ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 533 подписчиков, занимая 8 338 место в категории Технологии и приложения и 2 162 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 533 подписчиков.

Согласно последним данным от 29 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 6, а за последние 24 часа — -1, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.10%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.85% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 901 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 619 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 8.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 30 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 533
Подписчики
-124 часа
-167 дней
+630 день
Архив постов
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በዌብሳይት ኤክስፐርት 2ኛ እና ኮሙዩኒኬሽን ኦፊሰር 3ኛ የሥራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መጋቢት 2 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች በሙሉ ህዳር 03 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው በተቋሙ ዋና መ/ቤት የማሰልጠኛ አዳራሽ የጽሑፍ ፈተና ስለሚሰጥ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈ        ........///........ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን የአዲስ አበባ ከተማ እግር ኳስ ቡድንን በማሸነፍ ቀጣዩን ዙር ተቀላቅሏል።                 ጥቅምት 25 ቀን 2016 ዓ.ም. በአበበ ቢቄላ ስቴዲየም በተካሄደው የኢትዮጵያ የጥሎ ማለፍ ዋንጫ የእግር ኳስ ውድድር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የአዲስ አበባ አቻውን አንድ ለባዶ በመርታት ነው ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍ የቻለው።                                              ለክለቡ ብቸኛዋን የማሸነፊያ  ጎል በ22ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠረው የአማካይ ክፍል ተጫዋቹ ቢኒያም ካሳሁን ነው።     በጨዋታው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በኳስ ቁጥጥር እና በፍጥነት በማጥቃት  በተጋጣሚው ላይ የበላይነት መውሰድ ችሏል።                     በ75ኛው ደቂቃ በሰራው ጥፋት የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ግብ ጠባቂ በሽር ደሊል በቀጥታ በቀይ ካርድ ከሜዳ በመሰናበቱ ክለቡ ቀሪዎቹን 15  ደቂቃዎች በ10 ተጫዋቾች ለመጫወት ተገዷል።                       የአዲስ አበባ ከተማ እግር ኳስ ክለብ በበኩሉ በመከላከል እና መልሶ በማጥቃት ጨዋታውን ለመቆጣጠር ቢሞክርም ከሽንፈት ሳይድን ቀርቷል።                                   የመጀመሪያውን ዙር የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫ በድል ያጠናቀቀው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በቀጣይ በሚከናወን የዕጣ አወጣጥ ከኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ ክለብ ጋር የሚጫወት ይሆናል።                                              በዚህ የውድድር ዓመት ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እንደገና ለመመለስ ብርቱ ፉክክር የሚጠብቀው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የመጀመሪያ መርሀ ግብሩን ህዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት በአበበ ቢቄላ ስቴዲየም ከሀላባ ከተማ ጋር የሚያከናውን ይሆናል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ክለባቸውን እንዲያበረታቱ የክለቡ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሲሳይ ለማ ጥሪ አቅርበዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሰከረም 08 ቀን 2016 ዓ.ም በአውቶ ሜካኒክ 2ኛ፣ አውቶ ሜካኒክ 1ኛ፣ አውቶ ኤሌክትሪሽያን 3ኛ፣ አውቶ ኤሌክትሪሽያን 2ኛ፣ አውቶ ኤሌክትሪሽያን 1ኛ፣ አውቶ ቦዲ 2ኛ የስራ መደቦች ስራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በዚህ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች ጥቅምት 29 ቀን 2016 ዓ.ም ከጥዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልፅ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው በተቋሙ ዋናው መ/ቤት የማሰልጠኛ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና ስለሚሰጥ ለፈተናው እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

photo content
+3

የማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ተጨማሪ የኃይል ጥያቄ የማስተናገድ አቅም አላቸው ………///…….. የሀዋሳ ቁጥር አንድና ቁጥር ሁለት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል የሚፈልጉ ደንበኞችን ማስተናገድ የሚያስችል ትልቅ አቅም እንዳለቸው የጣቢያዎቹ ኃላፊዎች አስታወቁ። የሀዋሳ ቁጥር ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ዳንኤል አንጀሎ እንደገለጹት ባለ 230 ኪሎ ቮልት አቅም ያለው የማከፋፈያ ጣቢያው ሃያ ባለ 33 እና 8 ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡ ይሁንና ዝግጁ ከተደረጉት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ውስጥ ሦስቱ እንዲሁም ከባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ውስጥ ደግሞ አምስቱ መስመሮች ብቻ ለሀዋሳ ከተማ፣ ለሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክና በዙሪያው ለሚገኙ ፋብሪካዎች ኃይል እየሰጡ እንደሚገኙ ሥራ አስኪያጁ አብራርተዋል። ጣቢያው 420 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የመስጠት አቅም ቢኖረውም እየሰጠ የሚገኘው ከ140 ሜጋ ዋት ስለማይበልጥ ለኃይል ጠያቂ ደንበኞች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችለው አቅም እንዳለው ኃላፊው ተናግረዋል። የሀዋሳ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ ተወካይ ወ/ሪት ቤዛዊት ብርሃኑ ጣቢያው መስጠት ከሚችለው 62 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት አቅም ውስጥ እየሰጠ የሚገኘው እስከ 38 ሜጋ ዋት ኃይል ብቻ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ተወካይዋ ገለጻ ጣቢያው ጣቢያው በ 132 ኪሎ ቮልት ኃይል ተቀብሎ በ15 ኪሎ ቮልት ባሉት ስምንት ወጪ መስመሮች ለሀዋሳ ከተማና በዙሪያው ለሚገኙ የዱቄት ፋብሪካዎች ኃይል እየሰጠ ይገኛል፡፡ በ33 ኪሎ ቮልት ባሉት ሁለት ወጪ መስመሮች ደግሞ በሀዋሳ ዙሪያ እስከ 110 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ለሚገኙ የወረዳ ከተሞች ኃይል እየሰጠ ይገኛል ብለዋል። ጣቢያው በአሁኑ ወቅት ባለው አቅም አገልግሎት ፈልገው ለሚመጡ ተጨማሪ ደንበኞች ኃይል ለመስጠት ዝግጁ መሆኑንም ተወካይዋ ጠቁመዋል። የሀዋሳ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ በ1970ዎቹ መጀመሪያ በዲዝል ጀነሬተር ኃይል መስጠት የጀመረና በተለያዩ ጊዚያት በተደረጉለት የማስፋፊያ ሥራዎች አቅሙን ያሳደገ ጣቢያ ሲሆን የሀዋሳ ቁጥር ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ደግሞ ሐምሌ 2011 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረ ጣቢያ ነው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 23 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከሱዳኑ አል ሂላል ጋር አቻ ተለያየ ………///……… የኢትዮ - ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ከሱዳኑ አል ሂላል ጋር ባደረገው የወዳጅነት ጨዋታ ሁለት አቻ ተለያይቷል። ጨዋታው በተጀመረ አምስተኛው ደቂቃ አል ሂላል በፍጹም ቅጣት ምት ጎል አስቆጥሮ መምራት የቻለ ቢሆንም በመጀመሪያው አጋማሽ መገባደጃ ሰዓት ላይ ናትናኤል ሰለሞን ለኢትዮ ኤሌክትሪክ የአቻነቷን ጎል አስቆጥሯል። በመጀመሪያዎቹ 15 ደቂቃዎች በኳስ ቁጥጥር እና በተደጋጋሚ የተቃራኒ ቡድን የግብ ክልል በመድረስ አል ሂላል ጫና ማድረግ የቻለ ሲሆን ኢትዮ ኤሌክትሪክ በበኩሉ በአጭር እና ፈጣን የኳስ ቅብብል ወደ ጨዋታው በመመለስ የበላይነት አሳይቷል። በሁለተኛው አጋማሽ የተጫዋች ቅያሬ አድርጎ የገባው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ይበልጥ ጨዋታውን በመቆጣጠር በአጥቂው አቤል ሀብታሙ አማካኝነት ሁለተኛውን ጎል ማስቆጠር ችሏል። ይሁንና ጨዋታው ሊጠናቀቅ ስምንት ደቂቃዎች ሲቀሩት አል ሂላል አቻ ለመሆን ጫና አድርጎ በመጫወቱ ጥረቱ ሰምሮ በ85ኛው ደቂቃ የአቻነት ጎል አስቆጥሯል። ከኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባለፈው ዓመት የወረደው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በዚህ የውድድር ዓመት በከፍተኛ ሊግ ተሳትፎ እንደገና ወደ ሊጉ ለመመለስ ጠንካራ ልምምድ በማድረግ ላይ ይገኛል። የሱዳኑ አል ሂላል በበኩሉ በቀጣይ ላለበት ኢንተርናሽናል ጨዋታ በአዲስ አበባ ዝግጅት በማድረግ ላይ ነው። በኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫ ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በመጪው እሁድ ጥቅምት 25 ቀን 2016 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ከአዲስ አበባ እግር ኳስ ቡድን ጋር የሚጫወት ይሆናል። በተመሳሳይ የሴቶች ፕሪሜርሊግ ህዳር 16 ቀን 2016 ዓ.ም የሚጀመር ሲሆን በዚህ ዓመት ለሻምፒዮናነት የሚወዳደረው የኢትዮ ኤሌክትሪክ ሴቶች እግር ኳስ ቡድን የቅድመ ዝግጅት ልምምዱን ጀምሯል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

EEP Communication - Статистика и аналитика Telegram-канала @eepcommuication