es
Feedback
Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር

Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር

Ir al canal en Telegram

Welcome to Ethio Radar, a professional news analysis platform brought to you by a dedicated team of experienced journalist. stay informed,stay on radar! እንኳን ወደ ኢትዮ ራዳር ቻናል መጡ,ሀሳብ፣አስተያየት፣ መረጃ ለማጋራት ማስታወቂያ ለማሰራት በ @Ethioradarr01 ያናግሩን

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር

El canal Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር (@ethioradarinfo) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 53 495 suscriptores, ocupando la posición 184 en la categoría Marketing y relaciones públicas y el puesto 606 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 53 495 suscriptores.

Según los últimos datos del 26 agosto, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -3 463, y en las últimas 24 horas de -82, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 2.05%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 0.75% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 1 095 visualizaciones. En el primer día suele acumular 402 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 3.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
Welcome to Ethio Radar, a professional news analysis platform brought to you by a dedicated team of experienced journalist. stay informed,stay on radar! እንኳን ወደ ኢትዮ ራዳር ቻናል መጡ,ሀሳብ፣አስተያየት፣ መረጃ ለማጋራት ማስታወቂያ ለማሰራት በ @Ethioradarr01 ያናግሩን

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 27 agosto, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Marketing y relaciones públicas.

53 495
Suscriptores
-8224 horas
-7617 días
-3 46330 días
Archivo de publicaciones
ዉጤት ማየት ተጀምሯል!! የ 12ኛ ክፍል ዉጤት ማየት ተጀምሯል :: ማየት የምትፈልጉ 🤘 ኔትዎርክ የሚያስችግራችሁ በዚህ ቻናል ገብታችሁ ላኩልን 👍 https://t.me/+_ufqjHYHEIxkOWJk
ዉጤት ማየት ተጀምሯል!! የ 12ኛ ክፍል ዉጤት ማየት ተጀምሯል :: ማየት የምትፈልጉ 🤘 ኔትዎርክ የሚያስችግራችሁ በዚህ ቻናል ገብታችሁ ላኩልን 👍 https://t.me/+_ufqjHYHEIxkOWJk https://t.me/+_ufqjHYHEIxkOWJk ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

የ 12ተኛ ተማሪዎች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸው ማየት ይችላሉ " የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
የ 12ተኛ ተማሪዎች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸው ማየት ይችላሉ " የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡- https://result.eaes.et/complaint - በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et - ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram - አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፤ እንኳን ለ1501 ኛው የነቢዩ መሐመድ የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ኢትዮ ራዳር
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፤ እንኳን ለ1501 ኛው የነቢዩ መሐመድ የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ኢትዮ ራዳር

photo content

አስቃቂ የትራፊክ አደጋ ❗️ በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ በዛሬው ዕለት በደረሰ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት ማለፉን የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ገለጸ። ​ከ
አስቃቂ የትራፊክ አደጋ ❗️ በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ በዛሬው ዕለት በደረሰ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት ማለፉን የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ገለጸ። ​ከዚሁ አደጋ ጋር ተያይዞ የወጡ ዋና ዋና መረጃዎች፦ ​📌 የአደጋው ቦታና ሰዓት፦ አደጋው በዛሬው ዕለት ጠዋት 1 ሰዓት ከ50 ገደማ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ልዩ ቦታው ቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን አካባቢ የተከሰተ ነው። ​📌 አደጋው እንዴት ደረሰ፦ ከኮዬ ፈቼ ወደ ጎሮ በመጓዝ ላይ የነበረ ሚኒባስ ታክሲ በተጠቀሰው አካባቢ ሲደርስ፣ በመንገድ ሥራ ላይ የነበረ የስካቫተር ማሽን መቆፈሪያ አካል በታክሲው ላይ በመውደቁ ምክንያት አደጋው ሊከሰት ችሏል። ​📌 የጉዳቱ መጠን፦ በታክሲው ውስጥ ከነበሩት ተራንስፖርት ተጠቃሚዎች መካከል የ6ቱ ህይወት በቦታው ሲያልፍ፣ ሌሎች ተሳፋሪዎች ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በአሁኑ ወቅት የሕክምና ክትትል በማድረግ ላይ ይገኛሉ። ​የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ የአደጋውን መንስኤ በዝርዝር እያጣራ እንደሚገኝ አስታውቋል። @ethioradarinfo

ውጤት እንዴት መመልከት ይቻላል ? የ2018ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ዉጤት ስለቀቅ በሚከተሉት አማራጮች ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ። በዌብ ሳይት 👉 https://eaes.edu.et/ ወይም 👉 h
+1
ውጤት እንዴት መመልከት ይቻላል ? የ2018ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ዉጤት ስለቀቅ በሚከተሉት አማራጮች ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ። በዌብ ሳይት 👉 https://eaes.edu.et/ ወይም 👉 https://result.neaea.gov.et 👉 https://result.eaes.et በአጭር የጽሑፍ መልዕክት 6284 በቴሌግራም https://t.me/eaesbot @Freshmerejaet @Freshmerejaet

ዓመተ ምሕረት (ዓ.ም)» የሚለው የዘመን አቆጣጠር ተቀይሮ «የኢትዮጵያ አቆጣጠር (ኢ.አ)» በሚል እንዲተካ ለ4 ሺሕ ጉባኤተኞች በተነበበውና በኮሚሽኑ በተረከበው የምክረ ሀሳብ ሰነድ ላይ ስምምነት መ
ዓመተ ምሕረት (ዓ.ም)» የሚለው የዘመን አቆጣጠር ተቀይሮ «የኢትዮጵያ አቆጣጠር (ኢ.አ)» በሚል እንዲተካ ለ4 ሺሕ ጉባኤተኞች በተነበበውና በኮሚሽኑ በተረከበው የምክረ ሀሳብ ሰነድ ላይ ስምምነት መደረሱ ተገለጸ። በተጨማሪም የሒጅራ ዘመን አቆጣጠር እንደ ካላንደር እንዲካተት ሀሳብ መያዙ ተጠቅሷል። @ethioradarinfo

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ይፋ ይደረጋል። ትምህርት ሚኒስቴር በላከልን መረጃ የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል የሀገር አቀፍ ፈተና ውጤትን በተመለከተ ከሰዓት በኋላ መግለጫ እንደሚሰጥ ጠቅሷል
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ይፋ ይደረጋል። ትምህርት ሚኒስቴር በላከልን መረጃ የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል የሀገር አቀፍ ፈተና ውጤትን በተመለከተ ከሰዓት በኋላ መግለጫ እንደሚሰጥ ጠቅሷል። በዓመቱ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 62 በመቶ የሚሆኑት በኦንላይን ፈተናውን ወስደዋል። በ2018 የትምህርት ዘመን አጠቃላይ 563 ሺህ 501 ተማሪዎች በ607 የፈተና ማዕከላት ውስጥ የተፈተኑ ሲሆን ፈተናው በ6 ዙሮች ተሰጥቷል። ከዘንድሮ ጠቅላላ ተፈታኞች መካከል 306 ሺህ 456 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ሲሆኑ፣ 257 ሺህ 45 ደግሞ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ነበሩ፡፡ ውጤቱን በተመለከትም ትምህርት ሚኒስቴር በ9 ሰዓት መግለጫ እሰጣለሁ ብሏል፡፡ @Seledadotio @Seledadotio

የአፋልጉኝ ተማጽኖ #Ethiopia | “ከአባቴ ጋር ወደ አዲስ አበባ እሄዳለሁ” ብላ ከቤቷ ወጣች ስም፡ ሆናልያት ዮናስ ዋሲሁን እድሜ፡ 12 ዓመት አድራሻ፡ አዳማ ከተማ ገንደ ሐራ፣ ቦሌ ክፍለ ከተማ
+1
የአፋልጉኝ ተማጽኖ #Ethiopia | “ከአባቴ ጋር ወደ አዲስ አበባ እሄዳለሁ” ብላ ከቤቷ ወጣች ስም፡ ሆናልያት ዮናስ ዋሲሁን እድሜ፡ 12 ዓመት አድራሻ፡ አዳማ ከተማ ገንደ ሐራ፣ ቦሌ ክፍለ ከተማ ሆናልያት ዛሬ ጠዋት 1፡00 ሰዓት ላይ፣ “ከአባቴ ጋር ወደ አዲስ አበባ እሄዳለሁ” ብላ ከቤቷ ከወጣች በኋላ እስካሁን ልናገኛት አልቻልንም። ሆናልያትን ያያችሁ ወይም ስለእሷ መረጃ ያላችሁ ሰዎች እባካችሁ ወደሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች ይደውሉ፦ አዳማ የቦሌ ክፍለ ከተማ ፓሊስ መምሪያ አመልክተናል 📞 +251 910 276 304 📞 +251 932 260 525 📞 +251 913 867 421 🙏 እባካችሁ ለማግኘት እንዲረዳ ፖስቱን በሰፊው ሼር ያድርጉት! 🙏

የ11ኛ ክፍል ተማሪዎች ❗️❗️ ​የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የ11ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለሥራው ዓለም የሚያዘጋጅ አዲስ የአተገባበር ማንዋል ይፋ ማድረጉን አስታወቀ። ​ይህ አዲስ መመሪያ ተማሪዎች ትም
የ11ኛ ክፍል ተማሪዎች ❗️❗️ ​የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የ11ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለሥራው ዓለም የሚያዘጋጅ አዲስ የአተገባበር ማንዋል ይፋ ማድረጉን አስታወቀ። ​ይህ አዲስ መመሪያ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁ የራሳቸውን ሥራ መፍጠር እንዲችሉና የ21ኛ ክፍለ ዘመን ክህሎት እንዲጨብጡ ለማስቻል ያለመ ሲሆን፤ በውስጡ የያዛቸው ዋና ዋና ነጥቦች እንደሚከተለው ተብራርተዋል፦ ​📌 11 አዳዲስ የሙያ ዓይነቶች፦ በግንባታ፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ቢዝነስ፣ IT፣ ግብርና እና ጤና ሳይንስ ዘርፎች ተዘጋጅተው ለተማሪዎች እንዲቀርቡ ተደርጓል። ​📌 የተማሪዎች ምርጫ፦ ማንኛውም ተማሪ ከአቅሙና ከፍላጎቱ ጋር የሚሄድ አንድ የሙያ ዓይነት ብቻ መርጦ የሚማር ይሆናል። ​📌 የትምህርት ቤቶች አተገባበር፦ ትምህርት ቤቶች ሁሉንም 11 ሙያዎች በአንድ ጊዜ እንዲያስተምሩ አይገደዱም፤ ይልቁንም እንደ አቅማቸውና እንደ አካባቢው ሁኔታ ተስማሚ የሆኑትን መርጠው እንዲተገብሩ ተፈቅዶላቸዋል። @ethioradarinfo

በአደጋው የሰዎች ሕይወት ሊያልፍ ችሏል በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ዳሌ ወረዳ አካባቢ ነሐሴ 9 ቀን ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ገደማ በደረሰ ከባድ የትራፊክ አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ፣ በ4 ሰዎች ላይ
በአደጋው የሰዎች ሕይወት ሊያልፍ ችሏል በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ዳሌ ወረዳ አካባቢ ነሐሴ 9 ቀን ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ገደማ በደረሰ ከባድ የትራፊክ አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ፣ በ4 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል። አደጋው ከሐዋሳ ወደ ዓለታ ወንዶ በሚጓዝ የዶልፊን ተሽከርካሪ እና በተቃራኒ አቅጣጫ በሚጓዝ የኤፍኤስአር መኪና መካከል በተፈጠረ መጋጨት የተነሳ መንገድ ዘግተው በቆሙ ሌሎች ተሽከርካሪዎች ላይ አንድ የሲኖትራክ መኪና ተደርቦ በመጋጨቱ የተከሰተ ሲሆን፣ በአጠቃላይ በ11 ተሽከርካሪዎች ላይ ከፍተኛ የንብረት ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል። @ethioradarinfo

4 ኪሎ ወርቅ ተያዘ❗️ ከዱባይ ወደ አዲስ አበባ የተጓዘ አንድ ግለሰብ በህገ-ወጥ መንገድ ሊያሳልፈው የነበረ 4 ኪሎ ግራም ጥፍጥፍ ወርቅ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅርንጫ
4 ኪሎ ወርቅ ተያዘ❗️ ከዱባይ ወደ አዲስ አበባ የተጓዘ አንድ ግለሰብ በህገ-ወጥ መንገድ ሊያሳልፈው የነበረ 4 ኪሎ ግራም ጥፍጥፍ ወርቅ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ። ተጠርጣሪው ከፍተኛ ዋጋ ያለውን ይህን ወርቅ በለበሰው ውስጥ ሱሪ ውስጥ በመሸሸግ ለማሳለፍ ሲሞክር በኤርፖርቱ ጉምሩክ ሰራተኞች በተደረገበት ጥብቅ አካላዊ ፍተሻ እጅ ከፍንጅ ሊያዝ ችሏል። በአሁኑ ወቅት ግለሰቡ በህግ ጥላ ስር ውሎ የምርመራ ስራዎች እየተከናወኑበት የሚገኝ ሲሆን፣ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮንትሮባንድን በመግታት ረገድ ላበረከቱት አስተዋፅኦ ለኤርፖርቱ ሰራተኞች እና አመራሮች ምስጋና ማቅረቡን ሀገሬ ቲቪ ዘግቧል። @ethioradarinfo

💵የገንዘብ የመግዛት አቅም 21.05% በየአመቱ እየቀነሰ ገንዘቦትን ባንክ ማስቀመጥ ኪሳራ ነው።💵 ታዲያ ‼️6 ሳይቶችን ሰርተን አስረክበን አሁን ደግሞ (ያለምንም ወለድ እና inflation ) በተዋዋሉበት ብቻ የሚከፍሉትን ሳይት ይዘንሎ መተናል‼️ ከቤተመንግስት አቅራቢያ 📍(አዋሬ) ባለ 3 መኝታ (ከ121ካሬ -157 ካሬ) ከ121ካሬ ጀምሮ ሙሉ ለሚከፍሉ 8,415,000ብር ረጋ ብለው ለሚከፍሉ-12,947,000 ቅድመ ክፍያ-2,589,400(20%)              እስከ 157 ካሬ ሙሉ ለሚከፍሉ-10,919,000 ረጋ ብለው ለሚከፍሉ  -16,799,000 ቅድመ ክፍያ-3,359,000 ብር     📍በቡልጋሪያ (68ካሬ -142ካሬ)       ባለ 1መኝታ ከ68 ካሬ ጀምሮ ሙሉ ለሚከፍል-5,474,000ብር ረጋብለው ለሚከፍሉ-7,820,000 ቅድመ ክፍያ-1,564,000 ብር ባለ 2 መኝታ ከ87 ካሬ ጀምሮ ሙሉ ለሚከፍሉ-7,003,500ብር ረጋ ብለው ለሚከፍሉ-10,350,000 ቅድመ ክፍያ-2,000,000 ብር ባለ3 መኝታ ከ121 ካሬ ጀምሮ ሙሉለሚከፍሉ-9,740,000ብር ረጋ ብለው-13,915,000ብር ቅድመ ክፍያ-2,783,000ብር 📍በሀያት 49 ባለ 3 መኝታ 146&180 ካሬ 📍በፒያሳ ባለ3 መኝታ 136&142 ካሬ ✂️የንግድ ሱቅ 📍በፒያሳ አጠቃላይ ክፍያ-4,800,000 በቅድመ ክፍያ-1,400,000 📍በቡልጋሪያ አጠቃላይ ክፍያ-3,900,000 ቅድመ ክፍያ-900,000 📍በገላን ሙሉ ክፍያ-2,500,000 ቅድመ ክፍያ-500,000 ለበለጠ መረጃ            ☎️ +251938049922                Telegram @yovma

photo content

ወጣቱ ተፅእኖ ፈጣሪ ቲክቶከር አዋርድ ማሸነፍ ችሏል በዲጂታል ሚዲያና በማህበራዊ ዘርፍ በወጣቶች ዘንድ አዎንታዊ ተፅዕኖ ሲፈጥር የቆየው አዶናይ በርሃነ ሀይለሚካኤል፣ በካናዳ በሚዘጋጀው ስመ-ጥር ዓለ
ወጣቱ ተፅእኖ ፈጣሪ ቲክቶከር አዋርድ ማሸነፍ ችሏል በዲጂታል ሚዲያና በማህበራዊ ዘርፍ በወጣቶች ዘንድ አዎንታዊ ተፅዕኖ ሲፈጥር የቆየው አዶናይ በርሃነ ሀይለሚካኤል፣ በካናዳ በሚዘጋጀው ስመ-ጥር ዓለም አቀፍ የ2026 «ቢኪላ አዋርድ» (Bikila Award) የዓመቱ «Youth Impact Award» አሸናፊ በመሆን ስሙ ይፋ ተደርጓል። ​ከዚህ ቀደም እንደ አርቲስት ቴዲ አፍሮ ያሉ ግዙፍ የሀገራችን ባለሙያዎች የተቀበሉትን ይህንን የክብር ሽልማት አዶናይ መረከቡ፣ በዲጂታል ሚዲያው ዘርፍ ላሳየው የላቀ እንቅስቃሴ የተሰጠው ትልቅ ዕውቅና ተደርጎ ተወስዷል። ​በዘንድሮው የቢኪላ አዋርድ ዙሪያ የወጡ ዋና ዋና መረጃዎች፦ ​📌 የስነ-ስርዓቱ ዝርዝር፦ የሽልማት ስነ-ስርዓቱ በቶሮንቶ ካናዳ «Daniels Spectrum» አዳራሽ፣ ቅዳሜ Sep 26, 2026 ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ይካሄዳል። የካናዳ ፓርላማ አባል ክብርት ዶሊ Begum በዋና ተናጋሪነት እንዲሁም አንጋፋው የቴክኖሎጂ ባለሙያ ሳምሶን ደሚሴ ተፈራ በዋና አቅራቢነት ይመሩታል። ​📌 ሌሎች የክብር ተሸላሚዎች፦ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ (ከሞት በኋላ)፦ ለአፍሪካ ጥበብና ባህል ላበረከቱት አስተዋጽኦ ​አቶ ሳሙኤል ታፈሰ (የሳንሻይን ኢንቨስትመንት ግሩፕ መሥራች)፦ የሕይወት ዘመን ዕውቅና ​አና ጌታነህ (የ African Mosaique መሥራች)፦ የሙያ ብቃት ዕውቅና ​ዶክተር ምህረት ደበበ፣ ገዛሁ በቀለ፣ አብነት ታደለ እና በ GTA የሚኖሩ የኢትዮጵያውያን ማህበረሰብ በተለያዩ ዘርፎች የላቀ ዕውቅና አግኝተዋል። ​📌 የትምህርት ብቃት አሸናፊዎች፦ ቢኤምነት አስፋው፣ ኦሊያድ ሩንዳሳ፣ ናትናኤል ተሾመ፣ ኤደን በላይ እና ዮምኒ መኮንን የዘንድሮው የትምህርት ብቃት አሸናፊዎች ሆነዋል። @ethioradarinfo

ፊንቴክ ❗️ በፊንቴክ ኢንቨስትመንት ሽፋን በተፈጸመ ማጭበርበር የተጠረጠሩት አርቲስቶችና ቲክቶከሮች ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ ፍርድ ቤቱ ሙሉ በሙሉ ውድቅ ማድረጉ ተሰማ። ​የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤ
ፊንቴክ ❗️ በፊንቴክ ኢንቨስትመንት ሽፋን በተፈጸመ ማጭበርበር የተጠረጠሩት አርቲስቶችና ቲክቶከሮች ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ ፍርድ ቤቱ ሙሉ በሙሉ ውድቅ ማድረጉ ተሰማ። ​የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት በዋሉት ችሎት የሰጣቸው ውሳኔዎችና ያከናወናቸው አሰራሮች እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፦ ​📌 የመቃወሚያው ውድቅ መደረግ፦ ተከሳሾች "የሠራነው የማስታወቂያ ሥራ እንጂ የኮምፒውተር ማጭበርበር ወንጀል አልፈጸምንም" ሲሉ ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ውድቅ አድርጎታል። ​📌 የዐቃቤ ሕግ አቤቱታ፦ ተከሳሾቹ "እግረኛው" በተሰኘ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ ላይ መግለጫ መስጠታቸውን ተከትሎ፣ ድርጊቱ በፍትሕ ሂደቱ ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል በሚል ዐቃቤ ሕግ ባለ 5 ገጽ አቤቱታ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል። ​📌 የችሎቱ ተለዋጭ ቀጠሮ፦ ፍርድ ቤቱ የቀረበውን አቤቱታና ጉዳዩን ለማጣራት ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ እና ጠበቃ አበባው አበበ በችሎት ተገኝተው የእምነት ክህደት ቃላቸውን እንዲሰጡ ለጥቅምት 02 ቀን 2019 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። @ethioradarinfo

ሴኔጋልን ጨምሮ የ30 የአፍሪካ ሀገራት ዜጎች ለንግድና ለጉብኝት (B1 እና B2) ወደ አሜሪካ ለመጓዝ የቪዛ ማመልከቻ በሚያስገቡበት ወቅት እስከ 20 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የዋስትና ማስያዣ እንዲከፍሉ
ሴኔጋልን ጨምሮ የ30 የአፍሪካ ሀገራት ዜጎች ለንግድና ለጉብኝት (B1 እና B2) ወደ አሜሪካ ለመጓዝ የቪዛ ማመልከቻ በሚያስገቡበት ወቅት እስከ 20 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የዋስትና ማስያዣ እንዲከፍሉ የሚያስገድድ አዲስ መመሪያ ተጣለ። ​የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ይህ አሰራር የቪዛ ጊዜያቸውን አጠናቀው በህገ-ወጥ መንገድ የሚቀሩ ሰዎችን ቁጥር ለመቀነስ ያለመ ነው ሲል የገለጸ ሲሆን፤ በአንጻሩ የስደተኞች እና የጉዞ መብት ተሟጋቾች ውሳኔው ህጋዊ ተጓዦችን በማስደንግጥና ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና በመፍጠር ህጋዊ የሆኑ ጉዞዎችን የሚያስቀር ነው ሲሉ ተችተውታል። @ethioradarinfo

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙሉ የራስ-ገዝነት (Autonomy) መብቱን ተግባራዊ ለማድረግ ባካሄደው አዲስ የመዋቅር ማስተካከያ ምክንያት፣ ከ500 በላይ የሥራ አመራርና አስተዳደር ሠራተኞች እንዲሁም 5
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙሉ የራስ-ገዝነት (Autonomy) መብቱን ተግባራዊ ለማድረግ ባካሄደው አዲስ የመዋቅር ማስተካከያ ምክንያት፣ ከ500 በላይ የሥራ አመራርና አስተዳደር ሠራተኞች እንዲሁም 50 መምህራን ያለ ምደባ መቅረታቸው ተገለጸ። ​ከዚሁ የሪፎርም እርምጃ ጋር ተያይዞ የወጡ ዋና ዋና መረጃዎች፦ ​📌 የምደባው መስፈርት፦ ምደባው ለአስተዳደር ሠራተኞች በፈተና ውጤት፣ ለመምህራን ደግሞ በተማሩት የትምህርት ዘርፍ አግባብነትና ዝግጅት ላይ ብቻ ተመስርቶ የተከናወነ መሆኑ ተጠቅሷል። ​📌 የፕሬዚዳንቱ ማብራሪያ፦ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ምላሽ «ማንም ሠራተኛ አልተባረረም» ያሉት ሲሆን፣ ያለ ምደባ የቀሩት ሠራተኞች በጡረታ፣ በካሳ ክፍያ ወይም ዩኒቨርሲቲው በቅርቡ በሚጀምራቸው የንግድ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ተካተው መፍትሔ እንደሚሰጣቸው አረጋግጠዋል። ​📌 ለሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች አቅጣጫ ጠቋሚ፦ በሀገሪቱ ከሚገኙ 46 የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች መካከል የመጀመሪያው ሞዴል የራስ-ገዝ ተቋም የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሪፎርም እርምጃ፣ ቀጣይ ተመሳሳይ እርምጃ ለመውሰድ በመዘጋጀት ላይ ለሚገኙት እንደ ጂማ፣ መቐለ፣ ባህር ዳር እና ጎንደር ዩኒቨርሲቲዎች ትልቅ ማሳያ እንደሚሆን ተገልጿል። @ethioradarinfo

አማራ ክልል የ8ኛ ክፍል ውጤት ይፋ ሆኗል ተማሪዎች ውጤታቸውን https://amhara.ministry.et/#/result የሚለውን አድራሻ በመፃፍ ፤ በሚመጣው ቅጽ ላይ  የተማሪ መለያ ቁጥር (Registration Number) እና ስም በአማርኛ በማስገባት ፤ ዉጤት ይመልከቱ (Check your result) የሚለውን ቁልፍ በመጫን ማየት ይችላሉ፡፡

በቀድሞ የህወሓት አመራሮች የተመሰረተው ስምረት ፓርቲ፣ የትግራይ ሕዝብ የማይፈልገውና የማይመኘው አዲስ ወታደራዊ ግጭት መከሰቱን አስመልካች እጅግ ጠንካራ መግለጫ አውጥቷል። ​የፓርቲው መሪ አቶ ጌታቸው ረዳ ባስተላለፉት መልዕክትና በመግለጫው የተካተቱት ዋና ዋና ነጥቦች፦ ​📌 «የሳተላይት ክትትል ውጤቱን ጠብቁ»፦ ግጭቱን ማንና መቼ እንደጀመረው ለማወቅ አስቀድሞ ተዘጋጅቶ የወጣውን የኋላቀሩ ቡድን መግለጫ ከመስማት ይልቅ፣ ገለልተኛ አካላት የሚያደርጉትን የሳተላይት ክትትልና የክትትሉን ውጤት መጠበቅ ተገቢ መሆኑ ተገልጿል። ​📌 የውጭ ኃይሎች እጅና የፕሪቶሪያ ውል ጥሰት፦ አሁን የተከፈተው ጦርነት በውጭ ኃይሎች ፍላጎትና እቅድ የሚመራ መሆኑን በመጥቀስ፤ ቡድኑ የፕሪቶሪያውን የሰላም ውል በመጣስና የጊዜያዊ አስተዳደሩን ሥልጣን በኃይል ገልብጦ ህገ-ወጥ አስተዳደር ከመሠረተ በኋላ አሁን "ግዛታዊ አንድነትን ማስከበር" በሚል ሽፋን አዲስ ጦርነት ደግሷል ሲል ከሷል። ​📌 «ወደ አራት ኪሎ እንመለሳለን የሚለው ቅዠት ይቁም»፦ አቶ ጌታቸው ረዳ ለትግራይ ሠራዊት አመራሮችና አባላት ባስተላለፉት መልዕክት፣ በግዳጅ ወጣቱን በመመልመል "ወደ አራት ኪሎ እንመለሳለን" የሚለውን ቅዠት በአስቸኳይ ማቆም እንደሚገባ አሳስበዋል። ​📌 «ለወንጀለኞች ህልውና አትሙቱ»፦ አቶ ጌታቸው አክለውም፣ ለሠራዊቱ አባላት ሊያሳስባቸው የሚገባው በጣት የሚቆጠሩ ወንጀለኞች ህልውና ሳይሆን የትግራይ ሕዝብ ሰላምና ህልውና በመሆኑ በሕይወታቸውና በአካላቸው ላይ የሚጫወቱ አካላትን "ይበቃል" ሊሏቸው እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። ​ፓርቲው አክሎም በሃውልቲ የመሸገው ቡድን የዲፕሎማሲ በሮችን ዘግቶና ከውጭ አካላት በሚጠበቅ እርዳታ ተመክቶ ሁኔታዎችን ካበላሸ በኋላ "ዓለም ስማኝ" ማለቱ የአስተዋይነት ማነስን የሚያሳይ ነው ሲል ድርጊቱን በጽኑ ኮንኗል።