fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 687 مشترک است و جایگاه 8 031 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 153 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 687 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 27 اوت, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 154 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 9 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 34.69% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 17.14% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 443 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 690 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 11 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 28 اوت, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 687
مشترکین
+924 ساعت
+227 روز
+15430 روز
آرشیو پست ها
የኃይል መቋረጥን ለመቀነስ የሚያስችል ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው ....///.... በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ድንገተኛ አደጋዎች በሚከሰቱበት ወቅት ፈጣን መልሶ ጥገና ለመስጠት የሚያስ
+4
የኃይል መቋረጥን ለመቀነስ የሚያስችል ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው  ....///....   በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ድንገተኛ አደጋዎች በሚከሰቱበት ወቅት ፈጣን መልሶ ጥገና ለመስጠት የሚያስችሉ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ውጤቶች በሙከራ ደረጃ ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ።              በዘርፉ የቴክኒካል ድጋፍ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አበባው ያለው እንደገለፁት በሙከራ ደረጃ ተግባራዊ የተደረጉት የአደጋ ጊዜ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች (Emergency Restoration Tower) በተለያየ ምክንያት የሚወድቁ የብረት ምሰሶዎችን በአጭር ጊዜ በመተካት የኃይል መቋረጥን በከፍተኛ ሁኔታ የሚቀንሱ ናቸው።  በተጨማሪም የብረት ምሰሶዎቹ የተጨናነቁ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን አነስተኛ የኃይል ፍሰት ወደሚገኝባቸው ለማዘዋወርና ከአገልግሎት ውጭ የነበሩትን በፍጥነት ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ለማድረግ ሚናቸው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-መቋረጥን-ለመቀነስ-የሚያስችል-ቴ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 4 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል መሠረተ ልማት ደህንነትን ለማረጋገጥ በተሰሩ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል፤ ......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሠረተ ልማት ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የአሰራር ሥርዓቶች
የኃይል መሠረተ ልማት ደህንነትን ለማረጋገጥ በተሰሩ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል፤ ......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሠረተ ልማት ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የአሰራር ሥርዓቶች በመተግበር ለውጥ መምጣቱን የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ በጽ/ቤቱ የአስተዳደራዊ ጉዳዮች ሥራ አስኪያጅ ግርማ ግዛቸው (ዶ/ር) እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ ለዋና ሥራ አሰፈጻሚ የሚቀርቡ አስተዳደራዊ ጉዳዮችን ተፈጻሚነት ለማሻሻል፣ ተቋማዊ እና የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም የፖሊሲ፣ ፕሮሰስና ለውጥ ማኔጅመንት ተግባራትን በማከናወን ስትራቴጅካዊ ግቦችን ለማሳካት በርካታ ሥራዎች ተከናውነዋል። በዚህም በበጀት ዓመቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተመረጡ 5 ሪጅኖች 1 ሺህ 411 የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን በማኅበረሰቡ ለማስጠበቅ ታቅዶ በ1 ሺህ 279 ምሰሶዎች ላይ ተፈጻሚ ማድረግ መቻሉን አብራርተዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-መሠረተ-ልማት-ደህንነትን-ለማረጋ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የተቋሙን ጥቅምና ገጽታ የሚያስጠብቁ ሥራዎችን ተከናውነዋል ………///…….. በ2018 በጀት ዓመት ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የተቋሙን ጥቅምና ገጽታ የሚያስጠብቁ የተለያ
ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የተቋሙን ጥቅምና ገጽታ የሚያስጠብቁ ሥራዎችን ተከናውነዋል ………///…….. በ2018 በጀት ዓመት ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የተቋሙን ጥቅምና ገጽታ የሚያስጠብቁ የተለያዩ ተግባራት መከናወናቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮምፕሊያንስና ገቨርናንስ ዘርፍ ገለጸ፡፡ የዘርፉሥራ አስፈጻሚ ተወካይ ወ/ሮ መስከረም በቀለ እንደገለጹት የተቋሙን ስትራቴጅክ ዕቅድ መሰረት በማድረግ የተቋሙን ገጽታ ከመገንባት፣ ብልሹ አሰራሮችን ከመከላከል፣ የተቋሙን ጥቅም ከማስጠበቅ፣ ግልጸኝነትንና ተጠያቂነትን ከማስፈን እንዲሁም የሴቶችን ተሳትፎ ከማሳደግ አንጻር የተለያዩ ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ 10 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ መጠን ባላቸው 355 የፍትሐብሄር እና 57 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር መጠን ባላቸው 37 የሥራ ክርክር መዝገቦች ላይ ክትትል ሲደረግ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ብልሹ-አሰራሮችን-በመከላከል-የተቋሙን-ጥ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም

በከባድ ንፋስ ምክንያት የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ወደቁ ………///…….. ከለገጣፎ - ቃሊቲ በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ አምስት የብረት ምሰሶዎች መውደቃ
+5
በከባድ ንፋስ ምክንያት የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ወደቁ ………///…….. ከለገጣፎ - ቃሊቲ በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ አምስት የብረት ምሰሶዎች መውደቃቸውን የማዕከላዊ 1 ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ደረጄ ገዛኸኝ እንደተናገሩት ምንም እንኳ የብረት ምሰሶዎች በከባድ ንፋስ የወደቁ ቢሆንም በምሰሶዎቹ አካላት ላይ ስርቆት መፈፀሙ ለኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎቹ መውደቅ አሉታዊ አስተዋፅኦ አድርጓል። በዚህ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተደጋጋሚ የስርቆት ወንጀል እንደሚፈፀም የገለፁት ዳይሬክተሩ ከለሚ ኩራ ክፍለ ከተማና ከወረዳው የአስተዳደር አካላት ጋር በመነጋገር ለችግሩ እልባት መስጠት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። የወደቁ የኃይል ምሰሶዎችን በአፋጣኝ በመጠገን መስመሩን ወደ አገልግሎት ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን አቶ ደረጀ ተናግረዋል። አምስቱ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከሌሊት 7 ሰዓት አካባቢ መውደቃቸውንና በሰው እና በእንስሳት ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት አለመድረሱ ታውቋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም

ጥራት ያለው ሪፖርት የተቋሙን ገጽታ ከመገንባት ባሻገር የሀብት አጠቃቀምን ለማሻሻል እንደሚረዳ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ተናገሩ ……///……. ጥራት ያለው ሪፖርት የተቋሙን ገጽታ ከመገንባቱ ባሻገር የ
+4
ጥራት ያለው ሪፖርት የተቋሙን ገጽታ ከመገንባት ባሻገር የሀብት አጠቃቀምን ለማሻሻል እንደሚረዳ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ተናገሩ ……///……. ጥራት ያለው ሪፖርት የተቋሙን ገጽታ ከመገንባቱ ባሻገር የሀብት አጠቃቀምን ለማሻሻል እንደሚያግዝ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ተናገሩ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን እና የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ በጋራ በመሆን በሪፖርት ዝግጅትና አቀራረብ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ አካሂደዋል፡፡ በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ የኢነርጂ እና ኮኔክቲቪቲ ፖርትፎሊዮ ዳይሬክተር ዶክተር ጌትነት መላክ በሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ ላይ ያተኮረ የንድፈ-ሐሳብ እና ገቢራዊ ተሞክሮዎችን ለተሳታፊዎች አቅርበዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ጥራት-ያለው-ሪፖርት-የተቋሙን-ገጽታ-ከመገ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም

በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ስርቆት የፈፀመው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ …....///….…. በጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ በሚገኝ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ከባድ የስርቆት ወንጀል የፈጸመውን ግለሰ
+6
በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ስርቆት የፈፀመው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ …....///….…. በጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ በሚገኝ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ከባድ የስርቆት ወንጀል የፈጸመውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የወረዳው ፖሊስ አስታወቀ፡፡ የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር አዳነ ቡርጄ እንደገለጹት ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 አካባቢ ከወላይታ ሶዶ-ሳውላ በተዘረጋው ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ የስርቆት ወንጀል የፈጸመውን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ሥር ለማዋል ክትትል ሲደረግ ቆይቷል፡፡ ተጠርጣሪው ከ7 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማት በተለያዩ ጊዜያት በባለ ሦስት እግር ባጃጅ በማጓጓዝ በቁጫ ወረዳ ጋሌ 2 ቀበሌ ልዩ ሥፍራ ሞጎላ ማዞሪያ ከሚባል አካባቢ ከደበቀበት ቦታ በሕብረተሰቡ ጥቆማ ፖሊስ ንብረቱን በቁጥጥር ሥር መዋሉን ጠቁመዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በኤሌክትሪክ-መሰረተ-ልማት-ላይ-ስርቆት-የ-3&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከ805 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል …….////……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ከ805 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረ
+2
ተቋሙ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከ805 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል …….////……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ከ805 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የተለያዩ የማህበራዊ ኃላፊነት ተግባራትን ማከናወኑን በተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደገለጹት ተቋሙ የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ ለማሳካት ከሚያከናውናቸው ሥራዎች ጎን ለጎን በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በመሳተፍ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ላይ ይገኛል፡፡ በዚህም በበጀት ዓመቱ 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር የፋይናንስ ወጪ በማድረግ ለመቄዶኒያ የአረጋውያን መርጃ ማዕከል ማዕድ ማጋራቱን ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-ማህበራዊ-ኃላፊነቱን-ለመወጣት-ከ805-ሚ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም

ግድቡ “የሚሊየኖችን ቤት ወደ ብርሃን ቀይሯል” - ሲኤንኤን ..///…. ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ “የሚሊየኖችን ቤት ወደ ብርሃን የቀየረ ግድብ ነው” ሲል ዓለም አቀፉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሲ ኤን
+1
ግድቡ “የሚሊየኖችን ቤት ወደ ብርሃን ቀይሯል” - ሲኤንኤን ..///…. ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ “የሚሊየኖችን ቤት ወደ ብርሃን የቀየረ ግድብ ነው” ሲል ዓለም አቀፉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሲ ኤን ኤን ዘገበ፡፡ በሲኤንኤን የኬንያ ዘጋቢ ቪክቶሪያ ሩባደሪ ወደ ህዳሴ በመጓዝ ባሰናዳችው ዘገባ ግድቡን ኢትዮጵያውያን ያለማንም ድጋፍ በራሳቸው አቅም ገንብተው ለውጤት ማብቃታቸውን ገልፃለች፡፡ በአፍሪካ በግዙፍነቱ ቀዳሚ የሆነው የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ከኢትዮጵያ አልፎ ለቀጣናው የኃይል አቅርቦት ትስስር ሚናው ከፍተኛ መሆኑን በፕሮግራምዋ አንስታለች፡፡ ግድቡ ለኢትዮጵያውያን ኃይል ከማቅረብ ባለፈ የቱሪስት መዳረሻ በመሆን የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በመደገፍ ረገድ ትልስ ተስፋ ይዞ እንደመጣ አብራርታለች፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በዘገባው ላይ ግድቡ 5 ሺህ 150 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳለው አስረድተዋል፡፡ ግድቡ ከኢትዮጵያ አልፎ ጎረቤት ሀገራትን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን በመጥቀስ በቀጣይ ደግሞ ለሶማሊያ እና ደቡብ ሱዳን ኃይል ለመሸጥ ዝግጅት መደረጉን አመልክተዋል፡፡ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ 145 ሜትር ከፍታ እና 1 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር ርዝመት ሲኖረው በዓመት በአማካይ 15 ሺህ 670 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ያመነጫል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ https://www.eep.com.et ሐምሌ 28

