ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 533 подписчиков, занимая 8 338 место в категории Технологии и приложения и 2 162 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 533 подписчиков.

Согласно последним данным от 29 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 6, а за последние 24 часа — -1, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.10%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.85% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 901 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 619 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 8.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 30 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 533
Подписчики
-124 часа
-167 дней
+630 день
Архив постов
photo content
+6

ባለፉት 21 ቀናት ብቻ በሦስት የማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ስርቆት ተፈጽሟል ........///........ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሪጅን አንድ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ በሚያስተዳድራቸው የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች ላይ በተፈጸመ ስርቆት አራት ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ኪሳራ መድረሱን መምሪያው አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የማስተላለፊያ መስመርና ኦፕቲካል ፋይበር ኦፕሬሽን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ በፍቃዱ በቀለ እንደተናገሩት ባለፉት ሦስት ሳምንታት በሱሉልታ-ገርበጉራቻ- ደብረ ማርቆስ ባለ 400 ኪሎ ቮልት፣ በጌዶ-ገፈርሳ ባለ 230 ኪሎ ቮልት እና በቃሊቲ-ኮተቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ስርቆት ተፈጽሟል፡፡ በሱሉልታ-ገርበጉራቻ- ደብረ ማርቆስ ባለ 400 ኪ.ቮ እና በጊዶ-ገፈርሳ ባለ 230 ኪ.ቮ መስመሮች ላይ በተፈጸመው ስርቆት 338 የታወር ብረቶች፣ 678 ብሎኖች እና 1 ሺህ 290 የብሎን ማሰሪያዎች በዘራፊዎች መወሰዱን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ከቃሊቲ - ኮተቤ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የማስተላለፊያ መስመር ላይ አንድ የመስመሩ ተሸካሚ ምሶሶ መውደቁንም አመልክተዋል፡፡ ባለፉት ሁለት ሳምንታት በተፈጸሙ ስርቆቶች በአስር የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶችች ላይ ጉዳት እንደደረሰ ያነሱት ሥራ አስኪያጁ ጉዳት የደረሰባቸውን የምሰሶ አካላት መልሶ ለመተካት ከ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ የምሶሶዎችን የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚያፈልጉ የኤሌክትሮድ፣ የጉልበት ሠራተኛ፣ የነዳጅ እና ሌሎች ግብዓቶችን ለማሟላት የሚወጣውን ወጪ ጨምሮ በአጠቃላይ ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚያፈልግ አቶ በፍቃዱ ተናግረዋል። በመስመሮቹ ላይ በተፈጸመው ስርቆት ምክንያት ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ባይኖሩም ችግሩ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በሚሰራው ሥራ ላይ እንቅፋት እየሆነ ይገኛል ብለዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ለችግሩ አፋጣኝ መፍትሔ ካልተሰጠው በቀጣይ ጊዜያት ስርቆት በሚስተዋልባቸው አካባቢዎች የኃይል መቋረጥ ሊያጋጥም ይችላል፡፡ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የብረት ማቅለጫ ፋብሪካዎች የተሰረቁ እና ቁርጥራጭ ብረታብረቶችን በግብዓትነት መጠቀማቸው በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ በተደጋጋሚ ለሚፈጸመው ስርቆት ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡ በስርቆቱ ላይ የተሳተፉ አምስት ተጠርጣሪዎች በህብረተሰቡ ጥቆማና ትብብር በጸጥታ አካላት በቁጥጥር ስር እንደዋሉና እና ቀሪ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል በአካባቢው የሚገኙ የጸጥታ አካላት ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙ ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡ የጸጥታ አካላት ያደረጉትን ጥረት አመስግነው በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ ስርቆቶችን ለመከላከል ሁሉም የመስተዳድርና የፀጥታ አካላት ንብረቶችን በኃላፊነት መጠበቅ እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡ የማዕከላዊ ሪጅን አንድ የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ያላቸው 1 ሺህ 404 ነጥብ 39 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመር እና 22 ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እያስተዳደረ ይገኛል፡፡ ሪጅኑ በሚያስተዳድራቸው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች ላይ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በተፈጸመ ስርቆት በተቋሙ ላይ ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ኪሳራ መድረሱን ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር 4ኛ የሥራ መደብ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጳጉሜ 01 ቀን 2015 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍ እና የተግባር ፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከጥቅምት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት በሚገኘው የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን፡፡

photo content
+4

የሆለታ ማከፋፈያ ጣቢያ ግሪዱን በማረጋጋት ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው .........///.......... የሆለታ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ የሀገሪቱ የኃይል ቋት እንዲረጋጋ በማድረግ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ጥላሁን አዘዘው እንደገለፁት በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ከተገነቡት ጣቢያዎች መካከል ትልቁና የኤሌክትሪክ መዋዠቅ እንዳይከሰት የሚደርግ ስታቲክ ቫር ኮምፐንሴተር የተባለ ቴክኖሎጂ የተገጠመለት የማከፋፈያ ጣቢያ ነው። የተገጠመለት ቴክኖሎጂ ኃይል በሚዋዥቅበት ጊዜ ቮልቴጁን በማረጋጋት የጣቢያውን ደህንነት ከማስጠበቁ በተጨማሪ ብሔራዊ የኃይል ቋት ወይም ግሪዱ እንዳይረበሽ በማድረግ በሀገሪቱ ጤናማ የኤሌክትሪክ ፍሰት እንዲኖር እንደሚያግዝ ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ ማከፋፈያ ጣቢያው ከህዳሴ ግድብ በደዴሳ አድርጎ የሚመጣውን 500 ኪሎ ቮልት ኃይል ተቀብሎ ወደ 400 ኪሎ ቮልት በመቀየር ለሱልልታ፣ ሰበታ እና ገላን ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል የሚልክ ነው። ማከፋፈያ ጣቢያው በአካባቢው መገንባቱ ከግሪዱ ኃይል ለመስጠትና ለመቀበል አማራጮችን እንደሚያሰፋ ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል። ጣቢያው ለሆለታ ከተማና አካባቢው ማህበረሰብ እንዲሁም በዙሪያው እየተገነቡ ላሉት ኢንዱስትሪዎች ያልቆራረጠ ኃይል የሚያቀርቡ ከ6 በላይ ወጪ መስመሮች እንዲኖሩት የማስፋፊያ ሥራዎች መከናወናቸውን ሥራ አስኪያጁ አስታውሰዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 21 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የመቱ - ማሻ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ግንባታ በቅርቡ ዳግም ይጀመራል ...///… በተለያዩ ምክንያቶች ግንባታው ተቋርጦ የቆየው የሙቱ - ማሻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት በቅርቡ እንደሚጀመር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የፕሮግራም 1 ፕሮጀክት አስተዳደር 1 ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ ሙሉብርሃን እንዳስታወቁት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቱ በሚያልፍባቸው ቦታዎች ላይ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ጥናት ተካሂዶ ሥራው ሲሰራ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ በአካባቢው በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) የተመዘገበ ደን በመኖሩ ምክንያት ፕሮጀክቱን ፋይናንስ የሚያደርገው የዓለም ባንክ ተጨማሪ ጥናት መደረግ አለበት የሚል ምክረ ሀሳብ በማቅረቡ የግንባታ ሥራው መቋረጡን ተናግረዋል፡፡ ይኼን ተከትሎ በውጭ አማካሪ ድርጅት ተጨማሪ የአካባቢያዊ ተጽዕኖ ጥናት ተካሂዶ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ የሚዘረጋበትን አቅጣጫ በመቀየር ለችግሩ መፍትሔ መስጠቱን ገልፀዋል፡፡ ከአካባቢያዊ ተፅዕኖ ጥናት ጋር በተያያዘ ባንኩ ያነሳው ጥያቄ መፍትሄ እስኪያገኝ ድረስ ፕሮጀክቱ ከሁለት ዓመት በላይ ተቋርጦ መቆየቱንም ነው ሥራ አስኪያጁ የጠቆሙት፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የመስመር ዝርጋታው 68 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝመት የነበረው ቢሆንም የዲዛይን ለውጥ በመደረጉ ምክንያት 3 ኪሎ ሜትር ጨምሯል፡፡ የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ተቋርጦ እንዲቆይ በመደረጉ ምክንያት ሥራ ተቋራጩ የተጨማሪ በጀት ጥያቄ አቅርቦ እንደነበር የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ችግሩ መፍትሔ እስኪያገኝ ድረስ ወደ ግንባታ ቦታው ለመግባት ፈቃደኛ ሳይሆን መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡ በዋጋ ጭማሪው ዙሪያ ከግንባታ ተቋራጩ ጋር መግባባት ላይ በመደረሱ ግንባታው በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ እንደሚጀምር ሥራ አስኪያጁ አረጋግጠዋል፡፡ የማስተላለፊያ መስመሩ ከሚኖሩት 174 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች መካከል የ50 ምሶሶዎች መትከያ የመሰረት ሥራ መከናወኑንና የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ 75 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል፡፡ የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ሲኖ ሀይድሮ በተባለ የቻይና ኩባንያ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን በማማከር ሥራው ላይ ደግሞ ኢ ኤል ሲ የተሰኘ የጣሊያን ኩባንያ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 20 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1