EEP Communication
📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication
Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 518 подписчиков, занимая 8 330 место в категории Технологии и приложения и 2 175 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 518 подписчиков.
Согласно последним данным от 09 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -5, а за последние 24 часа — -12, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 28.93%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.57% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 489 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 416 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 11.
📝 Описание и контентная политика
Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
“EEP Communication”
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 10 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 10 июля | +2 | |||
| 09 июля | 0 | |||
| 08 июля | +5 | |||
| 07 июля | +1 | |||
| 06 июля | 0 | |||
| 05 июля | +1 | |||
| 04 июля | 0 | |||
| 03 июля | +1 | |||
| 02 июля | +8 | |||
| 01 июля | +4 |
| 2 | የወደፊት ዕጣ ፈንታችን በምንጠቀመው የኃይል አማራጭ ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ በCOP 32 ጉባኤ ላይ ዘላቂ መፍትሄዎችን በጋራ እንዘይዳለን፡፡
#Innovation #COP32 #GreenEnergy
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 03 ቀን 2018 ዓ.ም | 2 095 |
| 3 | ፕሮጀክቱ በግብርና ሥራችን ምርታማ እንድንሆን አስችሎናል፤
-የባንካ ቀበሌ አርሶ አደሮች
.....///.....
የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ያከናወናቸው የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች በግብርና ሥራቸው ምርታማ እንዲሆኑ እንዳስቻላቸው በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳ የባንካ ቀበሌ አርሶ አደሮች ገለጹ።
የአካባቢው ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ደነቀ ደስታ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ ከመጀመሩ በፊት በአካባቢው የመንገድን መሰረተ-ልማት ችግር የነበረ በመሆኑ ነዋሪው እርስ በእርስ ለመገናኘትና አካባቢውን አልምቶ ወደ ገበያ ለማውጣት አስቸጋሪ ነበር።
በተለይም በኦሞ ወንዝ ላይ ድልድይ ባለመኖሩ የኮንታንና የጎፋ ሕዝቦችን ከመለየቱም በላይ ታላቅ ወንድማቸውን ጨምሮ በርካታ ሠዎች በውኃ ሙላት ተወስደው ሕይወታቸው ማለፉን አስታውሰዋል።
የኮይሻ ፕሮጀክት በኦሞ ወንዝ ላይ ሁለቱን ሕዝቦች የሚያገናኝ ድልድይ እና መንገድ በመስራት የአካባቢው ማህበረሰብ ከምርቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻሉን ጠቁመዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=ፕሮጀክቱ-በግብርና-ሥራችን-ምርታማ-እን&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 02 ቀን 2018 ዓ.ም | 2 798 |
| 4 | የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ በፍጥነት እየተከናወነ ነው፤
….///….
የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ ሥራ በፍጥነትና በጥራት እየተከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮጀክቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡
ምክትል ሥራ አስኪያጁ ኢንጂነር አባይነህ ጌትነት እንደገለጹት የኃይል ማመንጫ ግድቡ ከባህር ወለል በላይ 179 ሜትር ቁመት እና 2 ነጥብ 4 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውኃ የመያዝ አቅም እንዲኖረው ሆኖ በፍጥነት እየተገነባ ይገኛል።
ቀደም ባለው ጊዜ በፋይናንስ እጥረት ምክንያት የግንባታ መዘግየቶች አጋጥመውት የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ መንግስት ቀጥተኛ የፋይናንስ ድጋፍ በማድረጉ እና ተቋማዊ የክፍያ አፈጻጸሞች በመሻሻላቸው ያለ ምንም የፋይናንስ ችግር ግንባታው እየተፋጠነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በግድቡ የተለያዩ አካላት ላይ የሚከናወኑ የግንባታ ሥራዎች በመርኃ ግብራቸው መሰረት እየሄዱ ይገኛሉ ያሉት ኢንጂነር አባይነህ ከውጭ የሚመጡ አስፈላጊ ግብዓቶችም ያለምንም መቆራረጥ ወደ ሣይቱ እየገቡ ሥለመሆኑ አብራርተዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የፕሮጀክቱ-የግንባታ-ሥራ-በፍጥነት-እየተ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 02 ቀን 2018 ዓ.ም | 2 874 |
| 5 | ተቋሙ በቢሾፍቱ ከተማ የሚያስገነባውን የስልጠና ማዕከል ፕሮጀክት ለመጀመር የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ
...…///…....
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቢሾፍቱ ከተማ የሚያስገነባውን የስልጠና ማዕከል እና የአቅም ግንባታ ፕሮጀክት ሥራን ለመጀመር የሚያስችሉ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን የፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አቶ እንዳለ የሺጥላ ገለጹ።
አቶ እንዳለ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ የተቋሙን የሰው ሀብት ሥራ አመራርና የስልጠና አቅርቦት በማዘመን እንዲሁም በዘመናዊ መሠረተ ልማቶችና ቴክኖሎጂዎች የተሟላ የማሰልጠኛ ማዕከል በመገንባት ተቋማዊ አቅምን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመ ነው።
ፕሮጀክቱ በተቋሙ በብቃት ላይ የተመሠረተ የሰው ሀብት ሥራ አመራር ሥርዓት ለመዘርጋት፣ በሁሉም የሥራ ክፍሎች የሥርዓተ-ፆታ አካቶን ለማዳበር እንዲሁም የማዕከሉን አገልግሎት በኃይል ዘርፉ ለተሰማሩ የሀገር ውስጥና የውጭ አካላት ክፍት በማድረግ በኢትዮጵያና በቀጣናው ተመራጭ ለመሆን ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወትም ሥራ አስኪያጅ ገልጸዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-በቢሾፍቱ-ከተማ-የሚያስገነባውን-የ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ-ገጽ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 01 ቀን 2018 ዓ.ም | 3 152 |
| 6 | ‹‹ድንበር ተሻጋሪ የኃይል ንግድን ለማሳለጥ የሚያስችሉ መሠረተ ልማቶች ተጠናቀዋል›› ኢንጂነር አሸብር ባልቻ
...////…
ድንበር ተሻጋሪ የኤሌክትሪክ ኃይል ንግድን ለማሳለጥና ቀጣናዊ ትስስሩን ለማጠናከር የሚያስችሉ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች መጠናቀቃቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የሥራ አስፈፃሚዎች ኮሚቴ ሰብሳቢ አስታወቁ፡፡
37ኛው የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የአመራር ኮሚቴ ልዩ ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡
ስብሰባው በአባል ሀገራቱ በቀረቡት የመንግሥታት እና የተቋማት የጋራ መግባቢያ ስምምነቶች እንዲሁም ተያያዥ የአስተዳደር ሰነዶች ማሻሻያ ሐሳቦች ላይ ለመምከር ያለመ ነው፡፡
በስብሰባው ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና የወቅቱ የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የሥራ አስፈፃሚዎች ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በአባል ሀገራቱ መካከል የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረትን በመቅረፍ አስተማማኝና ቀጣይነት ያለው የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል ይሰራል ብለዋል፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=ድንበር-ተሻጋሪ-የኃይል-ንግድን-ለማሳ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ-ገጽ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 01 ቀን 2018 ዓ.ም | 3 369 |
| 7 | 37ኛው የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የሥራ አስፈጻሚዎች ኮሚቴ ልዩ ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል
…///…
የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማት እርስ በርስ በማገናኘት ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ለመፍጠር የተቋቋመው የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የሥራ አስፈጻሚዎች ኮሚቴ 37ኛውን ልዩ ስብሰባ በአዲስ አበባ እያካሄደ ነው፡፡
በስብሰባው ላይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር ዶ/ር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ፣ የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ዋና ጸሐፊ ኢንጂነር ጄምስ ዋሆጎና የኮሚቴ አባላት እንዲሁም ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
ስብሰባው የሰው ኃብትና አስተዳደር ኮሚቴ እንዲሁም የሕግ ባለሙያዎች በቀደሙት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔዎች መሠረት በውስጣዊ የመንግስት እና የአገልግሎት መግባቢያ ሰነዶች ላይ ያዘጋጁትን የማሻሻያ ረቂቆች የደረሱበትን ደረጃ የሚገመግም ይሆናል፡፡
የተዘጋጁ የማሻሻያ ረቂቆች በሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ከታዩ በኋላ ሐምሌ 3 እና 4 ቀን 2018 ዓ.ም በፑሉ የወደፊት አስተዳደር እና በቀጠናዊ የኤሌክትሪክ ገበያ ሥራ ማስጀመር ላይ በሚካሄደው 22ኛው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ የሚቀርቡ ምክረ ሀሳቦችን እንደሚያዘጋጅ ይጠበቃል።
የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የሥራ አስፈጻሚዎች ኮሚቴ ሰብሳቢነትን የአባል ሀገራቱ የኢነርጂ ዘርፍ ተቋማት በየተራ የሚመሩት እንደሆነ ይታወሳል፡፡
ኢትዮጵያ የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የስትሪንግ ኮሚቴ መሪነቱን ከኬንያ በመረከብ ለቀጣይ አንድ ዓመት የምታስተዳድር ስትሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር) ደግሞ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ በመሆን ፑሉን ይመራሉ፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም | 3 276 |
| 8 | Нет текста... | 3 057 |
| 9 | ተቋሙ የቴክኒሺያኖች አቅም ለማጎልበት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፤
…….///…….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሲቪል እና ኤሌክትሮ ሜካኒካል ቴክኒሽያኖችን አቅም ቀጣይነት ባለው መልኩ ለመገንባት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ገለጸ፡፡
ተቋሙ ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከየካ ክፍለ ከተማ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ጋር በመተባበር በኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ በኮንስትራክሽን ማኔጅመንት መምሪያ ውስጥ የሚገኙ የሲቪል እና ኤሌክትሮሜካኒካል ኤሬክሽን ቴክኒሺያኖች አሰልጥኖ አስመርቋል።
የተቋሙን ዋና ሥራ አስፈፃሚ በመወከል በምረቃ ሥነ- ሥርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የሰው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ እንደተናገሩት ቴክኒሺያኖች በተግባር የተፈተነ ብቃት እንዲኖራቸው ለማድረግና አቅማቸውን ለማሳደግ ተቋሙ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፡፡
ከሀገር ውስጥ ባለፈ በውጭ ሀገራት ጭምር የተሻለ የግንባታና የኦፕሬሽን ሥራዎችን ማከናወን የሚችልበት ደረጃ ላይ እንዲደረስ ተቋሙ አቅዶ እየሰራ መሆኑንና መሰል ሥልጠናዎችም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-የቴክኒሺያኖች-አቅም-ለማጎልበት-ት&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም | 3 330 |
| 10 | #COP32
ታማኝነት፡- "በግልጽነትና በሃቀኝነት መስራት!" የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለአረንጓዴ ልማትና ለኮፕ 32 የአየር ንብረት ማስተካከያ (Climate Adaptation) የሚውሉ ማናቸውንም ሀብቶችና ፋይናንሶች በግልጽነትና በሃቀኝነት ለታለመላቸው ዓላማ በማዋል ኃላፊነቱን በታማኝነት ይወጣል። ⚖️💚 #COP32 #ታማኝነት #ግልጽነት #EEP
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም | 3 848 |
| 11 | በሪጅኑ የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነትን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፤
.....///....
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ደቡብ ሁለት ሪጅን ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት ለማስቀጠል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን የሪጅኑ ዳይሬክተር ገለፁ።
ዳይሬክተሩ አቶ ምትኩ ታዬ እንደገለፁት ሪጅኑ በስምንት ማከፋፈያ ጣቢያዎችና 1 ሺህ 178 ኪሎ ሜትር በሚሸፍኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ለኢትዮ-ኬኒያ ኮንቨርተር ጣቢያ ጨምሮ ለደቡባዊ የኢትዮጵያ ክፍል አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ ይገኛል።
የአካባቢው የኃይል ፍላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን ከግምት በማስገባት በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የማዘመንና የአቅም ማሳደግ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=በሪጅኑ-የኃይል-አቅርቦት-አስተማማኝነ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም | 3 795 |
| 12 | ተቋሙ ለተለያዩ ተቋማት የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል
....///.....
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ ዘርፎች ለመንግሥታዊና መንግሥታዊ ላልሆኑ ተቋማት የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን መስጠት መጀመሩን በተቋሙ የኢትዮ ፓወር አካዳሚ አስታወቀ፡፡
ተቋሙ ላለፉት አምስት ቀናት "በኤሌክትሪካል ፓወር ሲስተም ኦፕሬሽን፣ ጥገናና ፕሮቴክሽን" ጉዳዮች ላይ ለንብ ኢነተርናሽናል ባንክ የኤሌክትሪክ ሲስተም ኦፕሬሽንና ጥገና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጥቷል፡፡
የኢትዮ ፓወር አካዳሚ ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) በስልጠናው ማጠናቀቂያ ወቅት እንደተናገሩት የተቋሙ አካዳሚ በአቅም ግንባታ ሥራዎች የረጅም ጊዜ ልምድ አለው በዚህም በኃይል ዘርፉ በርካታ ባለሙያዎችን ከማፍራቱም ባሸገር ለሌሎች ተቋማትም የተለያዪ ስልጠናዎችን ለመስጠት መብቃቱን ገልፀዋል ።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-ለተለያዩ-ተቋማት-የአቅም-ግንባታ-ስ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም | 5 779 |
| 13 | የኮንቨርተር ጣቢያው የተቋሙን ርዕይ ማሳካት በሚያስችል ቁመና ላይ ይገኛል፤
....///.....
የኢትዮ ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን የያዘውን ርዕይ ለማሳካት በሚያስችል አስተማማኝ ቁመና ላይ እንደሚገኝ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ።
ሥራ አስኪያጁ አቶ ሀብታሙ ግርማ እንደገለፁት ከወላይታ ሶዶ ከተማ በ7 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ጣቢያው እስከ ኬኒያ የተዘረጋውን 1 ሺ 45 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመር በመጠቀም 2 ሺህ ሜጋ ዋት ኃይል ለጎረቤት ሀገራት የማስተላለፍ አቅም ይዞ 2014 ዓ.ም ላይ ወደ ኦፕሬሽን ገብቷል።
ጣቢያው የተገነባበት የቴክኖሎጅ ዓይነት የኤሌክትሪክ ፍሰቱ ሳይወዛወዝ ወደ አንድ አቅጣጫ ብቻ ቀጥ ብሎ የሚጓዝበት ቀጥተኛ የኤሌክትሪክ ዥረት (Direct Current - DC) መሆኑ ተጨማሪ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችንና የማከፋፈያ ጣቢያዎችን ግንባታ በማስቀረት ከፍተኛ ወጪ እንዲድን ማስቻሉን ጠቁመዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የኮንቨርተር-ጣቢያው-የተቋሙን-ርዕይ-ማ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም | 5 664 |
| 14 | ማከፋፈያ ጣቢያው ለደቡባዊ ግሪድ ዋነኛ የኃይል ማዕከል በመሆን እያገለገለ ነው፤
....///....
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወላይታ ሶዶ ሁለት ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ለአካባቢውና ለደቡባዊ ግሪድ ዋነኛ የኃይል ማዕከል በመሆን እያገለገለ እንደሚገኝ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ።
ሥራ አስኪያጁ አቶ በላይነህ ህንዳሞ እንደገለጹት ጣቢያው ከጊቤ ሦስት የሚመነጨውን 1 ሺህ 870 ሜጋ ዋት ኃይል የሚቀበል ሲሆን ከግልገል ጊቤ ሁለት እንዲሁም በይርጋለም ቁጥር ሁለት በኩል ደግሞ ከገናሌ ዳዋ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነው።
ከኃይል ማመንጫዎች ከሚቀበለው ኃይል ውስጥ 60 ከመቶ የሚሆነውን በቀጥታ ለገላን ማከፋፈያ ጣቢያ እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
በባለ 132 ኪሎ ቮልት ለሀላባ እና ለወላይታ ቁጥር አንድ፣ በባለ 230 ኪሎ ቮልት ለአዲሱ የአርባ ምንጭ ቁጥር ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም በ33/15 ኪሎ ቮልቶች ለዳታ ማይኒንግ ድርጅቶችና ለኢትዮጵያ ኤእሌክትሪክ አገልግሎት የአካባቢው ዲስትሪክት እንደሚያቀርብም ጠቁመዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=ማከፋፈያ-ጣቢያው-ለደቡባዊ-ግሪድ-ዋነኛ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም | 4 187 |
| 15 | የተሰረዘ ማስታወቂያ
.......///......
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም | 3 967 |
| 16 | የተቋሙን ስትራቴጂክ ዕቅድና አፈፃፀም ለማስተዳደር የሚያስችል መተግበሪያ ወደ ሥራ ለማስገባት ታቅዷል
…///…
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስትራቴጂክ ዕቅድና አፈፃፀምን ለመከታተልና ለማስተዳደር የሚያስችል “ኢ.ኢ.ፒ ቢ.ኤስ.ሲ” ተሰኘ የድረ-ገፅ መተግበሪያ በሥራ ላይ ለማዋል እየሰራ መሆኑን የዲጅታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡
የዘርፉ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ጽዮን በቀለ እንደተናገሩት መተግበሪያው የተቋሙን የዕቅድ አፈጻጸም ምዘናዎች በቴክኖሎጂ እንዲታገዙ በማድረግ የቆየውን ወረቀት ተኮር አሠራር ሙሉ በሙሉ የሚያስቀር ነው።
መተግበሪያው የተቋሙን ስትራቴጂካዊ ግቦች፣ የሥራ ክፍሎችንና የሠራተኞችን የሥራ አፈፃፀም ደረጃ በዲጂታል ሥርዓት ለመከታተልና ለመገምገም ከፍተኛ እገዛ ያደርጋልም ብለዋል።
የአሠራር ሥርዓቱ ከዚህ በፊት የነበሩትን የወረቀትና የተበታተኑ የሪፖርት ማቅረቢያ መንገዶችን በማስቀረት ሥራዎችን በጥራት፣ በፍጥነትና ያለሰው ንክኪ ለመከታተል እንደሚያስችልም ነው ያብራሩት፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-ስትራቴጂክ-ዕቅድና-አፈፃፀም-ለ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም | 4 865 |
| 17 | የኃይል መሠረተ ልማቶች እንዲጠበቁ የአካባቢው ማህበረሰብ ሚናውን መወጣት አለበት፤
.....///.....
በአካባቢው የሚገኙ የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶችን በመጠበቅ በኩል ማህበረሰቡ ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ገለፁ።
ከንቲባዋ ወይዘሮ እታገኝ ኃይለማሪያም እንደገለፁት በወላይታ ሶዶ ከተማና ዙሪያዋ የኢትዮ ኬኒያ ኮንቨርተር ጣቢያን ጨምሮ ሌሎች ሁለት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችና የማስተላለፊያ መስመሮች ይገኛሉ።
ሁለቱ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የከተማዋንና የአካባቢውን የኃይል ፍላጎት በአስተማማኝ መልኩ በማሟላት በኩል ሚናቸው የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-መሠረተ-ልማቶች-እንዲጠበቁ-የአካ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም | 5 548 |
| 18 | ማብቃት፡- የሰው ኃይል አቅምን መገንባትና ማበረታታት
….///….
በታዳሽ ኃይልና በአረንጓዴ ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተሰማሩ ምሁራኖቻችንን እና ሠራተኞቻችንን አቅም ማሳደግ፣ ለኮፕ 32 ስኬት እና ለአየር ንብረት መቋቋም ሽግግር መሠረት ነው። አቅምን በማልማት የአየር ንብረት ፈተናዎችን እናሸንፋለን።
#COP32 #ማብቃት #የሰውኃይልአቅም #EEP
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም | 5 693 |
| 19 | አስተማማኝነት፡- "በማንኛውም ጊዜ የሚታመን አገልግሎት መስጠት!"
….///….
ተለዋዋጭ የሆነውን የአየር ንብረት ሁኔታ መቋቋም የሚችል እና በማንኛውም ወቅቶች የማይቆራረጥ የንጹሕ ኃይል አቅርቦት ለሕዝባችን ማድረስ፣ ተቋማችን በኮፕ 32 ጉባዔ ላይ የሚያስተጋባውና በተግባር እያረጋገጠው የሚገኘው ትልቁ ስኬቱ ነው።
#COP32 #አስተማማኝነት #የሚታመንአገልግሎት #EEP
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም | 5 207 |
| 20 | የተቋማችን አንዱ ትልቅ እሴት ዘላቂነት ነው
….///….
"ለአሁኑም ሆነ ለወደፊቱ ትውልድ የሚተርፍ ሥራ መሥራት!" የኮፕ 32 (COP32) ጉባዔ ዋና ዓላማም መጪውን ትውልድ ከአየር ንብረት አደጋ መታደግ በመሆኑ፣ ይህ ተቋማዊ እሴታችን ከጉባዔው ዓለም አቀፋዊ ግብ ጋር አብሮ ይጓዛል።
#COP32 #ዘላቂነት #ለቀጣይትውልድ #EEP
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 19 ቀን 20 | 4 979 |