"አንድም ኪሎ ዋት ኃይል ያላግባብ እንዳይባክን ጥብቅ የውሃ አስተዳደር ሥርዓት እንዘረጋለን" ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ……..///……. ከኃይል ማመንጫዎች ግድቦች የሚመነጨውን አንድም ኪሎ ዋት ኃይል
+4
"አንድም ኪሎ ዋት ኃይል ያላግባብ እንዳይባክን ጥብቅ የውሃ አስተዳደር ሥርዓት እንዘረጋለን" ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ……..///……. ከኃይል ማመንጫዎች ግድቦች የሚመነጨውን አንድም ኪሎ ዋት ኃይል ያላግባብ እንዳይባክን ጥብቅ የውሃ አስተዳደር ሥርዓት እንደሚዘረጋ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለጹ፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ባቀረቡት የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት ዋና ዋና ዕቅዶች ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት ባለፈው በጀት ዓመት ተቋሙ የጀመረው የማንሰራራት ጉዞ ወደ ኋላ እንዳይመለስ አመራሩና ሠራተኛው በቅንጅት መሥራት ያስፈልጋል። የአየር ንብረት ለውጡን ተከትሎ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳይቀንስ አስፈላጊውን የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በስፋት መሥራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የተቋሙ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም መዘገየት ከተቋም ስኬት አልፎ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ተግዳሮት እንደሚሆን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ሁሉም ፕሮጀክቶች በታቀደላቸው ጊዜና የጥራት ደረጃ መጠናቀቅ እንዳለባቸውም ነው የተናገሩት፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=አንድም-ኪሎ-ዋት-ኃይል-ያላግባብ-እንዳይባ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም

“የኃይል አማራጮችን በማስፋት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የኢነርጂ አቅም መገንባት ያስፈልጋል” ኢንጂነር አይሻ መሐመድ …....///….... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተለያዩ የኃይል አማራ
+7
“የኃይል አማራጮችን በማስፋት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የኢነርጂ አቅም መገንባት ያስፈልጋል” ኢንጂነር አይሻ መሐመድ …....///….... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተለያዩ የኃይል አማራጮችን በማስፋት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የኢነርጂ አቅም መገንባት እንዳለበት የመከላከያ ሚኒስትርና የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ አባል ኢንጂነር አይሻ መሐመድ አስታወቁ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ የተቋሙን የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ሲገመግም ኢንጂነር አይሻ እንደገለጹት ተቋሙ በጀት ዓመቱ በቁጥር ደረጃ መልካም ውጤት ያሳየ ቢሆንም በሂደቱ የታዩ ጉድለቶችንና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በዝርዝር መተንተን አስፈላጊ ነው፡፡ በቀጣይ ከአየር ንብረት ለውጡ ጋር ተያይዞ ሊከሰቱ የሚችሉ የውሃ እና የኃይል አቅርቦት እጥረቶችን እንዲሁም እየጨመረ የመጣውን ፍላጎት ለማስተናገድ የሚያስችል ዝግጅት ሊደረግ እንደሚገባ ተናግረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-አማራጮችን-በማስፋት-ለአየር-ን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም

Le ahun new?

ተቋሙ የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነትን ለማረጋገጥ የግሪድ ማጠናከሪያ ጥናት አከናውኗል …….///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ከኮፕ-32 ጋር ተያይዞ ለአዲስ
ተቋሙ የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነትን ለማረጋገጥ የግሪድ ማጠናከሪያ ጥናት አከናውኗል …….///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ከኮፕ-32 ጋር ተያይዞ ለአዲስ አበባና አካባቢዋ ተጨማሪ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል የግሪድ ማጠናከሪያ ጥናት ማከናወኑን አስታወቀ፡፡ በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ተወካይ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ያለውአይቀር ማንደፍሮ እንደገለፁት‎ በበጀት ዓመቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን የሚጨምሩ እንዲሁም የግሪድ ሲስተም አስተማማኝነትን የሚያሻሽሉ ሦስት ፕሮጀክቶችን የቴክኒካዊ የአዋጭነት ጥናቶች ተከናውነዋል፡፡ የአራት አነስተኛ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች የቅድመ አዋጭነት ጥናት 50 በመቶ ለማከናወን ታቅዶ የዕቅዱን 90 በመቶ መጠናቀቁን ተናግረዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከአምስት ዓመት በፊት ተዘጋጅቶ የነበረውን የቴክኖሎጂ ካታሎግ የመከለስ ሥራ ከዴንማርክ እና ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባለሙያዎች ጋር በጥምረት መከናወኑን የጠቆሙት ሥራ አስፈጻሚው   ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-የኃይል-አቅርቦት-አስተማማኝነትን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

"የመንግሥት የፖሊሲ አቅጣጫዎች ተቋሙ ትርፋማ እንዲሆን አስችለውታል"  አምባሳደር ግርማ ብሩ ......///...... የመንግሥት የፖሊሲ አቅጣጫዎች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከነበረበት ከፍተኛ የዕዳ ጫና ወጥቶ ትርፍ እንዲያስመዘግብ ማስቻላቸውን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ አማካሪና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አምባሳደር ግርማ ብሩ አስታወቁ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ የተቋሙን የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በስካይ ላይት ሆቴል ገምግሟል። በግምገማ መድረኩ ላይ አምባሳደር ግርማ ብሩ  እንደገለፁት ከለውጡ በፊት የነበረው የመንግሥት የፖሊሲ አቅጣጫ ተቋሙ ከዕዳ አዙሪት ውስጥ እንዳይወጣ አድርጎት ቆይቷል። የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች የመንግሥትን የፖሊሲ ድጋፎች ተጠቅመው ላስመዘገቡት መልካም ውጤት ሊኮሩ እንደሚገባ ተናግረዋል። እንደ አምባሳደር ግርማ ገለጻ በ2018 በጀት ዓመት የታየው ስኬት በ2019 በጀት ዓመት ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ እንዳይሸረሸር ለማድረግ ወደ ግድቦች የሚገባውን የውሃ መጠን በጥንቃቄ መጠቀም ያስፈልጋል። በቀጣይ ከአየር ንብረት ለውጡ ጋር ተያይዞ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ስጋቶችን ከወዲሁ ለመቆጣጠር በትኩረትና በቅንጅት መስራት እንደሚገባም አሳስበዋል። ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና የጥራት ደረጃ ማጠናቀቅ አለመቻል በተቋሙ ገቢ ላይ አሉታዊ ጫና እንደሚያሳድር ያብራሩት አምባሳደር ግርማ ችግሩ እንዳይከሰት ለማድረግ በፕሮጀክት ግንባታዎች ላይ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች ሊጠናከሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ተቋሙ ከፍተኛ ሀብት የሚያንቀሳቅስ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደር ግርማ ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ የሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን በጋራ መታገል እንደሚገባም ነው ያሳሰቡት። አምባሳደር ግርማ እንዳሉት ለተቋሙ ሠራተኛ ምቹ የሥራ ከባቢ በመፍጠር የሥራ ላይ እርካታን መጨመር ይገባል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

የፕሮጀክቱ ሠራተኞች በአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ተሳትፈዋል .......///........ የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሠራተኞች "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ በሚገኘው በአንድ ጀንበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል የአረንጓዴ አሻራ መረሃ-ግብር ላይ አሻራቸውን አሳርፈዋል። በፕሮጀክቱ የአካባቢና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ በግንባታ ሥራ ምክንያት የተራቆቱ ቦታዎችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ እያከናወነ ካለው ሥራ በተጨማሪ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ከተጀመረበት ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በየዓመቱ ችግኞችን በመትከል በንቃት እየተሳተፈ ይገኛል፡፡ በዚህም ፕሮጀክቱ የራሱን የችግኝ ማፍያ ጣቢያ በማቋቋም መርሃ ግብሩ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የተለያየ ዝርያ ያላቸው 23 ሺህ 873 ችግኞችን መትከሉን ገልፀዋል፡፡ በዘንድሮው የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይም የተሻሻሉ ዝርያ ያላቸውና ለምግብነት የሚውሉ ችግኞችን መትከል መቻሉን ተናግረዋል፡፡ በተለያዩ ጊዜያት የተከናወኑ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሮች በሠራተኞች መኖሪያ አካባቢ የነበሩ የተፈጥሮ ዛፎችን ለምግብነት በሚውሉ እንዲተኩ እያስቻለ ስለመሆኑም አንስተዋል፡፡ እንደ አቶ ግዛቸው ገለፃ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ የአካባቢውን ሥነ ምህዳር በመጠበቅ የሥራ ቦታዎችን ለኑሮ ምቹ እያደረገ ይገኛል፡፡ በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻር መርሃ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የፕሮጀክቱ ሥራ ተቋራጭ እና አማካሪ ድርጅት ሠራተኞች እንዲሁም የፌደራል ፖሊስ አባላት ተሳትፈዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

የሥራ አመራር ቦርዱ የተቋሙን ዓመታዊ አፈፃፀም እየገመገመ ነው .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ የተቋሙን የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በስካይ ላይት ሆቴል መገምገም ጀምሯል። ግምገማው ተቋሙ በበጀት ዓመቱ  በኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች፣  በሰው ኃይል ልማት፣ በፋይናንስ፣ በኃይል ማመንጨት፣ በማስተላለፍ፣ በማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታና የጥገና ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። የበጀት ዓመቱን አፈጻጸም ያቀረቀቡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት በአስራ ሁለት ወራት ውስጥ ተቋሙ ካመነጨው አጠቃላይ ኃይል ውስጥ 93 በመቶውን ለሀገር ውስጥ እና  ቀሪ  7 በመቶውን ደግሞ ለጎረቤት ሀገራት አቅርቧል። በበጀት ዓመቱ በኃይል ማመንጨት፣ ማከፋፈል፣ ማስተላለፍ እና ሽያጭ እንዲሁም በዋና ዋና ፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ አበረታች ለውጦች መታየታቸውን ጠቁመዋል። ተቋሙ ለዘመናት ከተከማቸበት ዕዳ ወጥቶ ወደ ትርፍ የተሸጋገረበት ዓመት እንደነበርም ነው በሪፖርታቸው ያመለከቱት። በበጀት ዓመቱ ተቋሙ ከነበረበት 168 በመቶ ኪሳራ ወደ ያልተጣራ 39 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ትርፍ መሸጋገር መቻሉን ገልፀዋል። ለዚህ ስኬት መገኘትም የመንግስት፣ የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድና የተቋሙ ሠራተኞችና አመራሮች ድርሻ የጎላ መሆኑን በመጥቀስ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህዳሴ፣ የአይሻ እና የአሰላ ፕሮጀክቶችን በስኬት አጠናቆ ወደ ኦፕሬሽን ማስገባት መቻሉ የኢነርጂ ምርት ዕድገት እንዲመዘገብ ማስቻሉንም ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ የፕሮጀክቶች ማኔጅመንት አቅም ማነስ፣ የጸጥታ ችግርና ሥርቆት፣ የወሰን ማስከበር መዘገየት፣ የግዥ ሂደት መጓተት፣ የሎጂስቲክስ እንዲሁም የነዳጅ እጥረት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እንዳይጠናቀቁ ዋና ዋና ተግዳሮቶች የነበሩ መሆናቸውን ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም

ማመንጫ ጣቢያው በበጀት ዓመቱ ከ940 ጌጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል .....///..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግልገል ጊቤ 1 የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2018 በጀት ዓመት 94
+7
ማመንጫ ጣቢያው በበጀት ዓመቱ ከ940 ጌጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል  .....///..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግልገል ጊቤ 1 የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2018 በጀት ዓመት 943 ጌጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማመንጨቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ተናገሩ፡፡   ሥራ አስኪያጁ አቶ ደሳለኝ ንጉሳ እንደተናገሩት ጣቢያው በ2018 በጀት ዓመት ለማመንጨት ካቀደው 986 ጌጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ 943 ጌጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማመንጨት የዕቅዱን 95 ነጥብ 63 በመቶ አሳክቷል፡፡ በበጀት ዓመቱ የመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል ከዕቅዱ የ43 ጌጋ ዋት ሰዓት ወይም የ4 ነጥብ 37 በመቶ እንዲሁም ከባለፈው የ2017 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ34 ጌጋ ዋት ሰዓት ወይም የ3 ነጥብ 6 በመቶ ቅናሽ ያለው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡   ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ማመንጫ-ጣቢያው-በበጀት-ዓመቱ-ከ940-ጌጋ-ዋት-ሰ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም