ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 553 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 406 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 161 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 553 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 19 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -3، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -5، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 26.69‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.00‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 150 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 332 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 20 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 553
المشتركون
-524 ساعات
+97 أيام
-330 أيام
أرشيف المشاركات
"ጣቢያው የአንድ ትውልድ ጥያቄን የመለሰ ነው" ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል ...///... የወራቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን መገንባቱ የአንድ ትውልድ ዘመን ጥያቄን መመለስ መቻሉን የኢፌዲሪ  የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ገለፁ። ሚኒስትሯ ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል በማከፋፈያ ጣቢያው የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር የኤሌክትሪክ አቅርቦቱ የስልጤ ዞንን ቀጣይ የብልፅግና ጉዞ የሚያፋጥንና የአካባቢውን እምቅ አቅም ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑን ገልፀዋል። የኃይል መሰረተ ልማቱ የአካባቢውን ማህበረሰብ የልማት ፍላጎት ከማርካት ባለፈ የወራቤ ከተማንና አጠቃላይ የስልጤ ዞንን የንግድና የኢኮኖሚ መናኸሪያ ለማድረግ ለተያዘው ግብ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርም ነው የተናገሩት። የወራቤ ከተማ በንግድና በማህበራዊ ትስስር ረገድ ያላትን ስልታዊ ጠቀሜታ ያነሱት ወ/ሮ ሙፈሪያት ከተማዋ በርካታ መጋቢ መንገዶች የሚገናኙባትና ሰፊ የንግድ እንቅስቃሴ የሚስተናገድባት በመሆኗ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ማግኘቷ ስትራቴጂካዊ አቅሟን ይበልጥ እንደሚያጎለብተው ጠቅሰዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በሀገር ደረጃ የተከናወኑ የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማቶች የሀገሪቱን ከፍታ ያበሰሩ ብቻም ሳይሆኑ በአህጉርና በዓለም አቀፍ ደረጃ የኃይል ሚዛንን ያስተካከሉ ትልልቅ ስኬቶች መሆናቸውንም ነው የጠቀሱት። እንደ ሚኒስትሯ ገለፃ ጣቢያው የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ብቻ ሳይሆን የአካባቢውን ማህበረሰብ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ትስስር ይበልጥ የሚያጠናክርና የሚያቀናጅ ታሪካዊ መሰረት ነው። በአሁኑ ወቅት የኃይል አቅርቦቱ አስተማማኝ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በስልጤ ዞን በግሉ ዘርፍና በመንግሥት ትብብር ወደ አንድ ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የተጀመሩ የኢንዱስትሪ ልማቶች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል። ለፕሮጀክቱ ስኬት በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀን ከሌሊት በቁርጠኝነት የሠሩትን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር፣ የሥራ ተቋራጭና አማካሪ አካላትን ያደነቁት ሚኒስትሯ የአካባቢው አመራርና ማህበረሰብም ፕሮጀክቱን በባለቤትነት ስሜት በመንከባከብ ላሳዩት ቀና ትብብር ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ይህ የተቀናጀ የሥራ ባህልና የባለቤትነት መንፈስ ለሌሎች መሰል ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶችም በምሳሌነት ሊወሰድ የሚገባው ታላቅ ተሞክሮ መሆኑንም ነው ያብራሩት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

"የኤሌክትሪክ ኃይል የብልፅግና ምሰሶ ነው" ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ...///... የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሀገሪቱ የብልፅግና ጉዞ ዋነኛ ምሰሶ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገለፁ። ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የወራቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት የጣቢያው መገንባት ተቋሙ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል በመላ ሀገሪቱ ለማዳረስ ለያዘው ስትራቴጂካዊ ግብ ስኬት ትልቅ ማሳያ ነው። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ለአገልግሎት መብቃት ለአካባቢው ቀጣይ የዕድገትና የብልፅግና ጉዞ ትልቅ መደላደል እንደሚፈጥርም ነው የተናገሩት። የጣቢያው ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በይፋ ለማብሰር የተዘጋጀው የምርቃት መርሃ ግብር የተገኘውን ስኬትና ደስታ ከማህበረሰቡ ጋር በጋራ ለመካፈል መሆኑን አስረድተዋል። ተቋሙ በመላ ሀገሪቱ በርካታ የኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያና የማከፋፈያ ጣቢያዎችን እየገነባ እንደሚገኝ የገለፁት ኢንጂነር አሸብር ዘንድሮ በርካታ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃቱን አብራርተዋል። እነዚህ ግዙፍ የኃይል መሠረተ ልማቶች ተመርቀው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን ተከትሎ የሀገሪቱ የኃይል አቅርቦት አቅም በከፍተኛ ደረጃ ማደጉንም ነው የገለፁት። የወራቤ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአጭር ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ የስልጤ ዞንና የወራቤ ከተማ አመራሮች እንዲሁም ማህበረሰቡ ላደረጉት ልዩና አርአያነት ያለው ድጋፍ በተቋሙ ስም ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ከሚልን ጨምሮ የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

የወራቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት እየተከናወነ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioe
+9
የወራቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት እየተከናወነ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

የትራንፎርመር ተከላው ተጠናቆ ኃይል መስጠት ጀመረ ........///........ የበለስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን የአገልግሎት አቅም ለማሳደግና በጣቢያው ዙሪያ ለሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ሲከናወን የቆየው  የትራንስፎርመር ተከላ ሥራ ተጠናቆ በዛሬው ዕለት ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጉን የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ተወካይ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ግርማ ዘለቀ እንዳስታወቁት በጣቢያው 25 ሜጋ ቮልት አምፒር ኃይል የመሸከም አቅም ያለው አንድ ትራንፎርመር በመትከል በአካባቢው ለረጅም ጊዜ ይስተዋል የነበረውን የኃይል አቅርቦት ችግር በከፍተኛ ደረጃ ይፈታል። ትራንስፎርመሩ ወደ ሥራ መግባቱ በጣቢያው ላይ ይፈጠር የነበረውን ከፍተኛ የኃይል ጫና ከማቃለሉም ባሻገር የተረጋጋ የኤሌክትሪክ ፍሰት ለአካባቢው ማህበረሰብ ለማድረስ እንደሚያስችልም ተናግረዋል። ከዚሁ ጎን ለጎን ከሁለት ዓመት በፊት ጉዳት ደርሶበት የነበረው 400 ኪሎ ቮልትን ወደ 132 ኪሎ ቮልት የሚቀይር ባለ 125 ሜጋ ቮልት አምፒር አንድ ትራንስፎርመር በአዲስ መተካቱን ገልፀዋል። በዚህም ምክንያት የጃዊ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከአገልግሎት ውጪ ሆኖ መቆየቱን አስታውሰዋል። ማከፋፈያ ጣቢያው በ132 ኪሎ ቮልት ለበለስ ስኳር ፋብሪካ እና በአካባቢው ለሚገኙ ከተሞች ኃይል ይሰጥ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ግርማ የደረሰው ችግር በኃይል አቅርቦቱ ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሮ መቆየቱን ገልፀዋል። እንደ ተወካይ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በወቅቱ የነበረውን የኃይል እጥረት ጫና ለማቃለል ከጣቢያው ከተሰራ መስመር ላይ በመቀጠል ለአካባቢው ማህበረሰብ የኃይል አቅርቦት ለማመቻቸት ሙከራ ተደርጎ ነበር። ይሁን እንጂ የተወሰደው ጊዜያዊ መፍትሔ በመስመሮቹ ላይ ብልሽት ከተከሰተ በቀጥታ ወደ ኃይል ማመንጫ ጄኔሬተሩ በመተላለፍ ዘላቂ ጉዳት ሊያደርስ የሚችል በመሆኑ በጣቢያው ደህንነት ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኖ እንደነበር አብራርተዋል። ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት አንድ 125 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው የትራንስፎርመር ግዥ ተከናውኖ ከውጭ እንዲገባ ቢደረግም በወቅቱ በነበረው የፀጥታ ሁኔታ እና የመንገድ ችግር ምክንያት ለአምስት ወራት ያህል በሱልልታ ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲቆይ መደረጉንም ጠቅሰዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የትራንፎርመር ቅየራ ሥራው በመጠናቀቁ ላለፉት ሁለት ዓመታት ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩ አካባቢዎች ከዛሬ ጀምሮ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘት መጀመራቸውን ጠቁመዋል። በዚህም በ33 ኪሎ ቮልት የበለስ ስኳር ፋብሪካ፣ ጃዊ እና ሰሜን አቸፈር ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል እያገኙ መሆኑን ነው ያብራሩት። በአሁኑ ወቅት ለሊበን ከተማ የኃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎች በሪጅኑ በኩል እየተከናወኑ በመሆኑንም ነው ያስታወቁት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ የወራቤ ማከፋፈያ ጣቢያን ጎበኙ .......///... ... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተመራ ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን የወራቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን ጎብኝቷል። በ15 ወራት ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ የተጠናቀቀው ማከፋፈያ ጣቢያው በነገው ዕለት በይፋ ይመረቃል። በጉብኝቱ ወቅት ዋና ሥራ አስፈፃሚው እንደገለፁት የጣቢያው ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ የስልጢ ዞንና የወራቤ ከተማ አስተዳደር ያደረጉት ሁለንተናዊ ድጋፍ የሚደነቅ ነው። ዋና ሥራ አስፈፃሚው በጣቢያው ከኦፕሬሽን ሠራተኞች መኖሪያ ቤት፣ ከውሃና ከተሽከርካሪ አቅርቦት እንዲሁም ከኦፕሬሽን ሥራዎች አንፃር ያለውን እንቅስቃሴ ገምግመዋል። በማከፋፈያ ጣቢያው ዙሪያ ለሚገኙ  የአካባቢው ማህበረሰቦች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት  ጋር በቅንጅት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። የዞኑ ከፍተኛ አመራሮችም ተቋሙ ፕሮጀክቱን በተያዘለት የጊዜ ገደብ አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ በማድረጉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

ተቋሙ በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የኃይል መሠረተ-ልማት ያለውን ተሞክሮ ለአንጎላ ባለሙያዎች አጋራ ……….///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሀገሪቱ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (E-Mobility) ስትራቴጂያዊ ሽግግር ውስጥ እያከናወናቸው ያሉትን የኃይል አቅርቦትና የመሠረተ-ልማት ዝግጁነት ሥራዎች ከአንጎላ የመጡ የዘርፉ ባለሙያዎች አጋራ፡፡ በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ የኃይል ሲስተም ጥናት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙኒር ኑርሁሴን በልምድ ልውውጥ መድረኩ ላይ እንደገለጹት ተቋሙ በሀገሪቱ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ሽግግር ውስጥ የበኩሉን አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል። ሽግግሩ ሀገራችን ለነዳጅ ገቢ የምታወጣውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ለመቀነስ፣ የበለፀገውን የታዳሽ ኃይል ሀብታችንን በአግባቡ ለመጠቀም እንዲሁም የአካባቢ ብክለትን ለመከላከልና የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ ከፍተኛ ረዳት እንደሚሆን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ፣ የኃይል ማከፋፈያ መሠረተ ልማቶችን ማቀድና ማስፋፋት፣ የቴክኒክ ድጋፍ መስጠት እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መሥራት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ እንደሚገኝ ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል። ይህንን የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ፍላጎትና ቀጣይ ዕድገትን ለመደገፍም ተቋሙ አሁን ላይ ያለውን አጠቃላይ አቅምና የወደፊት ዕቅዶች አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ከፍተኛ የኃይል ሥርዓት መሐንዲስ የሆኑት አቶ ሀብታሙ አበበ በበኩላቸው የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ቋት ላይ የሚያሳድሩት ተፅዕኖ በሚል ርዕስ ጥናታዊ ማብራሪያ አቅርበዋል። ጥናቱ በሀገሪቱ በቅርቡ ይፋ የተደረገውን ብሔራዊ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ትግበራ ስትራቴጂ (2025–2030) መሠረት ያደረገ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሀብታሙ ስትራቴጂው እስከ 2030 ዓ.ም ድረስ 500 ሺህ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባትና በአዲስ አበባ የሚገነቡ 1 ሺህ 176 ጣቢያዎችን ጨምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ 2 ሺህ 230 የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን ለመገንባት የያዘውን ግብ ለማሳካት እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን በዝርዝር የሚያሳይ መሆኑን አብራርተዋል። በልምድ ልውውጥ መድረኩ ላይ የተገኙት በአንጎላ የዓለም አቀፍ የአረንጓዴ ዕድገት ኢንስቲትዩት (GGGI Angola) ተወካይ አቶ ሴሌስቲኖ ዴሎ  በበኩላቸው ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ዘርፍ ያላትን እምቅ አቅም ግልጽ የሆነ ሀገራዊ ራዕይ እና የተቀናጀ የፖሊሲ አፈፃፀም ለአንጎላ ልዑክ መሠረታዊ ልምዶችን የመቅሰም ዕድል የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ሀገር የተያዘው የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ስትራቴጂ ከከፍተኛ አመራር ጀምሮ እስከ ታችኛው የመንግስት መዋቅርና በተለያዩ ሴክተሮች መካከል በሚገባ በማቀናጀት በተግባር እየተተረጎመ መሆኑን መገንዘባቸውን ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያቀረባቸው የማስተላለፊያ የማከፋፈያ ጣቢያዎችና የወደፊት የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች መረጃዎች ተቋሙ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለመወጣት እያደረገ ያለውን ዝግጁነት የሚያሳይ መሆኑን ያወሱት አቶ ሎ ሀገራቸው አንጎላ ይህንን ስትራቴጂያዊ አሠራርና የመሠረተ-ልማት ትስስር እንደ መልካም ተሞክሮ የምትወስደው መሆኑን ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

የኤሌክትሪክ ኃይል አስደናቂና ውስብስቡ የሰከንዶች ጉዞ ⚡️🏗💡 እኛ ቤታችን ወይም ቢሮአችን ሆነን የአንድ ማብሪያ (Switch) ቁልፍ ስንጫን የምናገኘው ፈጣን ብርሃን፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜት
የኤሌክትሪክ ኃይል አስደናቂና ውስብስቡ የሰከንዶች ጉዞ ⚡️🏗💡   እኛ ቤታችን ወይም ቢሮአችን ሆነን የአንድ ማብሪያ (Switch) ቁልፍ ስንጫን የምናገኘው ፈጣን ብርሃን፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን አቋርጦ፣ በርካታ የምህንድስና፣ የሎጂስቲክስና የኦፕሬሽን ፈተናዎችን አልፎ የሚደርስ የሰከንዶች ጉዞ ውጤት ነው። ይህንን ግዙፍና ውስብስብ የኃይል ሰንሰለት (Power Value Chain) በአምስት ስልታዊ ምዕራፎች መመልከት ይቻላል፡፡   1. የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች  - የጉዞው መጀመሪያ   የኤሌክትሪክ ጉዞ የሚጀምረው እንደ ውሃ (Hydroelectric)፣ ንፋስ (Wind)፣ ወይም የከርሰ ምድር እንፋሎት (Geothermal) እምቅ ኃይልን ወደ ኤሌክትሪክ በሚቀይሩ ማመንጫ ጣቢያዎች ነው።   📌 የሚገጥመው ፈተና እነዚህ ማመንጫዎች አብዛኛውን ጊዜ የሚገነቡት ከከተሞችና ከኢንዱስትሪ ቀጣናዎች ርቀው በመሆኑ፣ ኃይሉን ወደ ተጠቃሚው ለማድረስ ረጅም ርቀት መጓዝ ግድ ይላቸዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኤሌክትሪክ-ኃይል-አስደናቂና-ውስብስቡ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ጉዞ እና የአፍሪካ የኃይል ማዕከልነት ራዕይ 🇪🇹 ኢትዮጵያ በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያላቸውን ስትራቴጂዎች በመተግበር፣ በታዳሽ ኃይል (Renewab
የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ጉዞ እና የአፍሪካ የኃይል ማዕከልነት ራዕይ 🇪🇹   ኢትዮጵያ በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያላቸውን ስትራቴጂዎች በመተግበር፣ በታዳሽ ኃይል (Renewable Energy) ልማት ረገድ ግንባር ቀደም መሪ እየሆነች ትገኛለች።   በተፈጥሮ ፀጋዎች የበለፀገችው ሀገራችን ከ90 በመቶ በላይ የሚሆነውን የኤሌክትሪክ ኃይሏን ከንፁህና ለአካባቢ ተስማሚ ከሆኑ ምንጮች በማመንጨት፣ በአፍሪካ አስተማማኝ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታን በግንባር ቀደምትነት እየመራች ነው።   የሀገሪቱ የኢነርጂ ዘርፍ ስኬት፣ የወደፊት ዕቅዶችና ቀጠናዊ ፋይዳው በሚከተሉት አራት ዓበይት ስልታዊ ምሰሶዎች ላይ የተመሠረተ ነው፡፡   1. የተደራጀና ስልታዊ የኃይል አማራጮች ማሰባጠር (Energy Mix) 🔄   የኢትዮጵያ መልክአ-ምድራዊ አቀማመጥ የተለያዩ የታዳሽ ኃይል ምንጮችን በተቀናጀ ሁኔታ ለመጠቀም አስችሏታል፦ ·  የውሃ ኃይል (Hydropower)፦ የሀገሪቱ የኃይል አቅርቦት ዋና ምሰሶ ሆኖ ቀጥሏል።   ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኢትዮጵያ-የታዳሽ-ኃይል-ጉዞ-እና-የአፍሪ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ምንጮችን ማሰባጠር - የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር! ⚡️ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በውሃ ኃይል (Hydro) ላይ በአብዛኛው የተመሠረተ የኃይል አቅርቦት ሥርዓት ለአየር ንብረት ለ
የኃይል ምንጮችን ማሰባጠር - የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር! ⚡️   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በውሃ ኃይል (Hydro) ላይ በአብዛኛው የተመሠረተ የኃይል አቅርቦት ሥርዓት ለአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ባለፉት ሰባት ዓመታት የኃይል ምንጮቹን በንፋስ እና በጂኦተርማል ዘርፎች ኃይል የማሰባጠር (Energy Mix) ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።   ዋና ዋና ስኬቶች እና በመተግበር ላይ ያሉ ፕሮጀክቶች፦   ● የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች መነቃቃት (Wind Power)፦   • የአሰላ ፕሮጀክት፦ 100 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው፤   • የአይሻ 2 ፕሮጀክት፦ በመጀመሪያው ምዕራፍ 80 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው፤   ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይልምንጮችንማሰባጠር-የኢትዮጵያየአ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ምንጮችን ማሰባጠር - የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር! ⚡️ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በውሃ ኃይል (Hydro) ላይ በአብዛኛው የተመሠረተ የኃይል አቅርቦት ሥርዓት ለአየር ንብረት ለ
የኃይል ምንጮችን ማሰባጠር - የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር! ⚡️   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በውሃ ኃይል (Hydro) ላይ በአብዛኛው የተመሠረተ የኃይል አቅርቦት ሥርዓት ለአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ባለፉት ሰባት ዓመታት የኃይል ምንጮቹን በንፋስ እና በጂኦተርማል ዘርፎች ኃይል የማሰባጠር (Energy Mix) ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።   ዋና ዋና ስኬቶች እና በመተግበር ላይ ያሉ ፕሮጀክቶች፦   ● የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች መነቃቃት (Wind Power)፦   • የአሰላ ፕሮጀክት፦ 100 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው፤   • የአይሻ 2 ፕሮጀክት፦ በመጀመሪያው ምዕራፍ 80 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው፤   ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይልምንጮችንማሰባጠር-የኢትዮጵያየአ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም

ታዳሽ ኃይል- የአምራች ኢንዱስትሪው ዕድገት የጀርባ አጥንት! 🇪🇹 ⚡️   በኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ ግብርና፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም እና ኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ ትኩረት ተደርጎ በመሰራቱ ታላላቅ ስኬቶች እየተመዘገቡ ይገኛሉ።   ከእነዚህ መካከል ለአምራች ኢንዱስትሪው ዕድገት ወሳኝ ግብዓት የሆነውን የኤሌክትሪክ ኃይል በአስተማማኝ ሁኔታ በማቅረብ ረገድ የኃይል አቅርቦት ዘርፉ ታሪካዊ ምዕራፍ ላይ ይገኛል።   ሀገራችን አረንጓዴ ኢኮኖሚን የመገንባትና ኢትዮጵያን የአፍሪካ የኃይል ማዕከል የማድረግ ራዕይ በመሰነቅ የውሃ፣ የንፋስ፣ የፀሐይ እና የጂኦተርማል ኃይል ማመንጫ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት አብቅታለች፡፡ የኮይሻን ጨምሮ በግንባታ ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችም በተስፋ ሰጪ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።   የተመዘገቡ ታላላቅ ስኬቶች በቁጥር እና በተግባር፦   ·  የኃይል አቅም እጥፍ ዕድገት፦ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ እንደገለጹት ከለውጡ ወዲህ የሀገሪቱ የኃይል አቅርቦት ከእጥፍ በላይ አድጓል። ቀደም ሲል ከ4 ሺህ ሜጋ ዋት ያልበለጠው የኃይል ማመንጨት አቅም አሁን ላይ ወደ 10 ሺህ ሜጋ ዋት እየተጠጋ ይገኛል! ·  የኢንዱስትሪ ፍላጎት ምላሽ፦ በአሁኑ ወቅት የሚመረተው ታዳሽ ኃይል በዚህ ዓመት 23 በመቶ ላደገው የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪዎች የኃይል ፍላጎት ሙሉ ምላሽ መስጠት ችሏል።   ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ታዳሽኃይል-የአምራችኢንዱስትሪውዕድገት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 10 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

ኢትዮጵያ — የአፍሪካ የኃይል ማማ እና የጋራ ኢኮኖሚያዊ ጥንካሬ መሰረት! 🇪🇹⚡️ ኢትዮጵያን "የአፍሪካ የኃይል ማማ" የማድረግ ስልታዊ ራዕይ በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት (EAPP) ውስጥ ባላት
ኢትዮጵያ — የአፍሪካ የኃይል ማማ እና የጋራ ኢኮኖሚያዊ ጥንካሬ መሰረት! 🇪🇹⚡️   ኢትዮጵያን "የአፍሪካ የኃይል ማማ" የማድረግ ስልታዊ ራዕይ በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት (EAPP) ውስጥ ባላት መሪነት በተግባር እየተረጋገጠ ይገኛል።   ሀገራችን ባላት ምቹ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ እና በተፈጥሮ በበለፀገ ሀብቷ ለምስራቅ አፍሪካ እንደ ቀጣናዊ ትስስር እንደ "ሞተር" ሆና እያገለገለች ነው።   የዚህ ታላቅ ስኬት ማሳያ የ "ምስራቅ ኤሌክትሪክ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር" (Eastern Electricity Highway Project) ነው።   የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሩን በቁጥር   · የኢትዮጵያን ወላይታ ሶዶ ከኬንያው ሱስዋ የሚያገናኝ 1,045 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ባለሁለት ዋልታ (Bipolar) 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የቀጥተኛ ቮልቴጅ (HVDC) መስመር ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ኢትዮጵያ-የአፍሪካ-የኃይል-ማማ-እና-የጋ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 10 ቀን 2018 ዓ.ም

የማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ሥራ 45 በመቶ ደርሷል …///… የደቡባዊ የኤሌክትሪክ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል የሆነው የቲርጋ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የሲቪል ሥራ አፈፃፀም
+4
የማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ሥራ 45 በመቶ ደርሷል …///… የደቡባዊ የኤሌክትሪክ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል የሆነው የቲርጋ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የሲቪል ሥራ አፈፃፀም 45 በመቶ መድረሱን የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራዎች ተቆጣጣሪ አስታወቁ። ተቆጣጣሪው አቶ ደረጄ ክፍሌ እንደተናገሩት የመቆጣጠሪያ ክፍሉ የብረትና የኤሌክትሪክ ሥራዎች ተጠናቅቀው በአሁኑ ወቅት የጣሪያ ኮንክሪት ለመሙላት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።   በተጨማሪም የውስጥ ለውስጥ የፍሳሽ ማስወገጃ መስመሮች እና የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ በተጓዳኝ እየተከናወኑ መሆኑ ነው የተናገሩት፡፡ የፕሮጀክቱ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች 15 በመቶ መድረሳቸውን የጠቀሱት አቶ ደረጄ ለተከላው የሚያስፈልጉ መሣሪያዎች ወደ ፕሮክቱ ሥፍራ መድረሳቸውን አብራርተዋል። በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ ትራንስፎርመሩን ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ የዘይት መሙላትና የማጣራት ሥራ እንደሚከናወን ገልፀዋል፡፡   ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የማከፋፈያ-ጣቢያው-የሲቪል-ሥራ-45-በመቶ-ደር&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 10 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል አቅርቦትን በማሳደግ የተገኘ 400 ሜጋ ዋት ተጨማሪ ኃይል! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እያደገ የመጣውን የደንበኞች የኃይል ፍላጎት በዘላቂነት ለማሟላትና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖ
የኃይል አቅርቦትን በማሳደግ የተገኘ 400 ሜጋ ዋት ተጨማሪ ኃይል!   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እያደገ የመጣውን የደንበኞች የኃይል ፍላጎት በዘላቂነት ለማሟላትና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ ስትራቴጂካዊ የአቅም ማሳደግ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።   የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትና የተገኙ ውጤቶች፦ ባለፉት 5 ዓመታት በ10 ቁልፍ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ በተከናወኑ የትራንስፎርመር አቅም ማሳደግ ሥራዎች 439 ሜጋ ዋት (ወይም 487.3 MVA) ተጨማሪ ኃይል ወደ ሲስተሙ ማግኘት ተችሏል። የአቅም ማሳደግ ሥራው የተከናወነባቸው ጣቢያዎች፦ ለገጣፎ፣ ቦሌ ለሚ 2፣ አዳማ 2፣ ወልቂጤ፣ ሚዛን፣ ባህር ዳር፣ ኮምቦልቻ 2፣ ገፈርሳ፣ ባሌ ሮቤ እና አዲስ ዌስት ናቸው።   የአቅም ማሳደግ ሥራዎቹ የቴክኒክ ብልሽቶችን በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነስ የኃይል መቆራረጥን ለማስወገድ ትልቅ ውጤት አስመዝግበዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-አቅርቦትን-በማሳደግ-የተገኘ-400-ሜጋ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም