es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 533 suscriptores, ocupando la posición 8 338 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 162 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 533 suscriptores.

Según los últimos datos del 29 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 6, y en las últimas 24 horas de -1, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 25.10%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.85% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 901 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 619 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 8.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 30 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 533
Suscriptores
-124 horas
-167 días
+630 días
Archivo de publicaciones
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በዌብሳይት ኤክስፐርት 2ኛ እና ኮሙዩኒኬሽን ኦፊሰር 3ኛ የሥራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መጋቢት 2 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች በሙሉ ህዳር 03 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው በተቋሙ ዋና መ/ቤት የማሰልጠኛ አዳራሽ የጽሑፍ ፈተና ስለሚሰጥ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈ        ........///........ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን የአዲስ አበባ ከተማ እግር ኳስ ቡድንን በማሸነፍ ቀጣዩን ዙር ተቀላቅሏል።                 ጥቅምት 25 ቀን 2016 ዓ.ም. በአበበ ቢቄላ ስቴዲየም በተካሄደው የኢትዮጵያ የጥሎ ማለፍ ዋንጫ የእግር ኳስ ውድድር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የአዲስ አበባ አቻውን አንድ ለባዶ በመርታት ነው ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍ የቻለው።                                              ለክለቡ ብቸኛዋን የማሸነፊያ  ጎል በ22ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠረው የአማካይ ክፍል ተጫዋቹ ቢኒያም ካሳሁን ነው።     በጨዋታው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በኳስ ቁጥጥር እና በፍጥነት በማጥቃት  በተጋጣሚው ላይ የበላይነት መውሰድ ችሏል።                     በ75ኛው ደቂቃ በሰራው ጥፋት የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ግብ ጠባቂ በሽር ደሊል በቀጥታ በቀይ ካርድ ከሜዳ በመሰናበቱ ክለቡ ቀሪዎቹን 15  ደቂቃዎች በ10 ተጫዋቾች ለመጫወት ተገዷል።                       የአዲስ አበባ ከተማ እግር ኳስ ክለብ በበኩሉ በመከላከል እና መልሶ በማጥቃት ጨዋታውን ለመቆጣጠር ቢሞክርም ከሽንፈት ሳይድን ቀርቷል።                                   የመጀመሪያውን ዙር የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫ በድል ያጠናቀቀው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በቀጣይ በሚከናወን የዕጣ አወጣጥ ከኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ ክለብ ጋር የሚጫወት ይሆናል።                                              በዚህ የውድድር ዓመት ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እንደገና ለመመለስ ብርቱ ፉክክር የሚጠብቀው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የመጀመሪያ መርሀ ግብሩን ህዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት በአበበ ቢቄላ ስቴዲየም ከሀላባ ከተማ ጋር የሚያከናውን ይሆናል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ክለባቸውን እንዲያበረታቱ የክለቡ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሲሳይ ለማ ጥሪ አቅርበዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሰከረም 08 ቀን 2016 ዓ.ም በአውቶ ሜካኒክ 2ኛ፣ አውቶ ሜካኒክ 1ኛ፣ አውቶ ኤሌክትሪሽያን 3ኛ፣ አውቶ ኤሌክትሪሽያን 2ኛ፣ አውቶ ኤሌክትሪሽያን 1ኛ፣ አውቶ ቦዲ 2ኛ የስራ መደቦች ስራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በዚህ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች ጥቅምት 29 ቀን 2016 ዓ.ም ከጥዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልፅ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው በተቋሙ ዋናው መ/ቤት የማሰልጠኛ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና ስለሚሰጥ ለፈተናው እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

photo content
+3

የማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ተጨማሪ የኃይል ጥያቄ የማስተናገድ አቅም አላቸው ………///…….. የሀዋሳ ቁጥር አንድና ቁጥር ሁለት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል የሚፈልጉ ደንበኞችን ማስተናገድ የሚያስችል ትልቅ አቅም እንዳለቸው የጣቢያዎቹ ኃላፊዎች አስታወቁ። የሀዋሳ ቁጥር ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ዳንኤል አንጀሎ እንደገለጹት ባለ 230 ኪሎ ቮልት አቅም ያለው የማከፋፈያ ጣቢያው ሃያ ባለ 33 እና 8 ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡ ይሁንና ዝግጁ ከተደረጉት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ውስጥ ሦስቱ እንዲሁም ከባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ውስጥ ደግሞ አምስቱ መስመሮች ብቻ ለሀዋሳ ከተማ፣ ለሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክና በዙሪያው ለሚገኙ ፋብሪካዎች ኃይል እየሰጡ እንደሚገኙ ሥራ አስኪያጁ አብራርተዋል። ጣቢያው 420 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የመስጠት አቅም ቢኖረውም እየሰጠ የሚገኘው ከ140 ሜጋ ዋት ስለማይበልጥ ለኃይል ጠያቂ ደንበኞች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችለው አቅም እንዳለው ኃላፊው ተናግረዋል። የሀዋሳ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ ተወካይ ወ/ሪት ቤዛዊት ብርሃኑ ጣቢያው መስጠት ከሚችለው 62 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት አቅም ውስጥ እየሰጠ የሚገኘው እስከ 38 ሜጋ ዋት ኃይል ብቻ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ተወካይዋ ገለጻ ጣቢያው ጣቢያው በ 132 ኪሎ ቮልት ኃይል ተቀብሎ በ15 ኪሎ ቮልት ባሉት ስምንት ወጪ መስመሮች ለሀዋሳ ከተማና በዙሪያው ለሚገኙ የዱቄት ፋብሪካዎች ኃይል እየሰጠ ይገኛል፡፡ በ33 ኪሎ ቮልት ባሉት ሁለት ወጪ መስመሮች ደግሞ በሀዋሳ ዙሪያ እስከ 110 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ለሚገኙ የወረዳ ከተሞች ኃይል እየሰጠ ይገኛል ብለዋል። ጣቢያው በአሁኑ ወቅት ባለው አቅም አገልግሎት ፈልገው ለሚመጡ ተጨማሪ ደንበኞች ኃይል ለመስጠት ዝግጁ መሆኑንም ተወካይዋ ጠቁመዋል። የሀዋሳ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ በ1970ዎቹ መጀመሪያ በዲዝል ጀነሬተር ኃይል መስጠት የጀመረና በተለያዩ ጊዚያት በተደረጉለት የማስፋፊያ ሥራዎች አቅሙን ያሳደገ ጣቢያ ሲሆን የሀዋሳ ቁጥር ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ደግሞ ሐምሌ 2011 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረ ጣቢያ ነው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 23 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከሱዳኑ አል ሂላል ጋር አቻ ተለያየ ………///……… የኢትዮ - ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ከሱዳኑ አል ሂላል ጋር ባደረገው የወዳጅነት ጨዋታ ሁለት አቻ ተለያይቷል። ጨዋታው በተጀመረ አምስተኛው ደቂቃ አል ሂላል በፍጹም ቅጣት ምት ጎል አስቆጥሮ መምራት የቻለ ቢሆንም በመጀመሪያው አጋማሽ መገባደጃ ሰዓት ላይ ናትናኤል ሰለሞን ለኢትዮ ኤሌክትሪክ የአቻነቷን ጎል አስቆጥሯል። በመጀመሪያዎቹ 15 ደቂቃዎች በኳስ ቁጥጥር እና በተደጋጋሚ የተቃራኒ ቡድን የግብ ክልል በመድረስ አል ሂላል ጫና ማድረግ የቻለ ሲሆን ኢትዮ ኤሌክትሪክ በበኩሉ በአጭር እና ፈጣን የኳስ ቅብብል ወደ ጨዋታው በመመለስ የበላይነት አሳይቷል። በሁለተኛው አጋማሽ የተጫዋች ቅያሬ አድርጎ የገባው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ይበልጥ ጨዋታውን በመቆጣጠር በአጥቂው አቤል ሀብታሙ አማካኝነት ሁለተኛውን ጎል ማስቆጠር ችሏል። ይሁንና ጨዋታው ሊጠናቀቅ ስምንት ደቂቃዎች ሲቀሩት አል ሂላል አቻ ለመሆን ጫና አድርጎ በመጫወቱ ጥረቱ ሰምሮ በ85ኛው ደቂቃ የአቻነት ጎል አስቆጥሯል። ከኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባለፈው ዓመት የወረደው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በዚህ የውድድር ዓመት በከፍተኛ ሊግ ተሳትፎ እንደገና ወደ ሊጉ ለመመለስ ጠንካራ ልምምድ በማድረግ ላይ ይገኛል። የሱዳኑ አል ሂላል በበኩሉ በቀጣይ ላለበት ኢንተርናሽናል ጨዋታ በአዲስ አበባ ዝግጅት በማድረግ ላይ ነው። በኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫ ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በመጪው እሁድ ጥቅምት 25 ቀን 2016 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ከአዲስ አበባ እግር ኳስ ቡድን ጋር የሚጫወት ይሆናል። በተመሳሳይ የሴቶች ፕሪሜርሊግ ህዳር 16 ቀን 2016 ዓ.ም የሚጀመር ሲሆን በዚህ ዓመት ለሻምፒዮናነት የሚወዳደረው የኢትዮ ኤሌክትሪክ ሴቶች እግር ኳስ ቡድን የቅድመ ዝግጅት ልምምዱን ጀምሯል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2