ch
Feedback
Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር

Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር

前往频道在 Telegram

Welcome to Ethio Radar, a professional news analysis platform brought to you by a dedicated team of experienced journalist. stay informed,stay on radar! እንኳን ወደ ኢትዮ ራዳር ቻናል መጡ,ሀሳብ፣አስተያየት፣ መረጃ ለማጋራት ማስታወቂያ ለማሰራት በ @Ethioradarr01 ያናግሩን

显示更多

📈 Telegram 频道 Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር 的分析概览

频道 Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር (@ethioradarinfo) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 51 361 名订阅者,在 营销与公关 类别中位列第 192,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 652

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 51 361 名订阅者。

根据 15 九月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -3 111,过去 24 小时变化为 -75,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 1.43%。内容发布后 24 小时内通常能获得 0.56% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 737 次浏览,首日通常累积 290 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 4

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Welcome to Ethio Radar, a professional news analysis platform brought to you by a dedicated team of experienced journalist. stay informed,stay on radar! እንኳን ወደ ኢትዮ ራዳር ቻናል መጡ,ሀሳብ፣አስተያየት፣ መረጃ ለማጋራት ማስታወቂያ ለማሰራት በ @Ethioradarr01 ያናግሩን

凭借高频更新(最新数据采集于 16 九月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 营销与公关 类别中的关键影响点。

51 361
订阅者
-7524 小时
-8237 天
-3 11130 天
帖子存档
አፋልጉኝ! አስቸኳይ ነው ሼር አድርጉት! ዛሬ ይሄ መኪና ተሰርቋል። ዛሬ እቲዮ ጠቢብ አካባቢ በተለምዶ ታይዋን ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ባለ ላቢያጆ ውስጥ ኮድ 3 አአ B33619 መኪና አጣቢው ጠዋት
+1
አፋልጉኝ! አስቸኳይ ነው ሼር አድርጉት! ዛሬ ይሄ መኪና ተሰርቋል። ዛሬ እቲዮ ጠቢብ አካባቢ በተለምዶ ታይዋን ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ባለ ላቢያጆ ውስጥ ኮድ 3 አአ B33619 መኪና አጣቢው ጠዋት 1:00 አከባቢ መኪናውን ይዞ ተሰውሯል። ይሄን መኪና በይትኛውም ቦታ የተመለከታቹ በዚህ ስልክ በመደወል ተባበሩን። ወረታ እንከፍላለን። ስልክ 0911117178/0912442183

እንኳን ለ2019 አዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ! አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የፍቅርና የጤና ይሁንልን! መልካም አዲስ ዓመት!🌼✨ ​Wishing you a Happy Ethiopian New Year! May 2019 bring you peace, joy, and endless prosperity. Happy New Year!🌼✨

➢ ምን ማስተዋወቅ ይፈልጋሉ ❓ 🔔• የምንሰጣቸው የማስታወቂያ አገልግሎቶች ┣➤ የ" ቻናል ማስታወቂያ " ┣➤ የ ድርጅት ማስታወቂያ ┣➤ የ ዩቲዩብ ቻናል ማስታወቂያ ┣➤ ሌሎችም ሽያጮች ማስታወቂያ ያስተዋውቁ👍 ➢ምርትና አገልግሎቶን በተመጣጣኝ ዋጋ ለብዙሀኑ ተደራሽ በማድረግ በእጥፍ ያትርፉ። ከኛጋ በመስራትዎ ይደሰታሉ። በተመጣጣኝ ዋጋ ለማስተዋወቅ ያናግሩን። •➤አሁኑኑ ያናግሩን 👇 @Ethioradarr01 ቻናላችንን Join at and share🙏🙏 👇👇👇 https://t.me/ethioradarinfo

photo content

ትናንት ይፋ ከተደረገው የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ውጤት ጋር በተያያዘ እጅግ በርካታ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ማድረሳቸው ተሰምቷል። ​በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸው ሙ
ትናንት ይፋ ከተደረገው የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ውጤት ጋር በተያያዘ እጅግ በርካታ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ማድረሳቸው ተሰምቷል። ​በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸው ሙሉ በሙሉ 'Disqualified' የተባለባቸው መሆኑን በመግለፅ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴር ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። ሌላው ቀርቶ የበርካታ ተማሪዎች የሂሳብ ትምህርት ውጤታቸው ብቻ 'Disqualified' ማለቱ አሳሳቢ ሆኗል። ​የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች የሆኑት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ በፈተና ወቅት ምንም አይነት የስነ-ምግባር ግድፈት አለመፈጸማቸውን ገልጸው፣ በእርማት ወቅት ቴክኒካል ችግር ከነበረ እንዲታይላቸው በትህትና ጠይቀዋል። ​በዚሁ መሠረት ተማሪዎች ቅሬታቸውን በኦንላይን በ result.ethernet.edu.et ገጽ በመግባት ማቅረብ የሚችሉ ሲሆን፣ አሰራሩም፦ ከውጤቱ ስር መጨረሻ ላይ ያለውን Submit Complaint የሚለውን በመጫን፣ Select a category በሚለው ስር My result disqualified without reason የሚለውን በመምረጥ፣ አጠር ያለ መግለጫና የስልክ ቁጥር ሞልቶ ማስገባት እንደሚቻል ተገልፆል። ​በትናንትናው ዕለት ይፋ በሆነው መረጃ መሠረት የሪሚዲያል ፕሮግራም የማለፊያ ነጥብ ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች (ከ5 የትምህርት አይነቶች) 250 እንዲሁም ለማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች (ከ4 የትምህርት አይነቶች) 200 መሆኑ ታውቋል። ​የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴር በተማሪዎቹ በቀረቡ ቅሬታዎች ላይ የሚሰጡትን ምላሽ ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ እንደሚያደርስ ገልፆል ። @ethioradarinfo

​የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ጋር በመተባበር 100 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያለው የመጀመሪያውን የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ መስርቷል። ​ከዚሁ
​የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ጋር በመተባበር 100 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያለው የመጀመሪያውን የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ መስርቷል። ​ከዚሁ ታሪካዊ የስምምነት እና አዲስ ተቋም መመስረት ጋር ተያይዞ የወጡ ዋና ዋና መረጃዎች፦ ​📌 የIFC አስተዋፅኦ፦ በዚሁ ስምምነት መሠረት IFC የ200 ሚሊዮን ዶላር አስተዋፅኦ ያደርጋል። ​📌 የተቋሙ ፋይዳ፦ ተቋሙ በባንክ ዘርፍ ያለውን የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠን በመቅረፍ በመላ አገሪቱ ተደራሽ የሆነ የቤት ፋይናንስ ስርዓት እንደሚዘረጋ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታውቀዋል። ​📌 ግብ፦ ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ ያለውን ግብ ለማሳካት ያለመ ነው። ​📌 ተጨማሪ ጥቅሞች፦ በፋይናንስ ሥርዓቱ ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት ያለውን ግብ እንደሚያሳካና ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን አጠናክራ እንደምትቀጥልም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጽንኦት ሰጥተዋል። #አብይአሕመድ #abiyahmed #ethiopia @ethioaradarinfo

በአዲስ አበባ ከተማ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ቦታው «ቻይና ካምፕ» አካባቢ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ መስራት በጀመረች በ4ኛው ቀን አሰሪዎቿ በተኙበት አጋጣሚ ቻርጅ ላይ የነበረ 85
በአዲስ አበባ ከተማ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ቦታው «ቻይና ካምፕ» አካባቢ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ መስራት በጀመረች በ4ኛው ቀን አሰሪዎቿ በተኙበት አጋጣሚ ቻርጅ ላይ የነበረ 85 ሺህ ብር የሚገመት አልትራ S21 ሞባይል እና የተለያዩ አልባሳትን ሰርቃ የተሰወረችው ተከሳሽ መልካም አያልነህ በፍርድ ቤት በጽኑ እስራት ተቀጣች። ​የጅማ በር አካባቢ ፖሊስ መምሪያ የምርመራና ክትትል ቡድን በማቋቋም ባደረገው ብርቱ ጥረት ተከሳሿን ከተሰወረችበት ቦታ በአጭር ጊዜ ውስጥ በቁጥጥር ስር በማዋል የተሰረቀውን ሞባይል ማስመለስ ችሏል። በግለሰቧ ላይ አስላጊውን ምርመራ ከተጣራ በኃላም የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ፈጣን ወንጀል ችሎት ጥፋተኝነቷን በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች በማረጋገጥ፣ ተከሳሿን በ5 አመት ከ7 ወር ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ውሳኔ አስተላልፎባታል። ​ፖሊስ በቤት ሰራተኝነት ከተቀጠሩ በኋላ መሰል ወንጀሎችን ፈፅመው የሚሰወሩ በመኖራቸው አሰሪዎች የቅርብ ክትትል ከማድረግ ጀምሮ ለንብረታቸው አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስቧል @ethioradarinfo

አባይ ቲቪ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በአባይ ቴሌቪዥን ላይ ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን አስታወቀ። ​ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱ ባለፉት ሦስት ወራት ባደረገው የቅርብ ክትትል፣ ጣቢያው
አባይ ቲቪ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በአባይ ቴሌቪዥን ላይ ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን አስታወቀ። ​ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱ ባለፉት ሦስት ወራት ባደረገው የቅርብ ክትትል፣ ጣቢያው በዜናዎቹና በፕሮግራሞቹ ላይ ከባድ የሕግና የሙያ ስነ-ምግባር ጥሰቶችን መፈጸሙን ደርሼበታለሁ ብሏል። ​ባለስልጣኑ የዘገባቸው ዋና ዋና የጥሰት ነጥቦች፦ ​📌 የህግና የስነ-ምግባር ጥሰቶች፦ ከባህላችን ያፈነገጡ ፀያፍ ንግግሮችን ማሰራጨት፣ የሴቶችን ክብር የሚነኩ ይዘቶችን ማቅረብ እና ያልተረጋገጡ የዜና ምንጮችን መጠቀም በጣቢያው ላይ ከተመዘገቡት ዋና ዋና ጥሰቶች መካከል ይጠቀሳሉ። ​📌 የጣቢያው ምላሽ፦ የቴሌቪዥን ጣቢያው ኃላፊዎች የተፈጸሙትን ጥፋቶች አምነው ይቅርታ የጠየቁ ሲሆን፣ ችግሮቹን ለማስተካከልና በአፋጣኝ አስፈላጊውን እርምጃ ለመውሰድ ቃል ገብተዋል። @ethioradarinfo

ከእስር የሚፈታ ታራሚ አይኖርም ❗️ አዲስ ዓመት በመጣ ቁጥር በርካታ ቤተሰቦች "ዘመዶቻችን በበዓሉ ምክንያት ከእስር ይፈቱልናል" ብለው ተስፋ የሚያደርጉ ቢሆንም፣ የፍትሕ ሚኒስቴር ያሰማው ዜና ግን
ከእስር የሚፈታ ታራሚ አይኖርም ❗️ አዲስ ዓመት በመጣ ቁጥር በርካታ ቤተሰቦች "ዘመዶቻችን በበዓሉ ምክንያት ከእስር ይፈቱልናል" ብለው ተስፋ የሚያደርጉ ቢሆንም፣ የፍትሕ ሚኒስቴር ያሰማው ዜና ግን ለብዙዎች አስደንጋጭ ሆኗል። ​ሚኒስቴሩ ለመናኸሪያ ሬዲዮ በሰጠው ማብራሪያ እንደገለጸው፤ በዓላትን ምክንያት በማድረግ ብቻ በይቅርታ የሚፈታ አንድም ታራሚ የለም። "ይቅርታ" የሚደረገው በአዲሱ መመሪያ መሠረት በይቅርታ ቦርድ ተመርምሮ ሲወሰን ብቻ እንደሆነ ተብራርቷል። ​ብዙዎቻችን "ምህረት" እና "ይቅርታ" አንድ ይመስለናል። ነገር ግን ምህረት ከፍተኛ የፖለቲካ ውሳኔ ሲሆን፣ ይቅርታ ግን ጥብቅ የሆነ ሕጋዊ አካሄድና መመሪያን የተከተለ አሰራር አለው።​በሌላ በኩል፣ ክልሎች በራሳቸው ርዕሳነ-መስተዳድሮች አማካኝነት ታራሚዎችን ሊፈቱ እንደሚችሉ ተጠቁሟል። @ethioradarinfo

ተገቢውን የጉምሩክ ሂደት ያላለፉና በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ የተለያዩ ዓይነትና መጠን ያላቸው ከ700 በላይ የሞባይል ቀፎዎች፣ ከሁለት ሺህ በላይ የቻርጀር ገመዶች፣ ልዩ ልዩ የኤሌክ
ተገቢውን የጉምሩክ ሂደት ያላለፉና በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ የተለያዩ ዓይነትና መጠን ያላቸው ከ700 በላይ የሞባይል ቀፎዎች፣ ከሁለት ሺህ በላይ የቻርጀር ገመዶች፣ ልዩ ልዩ የኤሌክትሮኒክስ መለዋወጫዎችና አልበሳት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ፖሊስ አስታወቀ። ​ከዚሁ የኮንትሮባንድ እገታ ጋር ተያይዞ የወጡ ዋና ዋና መረጃዎች፦ ​📌 የተያዙበት ቦታና ሰዓት፦ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የመሣለሚያ አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በክፍለ ከተማው ወረዳ 8 ልዩ ቦታው «አዲስ አበባ የገበያ ማዕከል» አካባቢ ከምሽቱ 1፡00 ሠዓት ላይ ነው እቃዎቹ የተያዙት። ​📌 ተጠርጣሪዎቹና የተጠቀሙበት ተሽከርካሪ፦ አሰፋ ጸጋ እና አማኑኤል ብርሀኑ የተባሉ ሁለት ተጠርጣሪዎች የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹን የሠሌዳ ቁጥር B-77746 አ.አ በሆነ «ሱዙኪ» የጭነት ተሽከርካሪ ጭነው ሲንቀሳቀሱ በሥራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ውለዋል። ​📌 የሕግ ሂደትና የፖሊስ መልዕክት፦ የክፍለ ከተማው ፖሊስ ዋና መምሪያ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ተገቢውን የሰውና የሰነድ ማስረጃ በማደራጀት ክስ እንደሚያስመሰርት ገልጻል። ህብረተሰቡም መሰል የወንጀል ድርጊቶች በሀገር ምጣኔ ሀብትና በህጋዊ ነጋዴዎች ላይ የሚያሳድሩትን አሉታዊ ተፅዕኖ በመረዳት መረጃ የመስጠት ባህሉን ሊያጠናክር እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል። @ethioradarinfo

ያለ አምራችነት ፈቃድ በመንደሮች በሚገኙ ሱቆች እና የንግድ ቦታዎች የሚመረት የለውዝ ቅቤ የጥራት እና የጤና ምርመራ ስለማይደረግለት ለጤና ችግር የመዳረግ እድሉ ከፍተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ የለውዝ ቅቤ አምራቾች ማኅበር እና የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት አስታውቀዋል። ​ከዚሁ አሳሳቢ የጤና እና የጥራት ማስጠንቀቂያ ጋር ተያይዞ የወጡ ዋና ዋና መረጃዎች፦ ​📌 የጤና ስጋቱ እና «አፍላቶክሲን»፦ የማኅበሩ ተወካይ አቶ ተስፋዬ አስራት ለአሐዱ ሬዲዮ እንደገለጹት፤ ለውዝ «አፍላቶክሲን» በተባለ መርዛማ ሻጋታ የመጠቃት እድሉ ከፍተኛ በመሆኑ ከእርሻ ጀምሮ ጥብቅ ቁጥጥር ይፈልጋል። በየመንደሩ የሚፈጨው ለውዝ ከምርት ስብሰባ ጀምሮ ሲቆላም ሆነ ሲፈጭ ተገቢው ጥንቃቄ ካልተደረገለት ካንሰርን ጨምሮ ለተለያዩ ከባድ የጤና እክሎች ያጋልጣል። ​📌 የማኅበራዊ ሚዲያ ማስታወቂያዎች፦ በቲክቶክ እና በሌሎች ማኅበራዊ ትስስር ገጾች በሱቆች የሚጨመቀውን የለውዝ ቂቤ ለማስተዋወቅ ሲባል የሕጋዊ ድርጅቶችን ስም በማጥፋት የንግድ ጉዳት የሚያደርሱ ያልተገቡ ማስታወቂያዎች እየተስፋፉ በመሆኑ ፈጻሚዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ተጠይቋል። ​📌 የኢንስቲትዩቱ አዲስ አሰራር፦ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሰረት በቀለ፤ አብዛኛዎቹ ተጠቃሚዎች እና አምራቾች ስለ «አፍላቶክሲን» በቂ ግንዛቤ እንደሌላቸው ገልጸው፣ ችግሩን ለመፍታት ኢንስቲትዩቱ ለአምራቾች የሙያ የብቃት ማረጋገጫ ለመስጠት ዝግጅት ማጠናቀቁን ተናግረዋል። ​📌 አስገዳጅ መስፈርቶች፦ ወደፊት ማንኛውም አምራች የንግድ ፈቃድ ከመውጣቱ በፊት የብቃት ማረጋገጫ ማግኘቱ አስገዳጅ እንደሚሆንና፤ ምርቶች ለገበያ ከመቅረባቸው በፊት የመቆያ ጊዜያቸው፣ የአገልግሎት ማብቂያቸው፣ የተሠሩበት አድራሻ እና የአጠቃቀም መመሪያዎች በግልጽ ሊካተቱባቸው እንደሚገባ ታውቋል።

ያለ አምራችነት ፈቃድ በመንደሮች በሚገኙ ሱቆች እና የንግድ ቦታዎች የሚመረት የለውዝ ቅቤ የጥራት እና የጤና ምርመራ ስለማይደረግለት ለጤና ችግር የመዳረግ እድሉ ከፍተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ የለውዝ ቅ
ያለ አምራችነት ፈቃድ በመንደሮች በሚገኙ ሱቆች እና የንግድ ቦታዎች የሚመረት የለውዝ ቅቤ የጥራት እና የጤና ምርመራ ስለማይደረግለት ለጤና ችግር የመዳረግ እድሉ ከፍተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ የለውዝ ቅቤ አምራቾች ማኅበር እና የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት አስታውቀዋል። ​ከዚሁ አሳሳቢ የጤና እና የጥራት ማስጠንቀቂያ ጋር ተያይዞ የወጡ ዋና ዋና መረጃዎች፦ ​📌 የጤና ስጋቱ እና «አፍላቶክሲን»፦ የማኅበሩ ተወካይ አቶ ተስፋዬ አስራት ለአሐዱ ሬዲዮ እንደገለጹት፤ ለውዝ «አፍላቶክሲን» በተባለ መርዛማ ሻጋታ የመጠቃት እድሉ ከፍተኛ በመሆኑ ከእርሻ ጀምሮ ጥብቅ ቁጥጥር ይፈልጋል። በየመንደሩ የሚፈጨው ለውዝ ከምርት ስብሰባ ጀምሮ ሲቆላም ሆነ ሲፈጭ ተገቢው ጥንቃቄ ካልተደረገለት ካንሰርን ጨምሮ ለተለያዩ ከባድ የጤና እክሎች ያጋልጣል። ​📌 የማኅበራዊ ሚዲያ ማስታወቂያዎች፦ በቲክቶክ እና በሌሎች ማኅበራዊ ትስስር ገጾች በሱቆች የሚጨመቀውን የለውዝ ቂቤ ለማስተዋወቅ ሲባል የሕጋዊ ድርጅቶችን ስም በማጥፋት የንግድ ጉዳት የሚያደርሱ ያልተገቡ ማስታወቂያዎች እየተስፋፉ በመሆኑ ፈጻሚዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ተጠይቋል። ​📌 የኢንስቲትዩቱ አዲስ አሰራር፦ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሰረት በቀለ፤ አብዛኛዎቹ ተጠቃሚዎች እና አምራቾች ስለ «አፍላቶክሲን» በቂ ግንዛቤ እንደሌላቸው ገልጸው፣ ችግሩን ለመፍታት ኢንስቲትዩቱ ለአምራቾች የሙያ የብቃት ማረጋገጫ ለመስጠት ዝግጅት ማጠናቀቁን ተናግረዋል። ​📌 አስገዳጅ መስፈርቶች፦ ወደፊት ማንኛውም አምራች የንግድ ፈቃድ ከመውጣቱ በፊት የብቃት ማረጋገጫ ማግኘቱ አስገዳጅ እንደሚሆንና፤ ምርቶች ለገበያ ከመቅረባቸው በፊት የመቆያ ጊዜያቸው፣ የአገልግሎት ማብቂያቸው፣ የተሠሩበት አድራሻ እና የአጠቃቀም መመሪያዎች በግልጽ ሊካተቱባቸው እንደሚገባ ታውቋል።

''አለሁ'' ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ከመገናኛ ብዙኃን ራቅ ማለታቸውን ተከትሎ የተለያዩ የሐሰት ዜናዎች ሲሰራጭ ሰንብቷል። በዛሬው እለት ብልጽግና ፓርቲ በይፋዊ የቲክቶክ ገጹ ለሰሞንኛ
''አለሁ'' ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ከመገናኛ ብዙኃን ራቅ ማለታቸውን ተከትሎ የተለያዩ የሐሰት ዜናዎች ሲሰራጭ ሰንብቷል። በዛሬው እለት ብልጽግና ፓርቲ በይፋዊ የቲክቶክ ገጹ ለሰሞንኛው አጀንዳ መልስ የሚመስል ቪዲዮ ለቋል። በቪዲው ላይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ! "አለሁ እግዚአብሔር ይመስገን" በማለት ሲናገሩ ተሰምተዋል። @ethioradarinfo

የምሽቱ ትልቁን ፍልሚያ ጆኒ አሸነፈ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በታላቅ ድምቀት ሲካሄድ የሰነበተው የኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ኮከቦች ምሽት በጉጉት በተጠበቀውና በዋናው የዋንጫ ፍልሚያ (Main
የምሽቱ ትልቁን ፍልሚያ ጆኒ አሸነፈ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በታላቅ ድምቀት ሲካሄድ የሰነበተው የኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ኮከቦች ምሽት በጉጉት በተጠበቀውና በዋናው የዋንጫ ፍልሚያ (Main Event) በይፋ ፍጻሜ አግኝቷል! በሚድል ዌይት (Middleweight MMA Bout) ዘርፍ በጆኒ እና በሴዶ መካከል የተደረገው ይህ አስደናቂና አቃጣጣኝ ፍልሚያ የመላው ተመልካች ቀልብ የሳበ ነበር። በከፍተኛ የኤምኤምኤ (MMA) ቴክኒክ፣ የላቀ ብቃትና ፍጹም የድል ወኔ ተጋጣሚውን ሴዶን ያሸነፈው ጆኒ፡ የምሽቱን ትልቅ ድል በመቀዳጀት አዲሱ የ ETFC 2 ቻምፒዮን (Champion) በመሆን ዘውዱን ደፍቷል! #ዳጉ_ጆርናል

በጆኒ አሸናፊነት ተጠናቀቀ‼
በጆኒ አሸናፊነት ተጠናቀቀ‼

10ኛው ፍልሚያ በኢድሪስ አሸናፊነት ተጠናቀቀ! በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም እየተካሄደ በሚገኘው የኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ምሽት፣ በዕለቱ አሥረኛው ፍልሚያ በኤምኤምኤ (MMA Bout) ዘርፍ በኢ
10ኛው ፍልሚያ በኢድሪስ አሸናፊነት ተጠናቀቀ! በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም እየተካሄደ በሚገኘው የኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ምሽት፣ በዕለቱ አሥረኛው ፍልሚያ በኤምኤምኤ (MMA Bout) ዘርፍ በኢድሪስ እና በቦይካ መካከል የተደረገው አቃጣጣኝ ፍልሚያ በይፋ ፍጻሜ አግኝቷል። ብቃትና ወኔ በተሞላው በዚህ ግጥሚያ ኢድሪስ ተጋጣሚውን ቦይካን በማሸነፍ ሌላኛውን ደማቅ ድል አስመዝግቧል! #ዳጉ_ጆርናል

ንቃተ ህሊና ፍልሚያ አሸነፏል በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም እየተካሄደ በሚገኘው የኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ምሽት፣ በዕለቱ ዘጠነኛው ፍልሚያ በኤምኤምኤ (MMA Bout) ዘርፍ በሮቤል እና በንቃተ
ንቃተ ህሊና ፍልሚያ አሸነፏል በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም እየተካሄደ በሚገኘው የኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ምሽት፣ በዕለቱ ዘጠነኛው ፍልሚያ በኤምኤምኤ (MMA Bout) ዘርፍ በሮቤል እና በንቃተ ህሊና መካከል የተደረገው አቃጣጣኝ ፍልሚያ በይፋ ፍጻሜ አግኝቷል። በከፍተኛ ቴክኒክ፣ ብቃትና ወኔ በተሞላው በዚህ ግጥሚያ ንቃተ ህሊና ተጋጣሚውን ሮቤልን በማሸነፍ ሌላኛውን ደማቅ ድል አስመዝግቧል! @ethioradarinfo