en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 533 subscribers, ranking 8 368 in the Technologies & Applications category and 2 174 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 533 subscribers.

According to the latest data from 30 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 10 over the last 30 days and by -6 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 24.86%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.87% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 862 views. Within the first day, a publication typically gains 2 620 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 01 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 533
Subscribers
-624 hours
-207 days
+1030 days
Posts Archive
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በዌብሳይት ኤክስፐርት 2ኛ እና ኮሙዩኒኬሽን ኦፊሰር 3ኛ የሥራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መጋቢት 2 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች በሙሉ ህዳር 03 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው በተቋሙ ዋና መ/ቤት የማሰልጠኛ አዳራሽ የጽሑፍ ፈተና ስለሚሰጥ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈ        ........///........ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን የአዲስ አበባ ከተማ እግር ኳስ ቡድንን በማሸነፍ ቀጣዩን ዙር ተቀላቅሏል።                 ጥቅምት 25 ቀን 2016 ዓ.ም. በአበበ ቢቄላ ስቴዲየም በተካሄደው የኢትዮጵያ የጥሎ ማለፍ ዋንጫ የእግር ኳስ ውድድር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የአዲስ አበባ አቻውን አንድ ለባዶ በመርታት ነው ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍ የቻለው።                                              ለክለቡ ብቸኛዋን የማሸነፊያ  ጎል በ22ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠረው የአማካይ ክፍል ተጫዋቹ ቢኒያም ካሳሁን ነው።     በጨዋታው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በኳስ ቁጥጥር እና በፍጥነት በማጥቃት  በተጋጣሚው ላይ የበላይነት መውሰድ ችሏል።                     በ75ኛው ደቂቃ በሰራው ጥፋት የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ግብ ጠባቂ በሽር ደሊል በቀጥታ በቀይ ካርድ ከሜዳ በመሰናበቱ ክለቡ ቀሪዎቹን 15  ደቂቃዎች በ10 ተጫዋቾች ለመጫወት ተገዷል።                       የአዲስ አበባ ከተማ እግር ኳስ ክለብ በበኩሉ በመከላከል እና መልሶ በማጥቃት ጨዋታውን ለመቆጣጠር ቢሞክርም ከሽንፈት ሳይድን ቀርቷል።                                   የመጀመሪያውን ዙር የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫ በድል ያጠናቀቀው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በቀጣይ በሚከናወን የዕጣ አወጣጥ ከኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ ክለብ ጋር የሚጫወት ይሆናል።                                              በዚህ የውድድር ዓመት ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እንደገና ለመመለስ ብርቱ ፉክክር የሚጠብቀው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የመጀመሪያ መርሀ ግብሩን ህዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት በአበበ ቢቄላ ስቴዲየም ከሀላባ ከተማ ጋር የሚያከናውን ይሆናል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ክለባቸውን እንዲያበረታቱ የክለቡ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሲሳይ ለማ ጥሪ አቅርበዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሰከረም 08 ቀን 2016 ዓ.ም በአውቶ ሜካኒክ 2ኛ፣ አውቶ ሜካኒክ 1ኛ፣ አውቶ ኤሌክትሪሽያን 3ኛ፣ አውቶ ኤሌክትሪሽያን 2ኛ፣ አውቶ ኤሌክትሪሽያን 1ኛ፣ አውቶ ቦዲ 2ኛ የስራ መደቦች ስራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በዚህ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች ጥቅምት 29 ቀን 2016 ዓ.ም ከጥዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልፅ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው በተቋሙ ዋናው መ/ቤት የማሰልጠኛ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና ስለሚሰጥ ለፈተናው እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

photo content
+3

የማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ተጨማሪ የኃይል ጥያቄ የማስተናገድ አቅም አላቸው ………///…….. የሀዋሳ ቁጥር አንድና ቁጥር ሁለት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል የሚፈልጉ ደንበኞችን ማስተናገድ የሚያስችል ትልቅ አቅም እንዳለቸው የጣቢያዎቹ ኃላፊዎች አስታወቁ። የሀዋሳ ቁጥር ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ዳንኤል አንጀሎ እንደገለጹት ባለ 230 ኪሎ ቮልት አቅም ያለው የማከፋፈያ ጣቢያው ሃያ ባለ 33 እና 8 ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡ ይሁንና ዝግጁ ከተደረጉት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ውስጥ ሦስቱ እንዲሁም ከባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ውስጥ ደግሞ አምስቱ መስመሮች ብቻ ለሀዋሳ ከተማ፣ ለሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክና በዙሪያው ለሚገኙ ፋብሪካዎች ኃይል እየሰጡ እንደሚገኙ ሥራ አስኪያጁ አብራርተዋል። ጣቢያው 420 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የመስጠት አቅም ቢኖረውም እየሰጠ የሚገኘው ከ140 ሜጋ ዋት ስለማይበልጥ ለኃይል ጠያቂ ደንበኞች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችለው አቅም እንዳለው ኃላፊው ተናግረዋል። የሀዋሳ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ ተወካይ ወ/ሪት ቤዛዊት ብርሃኑ ጣቢያው መስጠት ከሚችለው 62 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት አቅም ውስጥ እየሰጠ የሚገኘው እስከ 38 ሜጋ ዋት ኃይል ብቻ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ተወካይዋ ገለጻ ጣቢያው ጣቢያው በ 132 ኪሎ ቮልት ኃይል ተቀብሎ በ15 ኪሎ ቮልት ባሉት ስምንት ወጪ መስመሮች ለሀዋሳ ከተማና በዙሪያው ለሚገኙ የዱቄት ፋብሪካዎች ኃይል እየሰጠ ይገኛል፡፡ በ33 ኪሎ ቮልት ባሉት ሁለት ወጪ መስመሮች ደግሞ በሀዋሳ ዙሪያ እስከ 110 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ለሚገኙ የወረዳ ከተሞች ኃይል እየሰጠ ይገኛል ብለዋል። ጣቢያው በአሁኑ ወቅት ባለው አቅም አገልግሎት ፈልገው ለሚመጡ ተጨማሪ ደንበኞች ኃይል ለመስጠት ዝግጁ መሆኑንም ተወካይዋ ጠቁመዋል። የሀዋሳ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ በ1970ዎቹ መጀመሪያ በዲዝል ጀነሬተር ኃይል መስጠት የጀመረና በተለያዩ ጊዚያት በተደረጉለት የማስፋፊያ ሥራዎች አቅሙን ያሳደገ ጣቢያ ሲሆን የሀዋሳ ቁጥር ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ደግሞ ሐምሌ 2011 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረ ጣቢያ ነው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 23 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከሱዳኑ አል ሂላል ጋር አቻ ተለያየ ………///……… የኢትዮ - ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ከሱዳኑ አል ሂላል ጋር ባደረገው የወዳጅነት ጨዋታ ሁለት አቻ ተለያይቷል። ጨዋታው በተጀመረ አምስተኛው ደቂቃ አል ሂላል በፍጹም ቅጣት ምት ጎል አስቆጥሮ መምራት የቻለ ቢሆንም በመጀመሪያው አጋማሽ መገባደጃ ሰዓት ላይ ናትናኤል ሰለሞን ለኢትዮ ኤሌክትሪክ የአቻነቷን ጎል አስቆጥሯል። በመጀመሪያዎቹ 15 ደቂቃዎች በኳስ ቁጥጥር እና በተደጋጋሚ የተቃራኒ ቡድን የግብ ክልል በመድረስ አል ሂላል ጫና ማድረግ የቻለ ሲሆን ኢትዮ ኤሌክትሪክ በበኩሉ በአጭር እና ፈጣን የኳስ ቅብብል ወደ ጨዋታው በመመለስ የበላይነት አሳይቷል። በሁለተኛው አጋማሽ የተጫዋች ቅያሬ አድርጎ የገባው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ይበልጥ ጨዋታውን በመቆጣጠር በአጥቂው አቤል ሀብታሙ አማካኝነት ሁለተኛውን ጎል ማስቆጠር ችሏል። ይሁንና ጨዋታው ሊጠናቀቅ ስምንት ደቂቃዎች ሲቀሩት አል ሂላል አቻ ለመሆን ጫና አድርጎ በመጫወቱ ጥረቱ ሰምሮ በ85ኛው ደቂቃ የአቻነት ጎል አስቆጥሯል። ከኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባለፈው ዓመት የወረደው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በዚህ የውድድር ዓመት በከፍተኛ ሊግ ተሳትፎ እንደገና ወደ ሊጉ ለመመለስ ጠንካራ ልምምድ በማድረግ ላይ ይገኛል። የሱዳኑ አል ሂላል በበኩሉ በቀጣይ ላለበት ኢንተርናሽናል ጨዋታ በአዲስ አበባ ዝግጅት በማድረግ ላይ ነው። በኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫ ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በመጪው እሁድ ጥቅምት 25 ቀን 2016 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ከአዲስ አበባ እግር ኳስ ቡድን ጋር የሚጫወት ይሆናል። በተመሳሳይ የሴቶች ፕሪሜርሊግ ህዳር 16 ቀን 2016 ዓ.ም የሚጀመር ሲሆን በዚህ ዓመት ለሻምፒዮናነት የሚወዳደረው የኢትዮ ኤሌክትሪክ ሴቶች እግር ኳስ ቡድን የቅድመ ዝግጅት ልምምዱን ጀምሯል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2