፣ ዛሬ ቀን 10:00 ሰዓት ላይ በቅዱስ ዮሴፍ መካነ መቃብር እንደሚፈጸም ከቤተሰቦቿ የተገኘው መረጃ ያመላክታል። #ethioradar

አስቸኳይ የአፋልጉኝ ጥሪ ❗️❗️❗️ በጀሞ 3 የ11 ዓመት ህፃን በጎርፍ ተወሰደ! ሼር❗️ ሼር ❗️
አስቸኳይ የአፋልጉኝ ጥሪ ❗️❗️❗️ በጀሞ 3 የ11 ዓመት ህፃን በጎርፍ ተወሰደ! ሼር❗️ ሼር ❗️

ኢትዮቴሌኮም ስጦታ አበርክቷል የሀገራችን የቴሌኮም ግዙፍ ተቋም የሆነው ኢትዮ ቴሌኮም በያዝነው በጀት ዓመት 215.8 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን አበሰረ። ተቋሙ ያስመዘገበውን ከፍተኛ የገቢ እድገት
ኢትዮቴሌኮም ስጦታ አበርክቷል የሀገራችን የቴሌኮም ግዙፍ ተቋም የሆነው ኢትዮ ቴሌኮም በያዝነው በጀት ዓመት 215.8 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን አበሰረ። ተቋሙ ያስመዘገበውን ከፍተኛ የገቢ እድገት እና ትርፋማነት አስመልክቶ፣ የስኬቱ ዋና አካል ለሆኑት ከ90 ሚሊዮን በላይ ደንበኞቹ ነፃ የስጦታ ፓኬጅ ማዘጋጀቱን ገልጿል። ​የተዘጋጀው የቴሌ ስጦታ፦ ​📌 1.5 ጊጋ ባይት (GB) የኢንተርኔት ዳታ፤ ​📌 15 ደቂቃ የሀገር ውስጥ ጥሪ፤ ​📌 30 የጽሑፍ መልዕክቶች (SMS) ናቸው። ​የስጦታው መጠቀሚያ ጊዜ እና ደንብ፦የሚቆይበት ቀን፦ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሐምሌ 19/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ፤ ​የአገልግሎት ሰዓት፦ በየቀኑ ከሌሊቱ 6:00 እስከ ምሽቱ 12:00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ አገልግሎት ላይ የሚውል ይሆናል። #ethioradar

እገዳ ተጥሏል ❗️ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሀገሪቱ ውስጥ ያለ ሕጋዊ ፈቃድ የሚካሄዱ የዲጂታል እና ምናባዊ ንብረት (Virtual Assets) ግብይቶች ላይ የማይቀናጅ ጥብቅ እገዳ መጣሉን ይፋ አደ
እገዳ ተጥሏል ❗️ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሀገሪቱ ውስጥ ያለ ሕጋዊ ፈቃድ የሚካሄዱ የዲጂታል እና ምናባዊ ንብረት (Virtual Assets) ግብይቶች ላይ የማይቀናጅ ጥብቅ እገዳ መጣሉን ይፋ አደረገ። ባንኩ ባወጣው ድንገተኛ መግለጫ፣ ክልከላው የዲጂታል ገንዘብ ልውውጦችን ብቻ ሳይሆን ማንኛውንም ዓይነት የምናባዊ ንብረት ሽያጭ፣ ዝውውር እና ተያያዥ የፋይናንስ አገልግሎቶችን የሚያጠቃልል መሆኑን አስታውቋል።​ባንኩ አክሎም እነዚህ ያልተፈቀዱ የዲጂታል ግብይቶች የዜጎችን ሀብት ለከፍተኛ የገንዘብ ማጭበርበር እና ለሳይበር መጠለፍ አደጋ የሚያጋልጡ በመሆናቸው፣ በእንቅስቃሴው ላይ የተሰማሩ አካላት ድርጊታቸውን በአስቸኳይ እንዲያቆሙና ከሕገ-ወጥ ድርጊታቸው እንዲታቀቡ ማሳሰቢያ ሰጥቷል። ​ለመሆኑ "ምናባዊ ንብረት" የሚባሉት የትኞቹ ናቸው? ምናባዊ ንብረት (Virtual Asset) ማለት በአካል የማይጨበጡ፣ ነገር ግን በኢንተርኔትና በኮምፒውተር ቴክኖሎጂ አማካኝነት ከፍተኛ የገንዘብ እሴት ተሰጥቷቸው የሚገበያዩባቸው የዲጂታል ሀብቶች ናቸው።​ከእነዚህም መካከል፦ ​ክሪፕቶከረንሲዎች፦ እንደ ቢትኮይን (Bitcoin)፣ ኢቴሪየም (Ethereum) እና ቴዘር (USDT) ያሉ ታዋቂ የዲጂታል ገንዘብ አይነቶች ​ዲጂታል ቶከኖች (NFTs)፦ በዲጂታል መድረክ የተዘጋጁ የኪነ-ጥበብ፣ የሙዚቃ ወይም የንብረት ባለቤትነት ማረጋገጫዎች ዋና ዋናዎቹ ናቸው። #ethioradar

ትራምፕ ታዋቂውን የዓለም ዋንጫ አዘጋጅ የፊፋ መሪ ለተመድ ዋና ጸሐፊነት ይፈልጋሉ ተባለ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የፊፋውን ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖን ቀጣዩ የተባበሩት መንግሥታት ድር
ትራምፕ ታዋቂውን የዓለም ዋንጫ አዘጋጅ የፊፋ መሪ ለተመድ ዋና ጸሐፊነት ይፈልጋሉ ተባለ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የፊፋውን ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖን ቀጣዩ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሐፊ አድርገው የመሾም ፍላጎት እንዳላቸው ለፕሬዝዳንቱ ቅርብ የሆኑ ምንጮችን ዋቢ በማድረግ ዘገባዎች አመላክተዋል። ​እንደ ምንጮቹ ገለጻ ከሆነ፤ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኢንፋንቲኖ "በመላው ዓለም የሚገኙ አካላት የሚያከብሯቸው እና ሰዎችን በአንድ ላይ የማምጣት ልዩ ብቃት ያላቸው አዛዥ ሰው ናቸው" በሚል አቋም ይዘዋል። ​ኢንፋንቲኖ ከዶናልድ ትራምፕ ጋር በዓለም ዋንጫ አዘጋጅነት እና በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ ጥብቅ ቁርኝት የፈጠሩ ቢሆንም፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) ዋና ጸሐፊን የመምረጥ ሂደት ግን የራሱ የሆነ ጥብቅ የሕግ ሥነ-ሥርዓት አለው። ​በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቻርተር መሠረት፣ ዋና ጸሐፊው የሚሾመው በጸጥታው ምክር ቤት አቀራረብነት በጠቅላላ ጉባኤው ውሳኔ ነው። ይህም ማለት ማንኛውም ዕጩ የጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ አባላትን (ቻይናን እና ሩሲያን ጨምሮ) ድጋፍ ማግኘት ይኖርበታል። ​ይህ በዲፕሎማሲው ዓለም ትልቅ የመነጋገሪያ ርዕስ የሆነው ዘገባ ቢወጣም፣ የኢንፋንቲኖ ዋና ትኩረት አሁንም ቢሆን የፊፋን አጠቃላይ እንቅስቃሴዎችን እና የዓለም ዋንጫ ውድድርን በበላይነት መምራት ላይ እንደሆነ ይታመናል። #ethioradar

የጀነራሉ መሠወር አዲስ ስጋት ቀስቅሷል ​የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዝዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ በመቀሌ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው መሰወራቸው ተሰማ።እስከ ማክሰኞ ጠዋት
የጀነራሉ መሠወር አዲስ ስጋት ቀስቅሷል ​የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዝዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ በመቀሌ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው መሰወራቸው ተሰማ።እስከ ማክሰኞ ጠዋት ድረስ መኖሪያ ቤታቸውን በጥበቃ ተሽከርካሪዎች ከበበው የነበሩ ጥበቃዎችና ሰራተኞች ከምሽቱ ጀምሮ ከአካባቢው ሙሉ በሙሉ ጠፍተዋል። ​ጄነራሉ ከቀናት በፊት ከአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ጋር እንዳይገናኙ በትግራይ ጸጥታ ቢሮ ተከልክለው እንደነበርና ቤተሰቦቻቸውም ስለ ደህንነታቸው ስጋት አድሮባቸው እንደነበር ይታወቃል። በፌደራል መንግሥት ከተሾሙ በኋላ በሕወሓት ከኃላፊነታቸው የተነሱት ጄነራሉ፤ ከድርጊቱ በፊት ጊዜያዊ አስተዳደሩን በኃይል ለመገልበጥ የሚደረግ ሙከራ ክልሉን ወደ አዲስ ጦርነት እንደሚያስገባ አስጠንቅቀው ነበር። ​በሕወሓት እና በፌደራል መንግሥት መካከል የፖለቲካ ውጥረት በነገሰበት በዚህ ወቅት፣ የጄነራሉ ከአካባቢው መሰወር በክልሉ አዲስ የጸጥታ ስጋት ፈጥሯል ተብሏል።

አዲስሳይት 👉Studio 32ካሬ ✅1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ ✅2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና ✅3 መኝታ ከ 112ካሬ ጀምሮ 👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት 👉
አዲስሳይት 👉Studio 32ካሬ ✅1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ ✅2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና ✅3 መኝታ ከ 112ካሬ ጀምሮ 👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት 👉100% ለሚከፍሉ እስከ 35% ቅናሽ 👉4B+4SB+18 የሆነ ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርትመንት 👉 በመገናኛ ጫካ ፕሮጀክት ከቴምር ሪልስቴት 💥 የንግድ ሱቆች ⨳ #ቡልጋሪያ ላይ ከ900ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣ ⨳ #ፒያሳ ላይ ከ1.4ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣ ⨳ #ቃሊቲገላን ላይ ከ500ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ።     #ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ ለበለጠ መረጃ ይደውሉ        👇👇👇👇👇👇 ☎️09-38-04-99-22 ☎️09-90-22-09-02

ሱዳን በሃይል አቅርቦት ዙሪያ ኢትዮጵያን ተጠያቂ አደረገች ሱዳን በአንዳንድ አካባቢዎች በቀን እስከ 18 ሰዓታት የደረሰ የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ያጋጠማት በክረምቱ የፍላጎት መጨመር፣ የጥገና ሥራዎች፣
ሱዳን በሃይል አቅርቦት ዙሪያ ኢትዮጵያን ተጠያቂ አደረገች ሱዳን በአንዳንድ አካባቢዎች በቀን እስከ 18 ሰዓታት የደረሰ የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ያጋጠማት በክረምቱ የፍላጎት መጨመር፣ የጥገና ሥራዎች፣ የመሰረተ ልማት ውድመቶች እና ከኢትዮጵያ ይገባ የነበረው የኃይል አቅርቦት በመቋረጡ ምክንያት እንደሆነ የሀገሪቱ የኢነርጂ እና ነዳጅ ሚኒስቴር አስታውቋል። ሚኒስቴሩ ጉዳት የደረሰባቸውን መስመሮች በመጠገን የኃይል አቅሙን ዳግም ለመመለስ እየሰራ ቢሆንም ሂደቱ እስኪጠናቀቅ የመቆራረጡ ችግር እንደሚቀጥል ገልጿል። ​ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የድንበር ተሻጋሪ የኤሌክትሪክ ንግድ መሰረተ ልማት ማጠናቀቋን ብታስታውቅም፣ ከሱዳን ጋር ያለው የኃይል አቅርቦት መቋረጡ ተሰምቷል። ሱዳን ላለፉት ሦስት ዓመታት የኤሌክትሪክ ክፍያ ባለመክፈሏ ከ90 ሚሊዮን ዶላር በላይ ዕዳ ያለባት ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጦርነት ለተጎዳችው ሱዳን አቅርቦቱን ለመቀጠል ፍላጎት እንደነበረው ይታወቃል። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የኤሌክትሪክ ኤክስፖርቷን ወደ ኬንያ፣ ጂቡቲ እና ታንዛኒያ በማስፋፋት ላይ ትገኛለች። #ethioradar

የሬድዮ ጣቢያው ለስድስት ወራት ታገደ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የጄኤፍኤም (JFM 106.7) ሬድዮ ጣቢያ የብሮድካስት ስርጭት ከሐምሌ 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት ሙ
የሬድዮ ጣቢያው ለስድስት ወራት ታገደ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የጄኤፍኤም (JFM 106.7) ሬድዮ ጣቢያ የብሮድካስት ስርጭት ከሐምሌ 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት ሙሉ ለሙሉ እንዲታገድ መወሰኑን አስታወቀ። ​ባለሥልጣኑ ውሳኔውን ያስ አስተላለፈው ጣቢያው በተደጋጋሚ የተሰጡትን የቃልና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያዎች ሳይቀበል በመቅረቱ እና በአዋጅ ቁጥር 1238/2013 የተጣሉበትን የፈቃድ ውል ግዴታዎች ባለመወጣቱ እንደሆነ ገልጿል። ​የእግዱ ዋና ዋና ምክንያቶች፦ ​ባለሥልጣኑ ባደረገው የይዘት ክትትልና የአካል ኢንስፔክሽን ምልከታ መሠረት ጣቢያው የሚከተሉትን ጥሰቶች መፈጸሙ ተረጋግጧል፦ ​በሕግ የተጣለበትን የሀገራዊ ይዘት ሽፋን አለማካተት፤​ሕዝብን የሚያስተምሩና የሚያዝናኑ ፕሮግራሞችን ከማቅረብ መቆጠብ፤​ለሀገራዊ እሴቶችና ለፖለቲካዊ-ኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋጽኦ የማድረግ ግዴታን አለመወጣት። ​በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ ኮሚዩኒኬሽን ባለሥልጣን ጣቢያው የተመደበለትን 106.7 የሬድዮ ሞገድ በእግዱ ወቅት እንዳይጠቀም ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን፣ ጣቢያው ለሕግ ተገዢ በመሆን ስርጭቱን በአስቸኳይ እንዲያቆም ታዟል። #ethioradar

አዲስሳይት 👉Studio 32ካሬ ✅1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ ✅2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና ✅3 መኝታ ከ 112ካሬ ጀምሮ 👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት 👉
አዲስሳይት 👉Studio 32ካሬ ✅1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ ✅2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና ✅3 መኝታ ከ 112ካሬ ጀምሮ 👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት 👉100% ለሚከፍሉ እስከ 35% ቅናሽ 👉4B+4SB+18 የሆነ ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርትመንት 👉 በመገናኛ ጫካ ፕሮጀክት ከቴምር ሪልስቴት 💥 የንግድ ሱቆች ⨳ #ቡልጋሪያ ላይ ከ900ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣ ⨳ #ፒያሳ ላይ ከ1.4ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣ ⨳ #ቃሊቲገላን ላይ ከ500ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ።     #ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ ለበለጠ መረጃ ይደውሉ        👇👇👇👇👇👇 ☎️09-38-04-99-22 ☎️09-90-22-09-02