ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 553 подписчиков, занимая 8 395 место в категории Технологии и приложения и 2 164 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 553 подписчиков.

Согласно последним данным от 22 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 5, а за последние 24 часа — 1, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.99%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.38% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 043 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 393 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 9.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 23 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 553
Подписчики
+124 часа
+47 дней
+530 день
Архив постов
የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የግንባታ አፈፃፀም ከ96 በመቶ በላይ ደርሷል ...///.... ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ኤሌክትሪክ ለማቅረብ እየተገነባ የሚገኘው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አጠቃላይ ግንባታ 96 ነጥብ 5 በመቶ መድረሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት 1 ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። በተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተመራ ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እየተገነባ የሚገኘውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ያለበትን የግንባታ ደረጃ በመስክ በመገኘት ገምግሟል። የመስክ ግምገማው ፕሮጀክቱ የደረሰበትን የመጨረሻ ምዕራፍ የግንባታ አፈፃፀም እና በግንባታ ሂደቱ ላይ እያጋጠሙ የሚገኙ የዕቃ አቅርቦት ተግዳሮቶች ዙሪያ ተወያይቶ መፍትሄ ለመስጠት ያለመ ነው። በዚሁ የመስክ ጉብኝት ወቅት ለከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድኑ ገለፃ ያደረጉት በኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት 1 ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ተሾመ እንደተናገሩት በማከፋፈያ ጣቢያው ውስጥ እየተከናወኑ የሚገኙ የፍተሻና የማስተካከያ ሥራዎች የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሰዋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ከሚኖሩት አራት ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች መካከል 50 ሜጋ ዋት ኃይል የመጫን አቅም ያለው አንዱ ትራንስፎርመር በተንቀሳቃሽ ስዊችጊር አማካኝነት አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል። በማከፋፈያ ጣቢያው ውጫዊ ክፍል የተተከሉ መሣሪያዎችን የመፈተሽ ሥራ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን በመጥቀስ ሁለተኛውን የፍተሻ ሥራ ለማከናወን የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል። አንዳንድ የመቆጣጠሪያ ኬብሎች እና የኮሙዩኒኬሽን መሣሪያዎች በዕቃ አቅራቢ ኩባንያው በኩል ባለመቅረባቸው የተነሳ የሥራ መዘግየቶች እያጋጠሙ መሆኑንም ነው ያብራሩት። በአሁኑ ወቅትም የመቆጣጠሪያ ኬብሎችን እጥረት ለመቅረፍ ከሌሎች የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በውሰት የማምጣት ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስረድተዋል። የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አማካሪ አቶ ደመላሽ ሙሉ እንደገለፁት በኢኮኖሚ ዞኑ ውስጥ የሚገኙ ፋብሪካዎች በፍጥነት ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ ፕሮጀክቱን በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ማጠናቀቅ ይገባል። በማከፋፈያ ጣቢያው ያለውን ከፍተኛ የውሃ አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ከውሃ ምንጩ እስከ ጣቢያው ድረስ የ3 ኪሎ ሜትር የውሃ ቧንቧ መስመር ለመዘርጋት ዕቅድ መያዙን ተናግረዋል። ዕቃ አቅራቢ ኩባንያው የቀሩትን ዕቃዎች በአስቸኳይ እንዲያቀርብና የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት እንዲጀምር የተቋሙ የሥራ አመራር ቡድን ጥብቅ መመሪያም አስተላልፏል። የኃይል ማከፋፈያው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ባለስልጣን ለሚፈልገው አገልግሎት ኃይል የሚያቀርቡ 14 ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንዲኖሩት ተደርጎ እየተገነባ የሚገኝ ጣቢያ ነው፡፡ የፕሮጀክቱ የግንባታ እና የማማከር ሥራ በተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ዘርፍ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን ለግንባታ ሥራው የሚያስፈልገው ወጪም በገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ባለስልጣን እየተሸፈነ ይገኛል፡፡ ‎ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም

ፕሮጀክቱን በተያዘለት የጊዜ ገደብ አጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ ጥረት ይደረጋል ‎…....///....... ‎ የገንደ አርባ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን በተያዘለት የጊዜ ገደብ አጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ ጥረት እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ ‎በተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተመራ ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን ለቡልቡላ የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እየተገነባ የሚገኘውን የገንዳርባ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ያለበትን የግንባታ ደረጃ በመስክ በመገኘት ገምግሟል። የመስክ ግምገማው ፕሮጀክቱ የደረሰበትን የግንባታ አፈፃፀም እና በግንባታ ሂደቱ ላይ በሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች ዙሪያ ተወያይቶ መፍትሄ ለመስጠት ያለመ ነው። ‎በመስክ ግምገማው ወቅት በተቋሙ የኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ እንደገለፁት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እና ወጪ የማይጠናቀቁት በወቅቱ የክትትልና ድጋፍ ሥራዎች በትኩረት ስለማይሰሩ ነው። ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የገለፁት ኢንጂነር ውድነህ ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች አቅርቦት ችግሮች በመፈታታቸው ዕቃዎቹ በአሁኑ ወቅት ወደ ጣቢያው እየገቡ መሆኑን አብራርተዋል። ከዚህ በኋላ ተከታታይ የሆነ የዕቃዎች አቅርቦት የሚኖር ከሆነ ፕሮጀክቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ማድረግ እንደሚቻል አረጋግጠዋል። በአሁኑ ወቅት በፕሮጀክቱ የግንባታ ሂደት ላይ ማነቆ ሆኖ እየተስተዋለ ያለውን የነዳጅ አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ ከአካባቢው መስተዳድር አካላት ጋር በቅርበት በመተባበር መፍትሔ ለመስጠት እንደሚሰራም አስታውቀዋል። ፕሮጀክቶችን በታቀደላቸው የጊዜ ገደብና ወጪ ለማጠናቀቅ ከተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጀምሮ ያሉ ከፍተኛ አመራሮች በሪፖርት ብቻ ሳይወሰኑ በመስክ ተገኝተው መገምገማቸው ለሥራው መፋጠን ከፍተኛ መነቃቃትን እንደሚፈጥር ተናግረዋል። ‎እንደ ኢንጂነር ውድነህ ገለፃ በየጊዜው በሥራ መሪዎች የሚደረጉ የመስክ ምልከታዎች በፕሮጀክት ግንባታዎች ላይ ለሚስተዋሉ ችግሮች አፋጣኝ ውሳኔዎችን ለማሳለፍ ይረዳል። ‎ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ደርሶበት የነበረው መስመር ተጠግኖ ኃይል መስጠት ጀምሯል ....…///….... ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የመልካ ዋከና - ራይቱ - ጎዴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር በጊዜያዊነት ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ 1 ሪጅን አስታወቀ።   የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ንጉሴ እንደገለጹት ሚያዚያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ባሌ ዞን ጊኒር ወረዳ "ኦዳ" በተባለ ልዩ ቦታ ላይ ከባድ ንፋስ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለ ዝናብ በመስመሩ ላይ  ስድስት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችን እንዲወድቁ አድርጎ ነበር።   በዚህ የተነሳ ከመስመሩ ኃይል ሲያገኙ የነበሩት የጎዴ እና የቀብሪደሃር ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ከጣቢያዎቹ ኃይል ሲያገኙ በነበሩ አካባቢዎች ሙሉ በሙሉ ኃይል ተቋርጦ መቆየቱን አስታውሰዋል።   የወደቁትን ስድስት ከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ሙሉ በሙሉ ጠግኖ ወደ መደበኛ አገልግሎት ለማስገባት ረጅም ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም የኅብረተሰቡን እንግልት ለመቀነስ እና ለአካባቢው አስቸኳይ ኃይል ለመስጠት ጊዜያዊ የአማራጭ ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውንም ገልጸዋል፡፡    በዚህም አምስት ባለ 132 ኪሎ ቮልት እና አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችን በመጠቀም ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች በጊዜያዊነት መልሰው ኃይል እንዲያገኙ መደረጉን ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡   የወደቁትን ታወሮችን በዘላቂነት ለመጠገን የሚደረገው ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።   በአካባቢው የተቋረጠውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ወደነበረበት እስከሚመለስ ድረስ በትዕግስት ለጠበቁ ደንበኞች እና ለሥራው እገዛ ላደረጉ አካላት ዳይሬክተሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡። 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+6

የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት ለስልጤ ዞን ሁለንተናዊ ዕድገት አዲስ ምዕራፍ ይከፍታል ...///... የወራቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ መገንባት ለስልጤ ዞን ሁለንተናዊ ዕድገት አዲስ ምዕራፍ መክፈቱን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ገለፁ። ዋና አስተዳዳሪው አቶ ዘይኔ ቢልካ በጣቢያው የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር የኃይል መሠረተ ልማቱ ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱ ለአካባቢው የኢኮኖሚ፣ የኢንዱስትሪና የማህበራዊ ልማት መፋጠን የጎላ ድርሻ ይኖረዋል። ዞኑ ሰፊ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የሚካሄድበት ከ1 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ያረፈ የኢንዱስትሪ መንደር ልማት የተጀመረበትና ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ፍላጎት ያለበት አካባቢ መሆኑን ጠቅሰዋል። ይሁን እንጂ ባለፉት ዓመታት ያጋጥም የነበረው የኃይል አቅርቦት እጥረት ችግር የአካባቢውን እምቅ የኢኮኖሚ አቅም ለመጠቀም ትልቅ ማነቆ ሆኖ መቆየቱን አስታውሰዋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱ ችግሩን በዘላቂነት ከመፍታቱም በላይ ለተጀመሩት የልማት ሥራዎችና ለአዳዲስ ኢንቨስትመንቶች አስተማማኝ ግብዓት መሆኑን አስገንዝበዋል። የወራቤ ከተማ በርካታ መጋቢ መንገዶችና የንግድ መስመሮች የሚገናኙባት ስልታዊ ቦታ መሆኗን የጠቆሙት ዋና አስተዳዳሪው አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል መገኘቱ የከተማዋንና የአካባቢውን የንግድ ትስስር ይበልጥ እንደሚያሳድገውም ነው  የገለፁት። እንደ አቶ ዘይኔ ገለፃ በዞኑ ውስጥ ለሚገኙት የጤና፣ የትምህርትና የንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እንዲሁም ለወጣቶች ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ጣቢያው ያለው ፋይዳ እጅግ የጎላ ነው። ለፕሮጀክቱ መሳካት በቁርጠኝነት ለሠሩት ለክብርት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራሮች፣ ለግንባታ ተቋራጩ የቻይናው ሲኖ ሃይድሮ ኩባንያ እና ለአማካሪው እንዲሁም ለዞኑ የሥራ ኃላፊዎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የአካባቢው ማህበረሰብና አመራር ፕሮጀክቱን ከመጀመሪያው ጀምሮ በባለቤትነት ስሜት ሲደግፉና ሲከታተሉ መቆየታቸውን ያነሱት አቶ ዘይኔ በቀጣይም ይህንን ታላቅ ሀገራዊ መሰረተ ልማት በአግባቡ በመንከባከብና በመጠበቅ ረገድ  የበኩሉን ኃላፊነት እንደሚወጣ እምነታቸውን ገልፀዋል። 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

"ጣቢያው የአንድ ትውልድ ጥያቄን የመለሰ ነው" ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል ...///... የወራቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን መገንባቱ የአንድ ትውልድ ዘመን ጥያቄን መመለስ መቻሉን የኢፌዲሪ  የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ገለፁ። ሚኒስትሯ ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል በማከፋፈያ ጣቢያው የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር የኤሌክትሪክ አቅርቦቱ የስልጤ ዞንን ቀጣይ የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና የአካባቢውን እምቅ አቅም ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑን ገልፀዋል። የኃይል መሰረተ ልማቱ የአካባቢውን ማህበረሰብ የልማት ፍላጎት ከማርካት ባለፈ የወራቤ ከተማንና አጠቃላይ የስልጤ ዞንን የንግድና የኢኮኖሚ መናኸሪያ ለማድረግ ለተያዘው ግብ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርም ነው የተናገሩት። የወራቤ ከተማ በንግድና በማህበራዊ ትስስር ረገድ ያላትን ስልታዊ ጠቀሜታ ያነሱት ወ/ሮ ሙፈሪያት ከተማዋ በርካታ መጋቢ መንገዶች የሚገናኙባትና ሰፊ የንግድ እንቅስቃሴ የሚስተናገድባት በመሆኗ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ማግኘቷ ስትራቴጂካዊ አቅሟን ይበልጥ እንደሚያጎለብተው ጠቅሰዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በሀገር ደረጃ የተከናወኑ የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማቶች የሀገሪቱን ከፍታ ያበሰሩ ብቻም ሳይሆኑ በአህጉርና በዓለም አቀፍ ደረጃ የኃይል ሚዛንን ያስተካከሉ ትልልቅ ስኬቶች መሆናቸውንም ነው የጠቀሱት። እንደ ሚኒስትሯ ገለፃ ጣቢያው የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ብቻ ሳይሆን የአካባቢውን ማህበረሰብ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ትስስር ይበልጥ የሚያጠናክርና የሚያቀናጅ ታሪካዊ መሰረት ነው። በአሁኑ ወቅት የኃይል አቅርቦቱ አስተማማኝ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በስልጤ ዞን በግሉ ዘርፍና በመንግሥት ትብብር ወደ አንድ ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የተጀመሩ የኢንዱስትሪ ልማቶች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል። ለፕሮጀክቱ ስኬት በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀን ከሌሊት በቁርጠኝነት የሠሩትን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር፣ የሥራ ተቋራጭና አማካሪ አካላትን ያደነቁት ሚኒስትሯ የአካባቢው አመራርና ማህበረሰብም ፕሮጀክቱን በባለቤትነት ስሜት በመንከባከብ ላሳዩት ቀና ትብብር ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ይህ የተቀናጀ የሥራ ባህልና የባለቤትነት መንፈስ ለሌሎች መሰል ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶችም በምሳሌነት ሊወሰድ የሚገባው ታላቅ ተሞክሮ መሆኑንም ነው ያብራሩት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

"የኤሌክትሪክ ኃይል የብልፅግና ምሰሶ ነው" ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ...///... የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሀገሪቱ የብልፅግና ጉዞ ዋነኛ ምሰሶ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገለፁ። ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የወራቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት የጣቢያው መገንባት ተቋሙ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል በመላ ሀገሪቱ ለማዳረስ ለያዘው ስትራቴጂካዊ ግብ ስኬት ትልቅ ማሳያ ነው። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ለአገልግሎት መብቃት ለአካባቢው ቀጣይ የዕድገትና የብልፅግና ጉዞ ትልቅ መደላደል እንደሚፈጥርም ነው የተናገሩት። የጣቢያው ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በይፋ ለማብሰር የተዘጋጀው የምርቃት መርሃ ግብር የተገኘውን ስኬትና ደስታ ከማህበረሰቡ ጋር በጋራ ለመካፈል መሆኑን አስረድተዋል። ተቋሙ በመላ ሀገሪቱ በርካታ የኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያና የማከፋፈያ ጣቢያዎችን እየገነባ እንደሚገኝ የገለፁት ኢንጂነር አሸብር ዘንድሮ በርካታ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃቱን አብራርተዋል። እነዚህ ግዙፍ የኃይል መሠረተ ልማቶች ተመርቀው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን ተከትሎ የሀገሪቱ የኃይል አቅርቦት አቅም በከፍተኛ ደረጃ ማደጉንም ነው የገለፁት። የወራቤ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአጭር ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ የስልጤ ዞንና የወራቤ ከተማ አመራሮች እንዲሁም ማህበረሰቡ ላደረጉት ልዩና አርአያነት ያለው ድጋፍ በተቋሙ ስም ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ከሚልን ጨምሮ የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

የወራቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት እየተከናወነ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioe
+9
የወራቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት እየተከናወነ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

የትራንፎርመር ተከላው ተጠናቆ ኃይል መስጠት ጀመረ ........///........ የበለስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን የአገልግሎት አቅም ለማሳደግና በጣቢያው ዙሪያ ለሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ሲከናወን የቆየው  የትራንስፎርመር ተከላ ሥራ ተጠናቆ በዛሬው ዕለት ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጉን የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ተወካይ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ግርማ ዘለቀ እንዳስታወቁት በጣቢያው 25 ሜጋ ቮልት አምፒር ኃይል የመሸከም አቅም ያለው አንድ ትራንፎርመር በመትከል በአካባቢው ለረጅም ጊዜ ይስተዋል የነበረውን የኃይል አቅርቦት ችግር በከፍተኛ ደረጃ ይፈታል። ትራንስፎርመሩ ወደ ሥራ መግባቱ በጣቢያው ላይ ይፈጠር የነበረውን ከፍተኛ የኃይል ጫና ከማቃለሉም ባሻገር የተረጋጋ የኤሌክትሪክ ፍሰት ለአካባቢው ማህበረሰብ ለማድረስ እንደሚያስችልም ተናግረዋል። ከዚሁ ጎን ለጎን ከሁለት ዓመት በፊት ጉዳት ደርሶበት የነበረው 400 ኪሎ ቮልትን ወደ 132 ኪሎ ቮልት የሚቀይር ባለ 125 ሜጋ ቮልት አምፒር አንድ ትራንስፎርመር በአዲስ መተካቱን ገልፀዋል። በዚህም ምክንያት የጃዊ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከአገልግሎት ውጪ ሆኖ መቆየቱን አስታውሰዋል። ማከፋፈያ ጣቢያው በ132 ኪሎ ቮልት ለበለስ ስኳር ፋብሪካ እና በአካባቢው ለሚገኙ ከተሞች ኃይል ይሰጥ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ግርማ የደረሰው ችግር በኃይል አቅርቦቱ ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሮ መቆየቱን ገልፀዋል። እንደ ተወካይ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በወቅቱ የነበረውን የኃይል እጥረት ጫና ለማቃለል ከጣቢያው ከተሰራ መስመር ላይ በመቀጠል ለአካባቢው ማህበረሰብ የኃይል አቅርቦት ለማመቻቸት ሙከራ ተደርጎ ነበር። ይሁን እንጂ የተወሰደው ጊዜያዊ መፍትሔ በመስመሮቹ ላይ ብልሽት ከተከሰተ በቀጥታ ወደ ኃይል ማመንጫ ጄኔሬተሩ በመተላለፍ ዘላቂ ጉዳት ሊያደርስ የሚችል በመሆኑ በጣቢያው ደህንነት ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኖ እንደነበር አብራርተዋል። ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት አንድ 125 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው የትራንስፎርመር ግዥ ተከናውኖ ከውጭ እንዲገባ ቢደረግም በወቅቱ በነበረው የፀጥታ ሁኔታ እና የመንገድ ችግር ምክንያት ለአምስት ወራት ያህል በሱልልታ ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲቆይ መደረጉንም ጠቅሰዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የትራንፎርመር ቅየራ ሥራው በመጠናቀቁ ላለፉት ሁለት ዓመታት ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩ አካባቢዎች ከዛሬ ጀምሮ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘት መጀመራቸውን ጠቁመዋል። በዚህም በ33 ኪሎ ቮልት የበለስ ስኳር ፋብሪካ፣ ጃዊ እና ሰሜን አቸፈር ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል እያገኙ መሆኑን ነው ያብራሩት። በአሁኑ ወቅት ለሊበን ከተማ የኃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎች በሪጅኑ በኩል እየተከናወኑ በመሆኑንም ነው ያስታወቁት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ የወራቤ ማከፋፈያ ጣቢያን ጎበኙ .......///... ... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተመራ ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን የወራቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን ጎብኝቷል። በ15 ወራት ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ የተጠናቀቀው ማከፋፈያ ጣቢያው በነገው ዕለት በይፋ ይመረቃል። በጉብኝቱ ወቅት ዋና ሥራ አስፈፃሚው እንደገለፁት የጣቢያው ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ የስልጢ ዞንና የወራቤ ከተማ አስተዳደር ያደረጉት ሁለንተናዊ ድጋፍ የሚደነቅ ነው። ዋና ሥራ አስፈፃሚው በጣቢያው ከኦፕሬሽን ሠራተኞች መኖሪያ ቤት፣ ከውሃና ከተሽከርካሪ አቅርቦት እንዲሁም ከኦፕሬሽን ሥራዎች አንፃር ያለውን እንቅስቃሴ ገምግመዋል። በማከፋፈያ ጣቢያው ዙሪያ ለሚገኙ  የአካባቢው ማህበረሰቦች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት  ጋር በቅንጅት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። የዞኑ ከፍተኛ አመራሮችም ተቋሙ ፕሮጀክቱን በተያዘለት የጊዜ ገደብ አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ በማድረጉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

ተቋሙ በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የኃይል መሠረተ-ልማት ያለውን ተሞክሮ ለአንጎላ ባለሙያዎች አጋራ ……….///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሀገሪቱ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (E-Mobility) ስትራቴጂያዊ ሽግግር ውስጥ እያከናወናቸው ያሉትን የኃይል አቅርቦትና የመሠረተ-ልማት ዝግጁነት ሥራዎች ከአንጎላ የመጡ የዘርፉ ባለሙያዎች አጋራ፡፡ በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ የኃይል ሲስተም ጥናት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙኒር ኑርሁሴን በልምድ ልውውጥ መድረኩ ላይ እንደገለጹት ተቋሙ በሀገሪቱ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ሽግግር ውስጥ የበኩሉን አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል። ሽግግሩ ሀገራችን ለነዳጅ ገቢ የምታወጣውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ለመቀነስ፣ የበለፀገውን የታዳሽ ኃይል ሀብታችንን በአግባቡ ለመጠቀም እንዲሁም የአካባቢ ብክለትን ለመከላከልና የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ ከፍተኛ ረዳት እንደሚሆን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ፣ የኃይል ማከፋፈያ መሠረተ ልማቶችን ማቀድና ማስፋፋት፣ የቴክኒክ ድጋፍ መስጠት እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መሥራት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ እንደሚገኝ ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል። ይህንን የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ፍላጎትና ቀጣይ ዕድገትን ለመደገፍም ተቋሙ አሁን ላይ ያለውን አጠቃላይ አቅምና የወደፊት ዕቅዶች አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ከፍተኛ የኃይል ሥርዓት መሐንዲስ የሆኑት አቶ ሀብታሙ አበበ በበኩላቸው የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ቋት ላይ የሚያሳድሩት ተፅዕኖ በሚል ርዕስ ጥናታዊ ማብራሪያ አቅርበዋል። ጥናቱ በሀገሪቱ በቅርቡ ይፋ የተደረገውን ብሔራዊ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ትግበራ ስትራቴጂ (2025–2030) መሠረት ያደረገ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሀብታሙ ስትራቴጂው እስከ 2030 ዓ.ም ድረስ 500 ሺህ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባትና በአዲስ አበባ የሚገነቡ 1 ሺህ 176 ጣቢያዎችን ጨምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ 2 ሺህ 230 የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን ለመገንባት የያዘውን ግብ ለማሳካት እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን በዝርዝር የሚያሳይ መሆኑን አብራርተዋል። በልምድ ልውውጥ መድረኩ ላይ የተገኙት በአንጎላ የዓለም አቀፍ የአረንጓዴ ዕድገት ኢንስቲትዩት (GGGI Angola) ተወካይ አቶ ሴሌስቲኖ ዴሎ  በበኩላቸው ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ዘርፍ ያላትን እምቅ አቅም ግልጽ የሆነ ሀገራዊ ራዕይ እና የተቀናጀ የፖሊሲ አፈፃፀም ለአንጎላ ልዑክ መሠረታዊ ልምዶችን የመቅሰም ዕድል የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ሀገር የተያዘው የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ስትራቴጂ ከከፍተኛ አመራር ጀምሮ እስከ ታችኛው የመንግስት መዋቅርና በተለያዩ ሴክተሮች መካከል በሚገባ በማቀናጀት በተግባር እየተተረጎመ መሆኑን መገንዘባቸውን ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያቀረባቸው የማስተላለፊያ የማከፋፈያ ጣቢያዎችና የወደፊት የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች መረጃዎች ተቋሙ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለመወጣት እያደረገ ያለውን ዝግጁነት የሚያሳይ መሆኑን ያወሱት አቶ ሎ ሀገራቸው አንጎላ ይህንን ስትራቴጂያዊ አሠራርና የመሠረተ-ልማት ትስስር እንደ መልካም ተሞክሮ የምትወስደው መሆኑን ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

የኤሌክትሪክ ኃይል አስደናቂና ውስብስቡ የሰከንዶች ጉዞ ⚡️🏗💡 እኛ ቤታችን ወይም ቢሮአችን ሆነን የአንድ ማብሪያ (Switch) ቁልፍ ስንጫን የምናገኘው ፈጣን ብርሃን፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜት
የኤሌክትሪክ ኃይል አስደናቂና ውስብስቡ የሰከንዶች ጉዞ ⚡️🏗💡   እኛ ቤታችን ወይም ቢሮአችን ሆነን የአንድ ማብሪያ (Switch) ቁልፍ ስንጫን የምናገኘው ፈጣን ብርሃን፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን አቋርጦ፣ በርካታ የምህንድስና፣ የሎጂስቲክስና የኦፕሬሽን ፈተናዎችን አልፎ የሚደርስ የሰከንዶች ጉዞ ውጤት ነው። ይህንን ግዙፍና ውስብስብ የኃይል ሰንሰለት (Power Value Chain) በአምስት ስልታዊ ምዕራፎች መመልከት ይቻላል፡፡   1. የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች  - የጉዞው መጀመሪያ   የኤሌክትሪክ ጉዞ የሚጀምረው እንደ ውሃ (Hydroelectric)፣ ንፋስ (Wind)፣ ወይም የከርሰ ምድር እንፋሎት (Geothermal) እምቅ ኃይልን ወደ ኤሌክትሪክ በሚቀይሩ ማመንጫ ጣቢያዎች ነው።   📌 የሚገጥመው ፈተና እነዚህ ማመንጫዎች አብዛኛውን ጊዜ የሚገነቡት ከከተሞችና ከኢንዱስትሪ ቀጣናዎች ርቀው በመሆኑ፣ ኃይሉን ወደ ተጠቃሚው ለማድረስ ረጅም ርቀት መጓዝ ግድ ይላቸዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኤሌክትሪክ-ኃይል-አስደናቂና-ውስብስቡ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም