uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 530 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 333-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 176-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 530 obunachiga ega bo‘ldi.

08 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 5 ga, so‘nggi 24 soatda esa 2 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 28.83% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.82% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 478 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 457 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 11 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“EEP Communication”

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 09 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 530
Obunachilar
+224 soatlar
-77 kunlar
+530 kunlar
Postlar arxiv
ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለጅማ ከተማዋና አካባቢው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መነቃቃት ጉልህ አስተዋፅኦ እያበረከቱ ነው በጅማ ከተማ የሚገኙት ሁለቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለከተማዋና ለአካባቢው ሁለንተናዊ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት መነቃቃት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከቱ እንደሚገኙ የጣቢያዎቹ የሥራ ኃላፊዎች ገለፁ። የጅማ ቁጥር አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ናትናኤል ወርቅነህ እንደተናገሩት ጣቢያው ከመስከረም 1980 ዓ.ም ጀምሮ የጅማ ቁጥር ሁለት ማከፉፈያ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት እስከጀመረበት እስከ ነሐሴ 2007 ዓ.ም ድረስ ለከተማዋና ለአካባቢው ብቸኛ የኃይል አቅራቢ በመሆን አገልግሏል። ይሁንና የቁጥር ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ሼል ከገባ በኋላ የተወሰኑ የከተማዋ አካባቢዎች ከቁጥር ሁለት እንዲያገኙ በመደረጉ አሁን ላይ ጣቢያው 90 በመቶ የሚሆነውን የከተማዋን የኃይል አቅርቦት እየሸፈነ ይገኛል ብለዋል። ጣቢያው ባለ 20 እና ባለ 16 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች፣ አንድ ባለ 132፣ ዘጠኝ ባለ 15 እና ስድስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች አሉት። አሁን ላይ በአራት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች አማካኝነት ለጅማ ከተማ እስከ 18 ሜጋ ዋት ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ የገለፁት አቶ ናትናኤል በሦስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ደግሞ ለሊሙ ገነትና ለሾቤ ወረዳዎች እንዲሁም ለጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክ እስከ 8 ሜጋ ዋት ኃይል በማቅረብ ላይ ይገኛል። ይህም ለአካባቢው ኢኮኖሚ መነቃቃት ትልቅ መሠረት ጥሏል። ቀሪዎቹ አምስት ባለ 15 እና ሦስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ለታለመው የስማርት ሲቲ ፕሮጀክትና ለሌሎች አዳዲስ አገልግሎቶች በመጠባበቂያነት መዘጋጀታቸውንም ኃላፊው አክለዋል። በአሁኑ ወቅት የባለ 20 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሩ የመጫን አቅሙ በመሙላቱ ተጨማሪ ደንበኞችን ማስተናገድ እንደማይችል ጠቁመው የባለ 16 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሩ ደግሞ ከአቅሙ 55 በመቶ በላይ  የሚሆነው ጥቅም ላይ ውሏል ብለዋል። ከቴክኖሎጂ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ ከዘጠኝ ወር በፊት የጣቢያውን የ33 ኪሎ ቮልት የመቆጣጠሪያ ብሬከሮች ወደ ዘመናዊው የጂአይኤስ (GIS) ሥርዓት በመቀየር ከመረጃ አያያዝ እና ከኦፕሬሽን አሰራር ጋር ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን መቅረፍ ተችሏል። በቀጣይም ለረጅም ዓመታት ያገለገሉትን የሲዊች ያርድ፣ የባዝ ባርና ሌሎች የጣቢያው አካላትን ማሻሻል እንደሚያስፈልግ ኃላፊው አስገንዝበዋል። የጅማ ቁጥር ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ይልማ አበበ በበኩላቸው ጣቢያው እያንዳንዳቸው 63 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት አዉቶ ትራንስፎርመሮች እና የ25 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው አንድ ፖወር ትራንስፎርመር እንዳለው ገልፀዋል። በተጨማሪም አንድ ባለ 230 ጥምር ገቢ፣ አንድ ባለ 230 ጥምር፣ ሁለት ባለ 132 እና አምስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች አሉት። ጣቢያው በአሁኑ ወቅት በባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮቹ ለጅማ ከተማ ማህበረሰብ፣ ለጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ለውሃ አገልግሎት ተቋማት፣ ለአባ ጅፋር ቤተ መንግስት እና ለሰርቦ ከተማ እስከ 18 ሜጋ ዋት ኃይል በማሰራጨት ላይ ይገኛል። እንደ አቶ ይልማ ማብራሪያ የጣቢያው አውቶ ትራንስፎርመሮች እስከ 100 ሜጋ ዋት የመጫን አቅም ቢኖራቸውም የፖወር ትራንስፎርመሩ አቅም አነስተኛ በመሆኑ ያለውን አጠቃላይ አቅም በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል አልተቻለም። ስለሆነም በአካባቢው በፍጥነት እያደገ ለመጣው የኃይል ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት እና የቁጥር ሁለት አውቶ ትራንስፎርመሮችን ሙሉ አቅም ለመጠቀም የቁጥር አንድ ባለ 20 እና የቁጥር ሁለት ባለ 25 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመሮችን አቅም የማሳደግ ሼል በዕቅድ መያዙን የሥራ ኃላፊዎቹ ጠቁመዋል። ከዚህ ጎን ለጎን የቁጥር ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ የመቆጣጠሪያ ሥርዓትን በጂአይኤስ (GIS) ብሬከር ለማዘመን ዕቅድ ተይዟል። የማከፋፈያ ጣቢያዎቹ በአካባቢው መኖራቸው ስማርት ከተሞች እንዲመሠረቱ፣ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ እና ሰፊ የሥራ ዕድል እንዲፈጠር ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የገለፁት የሥራ ኃላፊዎቹ በቀጣይም ይበልጥ አስተማማኝና ያልተቋረጠ የኤሌክትሪክ ኃይል ለደንበኞች ለማቅረብ ከአገልግሎቱ ተቋሙ ጋር በቅንጅትና በትብብር እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአስተናጋጅ (Waiter) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በቁጥር አ.ኤ.ኃ/8.4/245/18 ሚያዚያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስ
+3
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአስተናጋጅ (Waiter) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በቁጥር አ.ኤ.ኃ/8.4/245/18 ሚያዚያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት ስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 የፅሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ  ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የስብሰባ አዳራሽ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም

በማከፋፈያ ጣቢያው የኃይል ፍላጎት በማደጉ የአቅም ማሳደግ ሥራ እየተከናወነ መሆኑ ተገለፀ ....///…. በአካባቢው ካለው የከተሞችና የኢንዱስትሪ መስፋፋት ጋር ተያይዞ በሚዛን ባለ 132 ኪሎ ቮልት
+6
በማከፋፈያ ጣቢያው የኃይል ፍላጎት በማደጉ የአቅም ማሳደግ ሥራ እየተከናወነ መሆኑ ተገለፀ ....///…. በአካባቢው ካለው የከተሞችና የኢንዱስትሪ መስፋፋት ጋር ተያይዞ በሚዛን ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ያለው የኃይል ጭነት በፍጥነት እያደገ መምጣቱን የጣቢያው ኃላፊ ወ/ሮ ፀጋነሽ ሞላ ተናግረዋል ማከፋፈያ ጣቢያው በአሁኑ ወቅት 6 ነጥብ 3 እና 25 ሜጋ ቮልት አምፒር ኃይል መሸከም የሚችሉ ሁለት ትራንስፎርመሮች ያሉት ሲሆን በ132 ኪሎ ቮልት የተቀበለውን ኃይል በስድስት ባለ 15 እና ባለ 33 እንዲሁም በአንድ ባለ 66 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች አማካኝነት እያቀረበ ይገኛል። የጣቢያው ኃላፊ እንዳብራሩት በሦስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ለሚዛን፣ ሸኮ፣ አማን ከተሞችና አካባቢዎቻቸው ኃይል የሚሰራጭ ሲሆን በ33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ደግሞ ለዲማ፣ ጨና 1 እና 2፣ ባቹማ፣ ሸዋ ቤንች ከተሞችና አካባቢዎች እስከ ጋምቤላ ክልል ድረስ ኃይል ያቀርባል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በማከፋፈያ-ጣቢያው-የኃይል-ፍላጎት-በማደ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም

የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ጣቢያ የካይዘን ሥርዓትን ተግባራዊ አደረገ ....///…. የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ብክነትን በመቀነስ የሥራ ቅልጥፍናን የሚያሳድገውን የካይዘን የአሠራ
+5
የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ጣቢያ የካይዘን ሥርዓትን ተግባራዊ አደረገ ....///…. የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ብክነትን በመቀነስ የሥራ ቅልጥፍናን የሚያሳድገውን የካይዘን የአሠራር ሥርዓት በተግባር ማዋል ጀመረ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ግርማ እንደገለፁት በጣቢያው የሚገኙ ልዩ ልዩ የመለዋወጫ ዕቃዎች በካይዘን ፍልስፍና መርሆዎች መሠረት በግምጃ ቤት ውስጥ በሥርዓት እንዲቀመጡና እንዲደራጁ ተደርጓል። ይህም ዕቃዎቹ ለአገልግሎት በሚፈለጉበት ወቅት ያለ ምንም እንግልትና ጊዜ ሳይባክን በቀላሉ ለማግኘት ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። ስለ አሠራሩ አስፈላጊነት አቶ ሀብታሙ ሲያብራሩ የካይዘን ሥርዓት መተግበሩ በጣቢያው የሚታዩ አላስፈላጊ የሀብትና የጊዜ ብክነቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት ይረዳል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የወላይታ-ሶዶ-ኮንቨርተር-ጣቢያ-የካይዘን 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙን ከተለያዩ የሕግና የፋይናንስ ስጋቶች ለመከላከል በትኩረት መስራት ይገባል ....///…. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ገቨርናንስ እና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈፃሚ ተቋሙን ከተለያዩ የ
+7
ተቋሙን ከተለያዩ የሕግና የፋይናንስ ስጋቶች ለመከላከል በትኩረት መስራት ይገባል ....///…. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ገቨርናንስ እና ኮምፕሊያንስ ሼል አስፈፃሚ ተቋሙን ከተለያዩ የሕግና የፋይናንስ ስጋቶች ለመከላከል በትኩረት መስራት እንደሚገባ አሳሰቡ። ይህ መልዕክት የተላለፈው ተቋሙ ለሕግ ባለሙያዎቹ በሕግና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ  ሥልጠና እንዲሰጥለት ለፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ባቀረበው ጥያቄ መሠረት በተዘጋጀው የሥልጠና ማጠናቀቂያ መርሃ-ግብር ላይ ነው። የኮርፖሬት ገቨርናንስ እና ኮምፕሊያንስ ሼል አስፈፃሚው አቶ ዱጉማ ነዳ ባስተላለፉት መልዕክት ሥልጠናው የሕግ ባለሙያዎቹ ከተቋሙ ነባራዊ ሁኔታና የቢዝነስ እንቅስቃሴዎች ጋር የተጣጣመ የላቀ የሕግ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል በእጅጉ ያግዛል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙን-ከተለያዩ-የሕግና-የፋይናንስ-ስጋ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም

የጣቢያው ሁለተኛ የግንባታ ምዕራፍ እየተከናወነ ነው ....///…. የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሁለተኛው የግንባታ ምዕራፍ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑን የፕሮጀክቱ አማካሪ ተወካይ ሪዚ
+9
የጣቢያው ሁለተኛ የግንባታ ምዕራፍ እየተከናወነ ነው ....///…. የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሁለተኛው  የግንባታ ምዕራፍ  በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑን የፕሮጀክቱ አማካሪ ተወካይ ሪዚደንት መሀንዲስ አስታወቁ:: ተወካዩ አቶ ሰለሞን ክንፈ እንደገለፁት የጣቢያው ግንባታ በሁለት ምዕራፎች የተከፈለ ሲሆን በመጀመሪያው ምዕራፍ 32 የንፋስ ተርባይኖችን በመትከል 80 ሜጋ ዋት ኃይል ማመንጨት ተችሏል። በአሁኑ ወቅት እየተከናወነ ባለው በሁለተኛው የግንባታ ምዕራፍ ደግሞ የ16 ተርባይኖች ተከላ ሼል እየተሠራ ይገኛል። ይህም ጣቢያው ተጨማሪ 40 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያመነጭ የሚያስችለው ሲሆን አጠቃላይ የማመንጨት አቅሙን 120 ሜጋ ዋት በማድረስ ሀገሪቱ በኃይል አቅርቦት ዘርፍ ለምታደርገው እንቅስቃሴ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የጣቢያው-ሁለተኛ-የግንባታ-ምዕራፍ-እየተ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም

ኢትዮጵያ - የምሥራቅ አፍሪካ የአረንጓዴ ኃይል አቅራቢ! የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል ድንበር የለውም። ተቋማችን ለአገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል ኃይል ከማመንጨት ባለፈ፣ ንፁህና ታዳሽ የሆነውን የኤ
ኢትዮጵያ - የምሥራቅ አፍሪካ የአረንጓዴ ኃይል አቅራቢ! የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል ድንበር የለውም። ተቋማችን ለአገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል ኃይል ከማመንጨት ባለፈ፣ ንፁህና ታዳሽ የሆነውን የኤሌክትሪክ ኃይል ለጎረቤት ሀገራት በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል። ሀገራችን የምታስተናግደው ኮፕ 32 (COP 32) ጉባኤ፣ ተቋማችን የአፍሪካን አህጉር ካርቦን የመቀነስ (Decarbonization) ጉዞ በግንባር ቀደምትነት እየመራ መሆኑን ያበስራል። ንፁህ ኃይልን በመሸጥ የውጭ ምንዛሬን እናሰባስባለን፤ የአየር ንብረት ብክለትንም በጋራ እንከላከላለን! ቀጣናዊ ትስስር በታዳሽ ኃይል ልማት! #RegionalIntegration #PowerExport #GreenAfrica #COP32 #EthiopianElectricPower 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም

ኢትዮጵያ - የምሥራቅ አፍሪካ የአረንጓዴ ኃይል አቅራቢ! የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል ድንበር የለውም። ተቋማችን ለአገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል ኃይል ከማመንጨት ባለፈ፣ ንፁህና ታዳሽ የሆነውን የኤ
ኢትዮጵያ - የምሥራቅ አፍሪካ የአረንጓዴ ኃይል አቅራቢ! የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል ድንበር የለውም። ተቋማችን ለአገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል ኃይል ከማመንጨት ባለፈ፣ ንፁህና ታዳሽ የሆነውን የኤሌክትሪክ ኃይል ለጎረቤት ሀገራት በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል። ሀገራችን የምታስተናግደው ኮፕ 32 (COP 32) ጉባኤ፣ ተቋማችን የአፍሪካን አህጉር ካርቦን የመቀነስ (Decarbonization) ጉዞ በግንባር ቀደምትነት እየመራ መሆኑን ያበስራል። ንፁህ ኃይልን በመሸጥ የውጭ ምንዛሬን እናሰባስባለን፤ የአየር ንብረት ብክለትንም በጋራ እንከላከላለን! ቀጣናዊ ትስስር በታዳሽ ኃይል ልማት! #RegionalIntegration #PowerExport #GreenAfrica #COP32 #EthiopianElectricPower 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም

ማመንጫ ጣቢያው የ9 ወራት ዕቅዱን 99 ነጥብ 1 በመቶ አሳካ ...///… የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 256 ነጥብ 11 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማምረት የዕቅዱን 9
+6
ማመንጫ ጣቢያው የ9 ወራት ዕቅዱን 99 ነጥብ 1 በመቶ አሳካ ...///… የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 256 ነጥብ 11 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማምረት የዕቅዱን 99 ነጥብ 1 በመቶ ማሳካቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ:: ሥራ አስኪያጁ አቶ ሙሉቀን ተሰማ እንዳስታወቁት ጣቢያው ባለፉት ዘጠኝ ወራት በ32 ተርባይኖች 258 ነጥብ 28 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማመንጨት አቅዶ 256 ነጥብ 11 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማምረት ችሏል። አፈፃፀሙ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ8 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ3 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት ማሳየቱንም ገልፀዋል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት የጣቢያው ዝግጁነት ወይም የአገልግሎት አሰጣጥ ደረጃ (Plant Availability) እና ኃይል ከሚያመነጨው አቅም አንፃር ጥቅም ላይ የዋለው (Utilization Index – UI) አፈፃፀም ከዕቅዱ በላይ መሆኑን አብራርተዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ማመንጫ-ጣቢያው-የ9-ወራት-ዕቅዱን-99-ነጥብ-1-በ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም

የአጋሮ ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ ሙሉ አቅም እንዳለው ተገለፀ የአጋሮ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው በየጊዜው እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት በአስተ
+5
የአጋሮ ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ ሙሉ አቅም እንዳለው ተገለፀ የአጋሮ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው በየጊዜው እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት በአስተማማኝ ሁኔታ በማሟላት ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ ሙሉ አቅም ያለው መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ የጣቢያው ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ሞሲሳ እንደገለጹት ማከፋፈያ ጣቢያው በ1980ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የነበረው የኃይል መጠን 132 ኪሎ ቮልት ብቻ ነበር። በወቅቱም በአንድ ባለ 16 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመር እና በሦስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች አማካኝነት ለአጋሮ ከተማና ለአካባቢው ውስን ማህበረሰብ ብቻ የኤሌክትሪክ ኃይል ያቀርብ እንደነበር አስታውሰዋል።  ይሁን እንጂ በአካባቢው በየጊዜው እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ተከትሎ በ2008 ዓ.ም ሰፊ የአቅም ማሳደግና የማስፋፊያ ሥራዎች ተከናውነውለታል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የአጋሮ-ማከፋፈያ-ጣቢያ-ተጨማሪ-ደንበኞች&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም

ያልተነካውን የፀሐይ ኃይል አቅማችንን ማልማት! ኢትዮጵያ ዐሥራ ሦስት ወራት ሙሉ የምታገኘውን የፀሐይ ብርሃን ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመቀየር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ግዙፍ የሶላር ፕሮጀክቶችን በ
ያልተነካውን የፀሐይ ኃይል አቅማችንን ማልማት! ኢትዮጵያ ዐሥራ ሦስት ወራት ሙሉ የምታገኘውን የፀሐይ ብርሃን ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመቀየር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ግዙፍ የሶላር ፕሮጀክቶችን በዕቅድ እየመራ ይገኛል። እነዚህ የአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆኑ ፕሮጀክቶች በኮፕ 32 መድረክ ላይ ለዓለም አቀፍ አጋሮች የሚቀርቡ ዋና ዋና ማሳያዎቻችን ናቸው። ታዳሽ ኃይልን ማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የምንጠቀምበት ዋናው ስትራቴጂያችን ነው። የተፈጥሮ ብርሃን ለሀገር ብልጽግና! #SolarPower #RenewableEnergy #CleanFuture #COP32Sustainable #EEP 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም

ከሜጋ ዋት በስተጀርባ ያሉት የብርሃን ታሪኮች! እኛ የምናመነጨው እያንዳንዱ ሜጋ ዋት የኃይል መጠን ደረቅ ቁጥር ሳይሆን በኢንዱስትሪዎቻችን ውስጥ ለሚሰሩ ወጣቶች የሥራ ዕድል፣ በጤና ተቋማት ውስጥ ለ
ከሜጋ ዋት በስተጀርባ ያሉት የብርሃን ታሪኮች! እኛ የምናመነጨው እያንዳንዱ ሜጋ ዋት የኃይል መጠን ደረቅ ቁጥር ሳይሆን በኢንዱስትሪዎቻችን ውስጥ ለሚሰሩ ወጣቶች የሥራ ዕድል፣ በጤና ተቋማት ውስጥ ለሚታደጉ ሕይወቶች ዋስትና፣ ለነገዋ ኢትዮጵያ ተስፋ ለሚሰንቁ ሕፃናት የብርሃን ምንጭ ነው! ኮፕ 32 በኢትዮጵያ መካሄዱ ሀገራችን የምታመነጨው አረንጓዴ ኃይል ማኅበራዊ ፍትሕንና የአየር ንብረት ጥበቃን እንዴት እያረጋገጠ እንደሚገኝ ለዓለም የምናስመሰክርበት ወሳኝ መድረክ ነው። ⚡️የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል - ሕይወትን በታዳሽ ኢነርጂ ማብራት! #HumanStory #Sustainability #CleanPower #COP32Ethiopia #EEPBrand #EmpoweringLives 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም

የአየር ንብረት ለውጥን የማይበግረው የምድር ውስጥ እንፋሎት ኃይል! የአየር ንብረት ለውጥ የውሃ መጠንን በሚቀንስበት ጊዜ እንኳ ያለምንም መቆራረጥ 24/7 አስተማማኝ ኃይል መስጠት የሚችለው የጂኦተር
የአየር ንብረት ለውጥን የማይበግረው የምድር ውስጥ እንፋሎት ኃይል! የአየር ንብረት ለውጥ የውሃ መጠንን በሚቀንስበት ጊዜ እንኳ ያለምንም መቆራረጥ 24/7 አስተማማኝ ኃይል መስጠት የሚችለው የጂኦተርማል (የምድር ውስጥ እንፋሎት) ኃይል የሀገራችን ሌላኛው ትልቅ አቅም ነው። ኢትዮጵያ በስምጥ ሸለቆ ውስጥ ያላትን ሰፊ የጂኦተርማል ኃይል አቅም በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አማካኝነት ወደ ልማት እያቀረበችው ትገኛለች። ኮፕ 32 ሀገራችን በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ (Climate-Resilient) የኃይል አማራጮችን በማስፋፋት ረገድ ያላትን ዓለም አቀፍ ተሞክሮ የምታጋራበት መድረክ ነው! ⚡️ የማይበገር አረንጓዴ ኃይል ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ! #GeothermalEnergy #ClimateResilient #CleanEnergy #COP32Ethiopia #EEP

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ .......///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጀንደርና ሶሻል አፌይርስ ኦፊሰር - 5ኛ (Gender and Social Affairs Expert V) የሥራ መደብ ላይ
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ .......///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጀንደርና ሶሻል አፌይርስ ኦፊሰር - 5ኛ (Gender and Social Affairs Expert V) የሥራ መደብ ላይ አወዳድሮ ለመቅጠር የካቲት 05 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የውጭ ማስታወቂያ መውጣቱ ይታወሳል፡፡ በመሆኑም የቀረበውን መስፈርት አሟልታችሁ የጽሁፍ ፈተና ከወሰዳችሁ መካከል ስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው አመልካቾች፤ ዕሮብ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ጠዋት 2፡30 ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው የተቋሙ ዋና መ/ቤት ለሚሰጠው የቃል ፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

1፡ ታሪካዊ ስኬት ለሀገራችን! ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP 32) ለማስተናገድ መመረጧ፣ በታዳሽ ኃይል ልማትና በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የደረሰችበትን የላቀ ደረ
1፡ ታሪካዊ ስኬት ለሀገራችን! ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP 32) ለማስተናገድ መመረጧ፣ በታዳሽ ኃይል ልማትና በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የደረሰችበትን የላቀ ደረጃ ያሳያል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከውሃ፣ ከንፋስ፣ ከፀሐይና ከእንፋሎት (Geothermal) 100% ንፁህና ለአየር ንብረት የማይበክሉ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በስፋት በመገንባት የሀገራችንን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ በግንባር ቀደምትነት እየመራ ይገኛል። ኮፕ 32 ተቋማችን የሚያመነጨውን ዘላቂ ኃይል ለዓለም አቀፍ ባለሀብቶችና ለአጋር ድርጅቶች ለማስተዋወቅ ትልቅ ድልድይ ነው! ኃይል ለኢትዮጵያ ብልጽግና፣ ንፁህ ኢነርጂ ለዓለም ደህንነት! #EthiopiaCOP32 #GreenEnergy #RenewablePower #EEP #CleanEnergy #ClimateAction 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ .......///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጀንደርና ሶሻል አፌይርስ ኦፊሰር - 5ኛ (Gender and Social Affairs Expert V) የሥራ መደብ ላይ
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ .......///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጀንደርና ሶሻል አፌይርስ ኦፊሰር - 5ኛ (Gender and Social Affairs Expert V) የሥራ መደብ ላይ አወዳድሮ ለመቅጠር የካቲት 05 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የውጭ ማስታወቂያ መውጣቱ ይታወሳል፡፡ በመሆኑም የቀረበውን መስፈርት አሟልታችሁ የጽሁፍ ፈተና ከወሰዳችሁ መካከል ስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው አመልካቾች፤ ዕሮብ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ጠዋት 2፡30 ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው የተቋሙ ዋና መ/ቤት ለሚሰጠው የቃል ፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

የእስልምና እምነት ተከታይ ለሆናችሁ የተቋማችን አመራሮችና ሰራተኞች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የአረፋ በዓል የታላቅ መስዋዕትነት፣ የጽናት፣ የሰ
የእስልምና እምነት ተከታይ ለሆናችሁ የተቋማችን አመራሮችና ሰራተኞች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የአረፋ በዓል የታላቅ መስዋዕትነት፣ የጽናት፣ የሰዋዊ መተሳሰብና ለላቀ ዓላማ የመገዛት ታላቅ ተምሳሌት ነው። ተቋማችን በሀገሪቱን እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት አስተማማኝና ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨትና በማስተላለፍ ረገድ ሀገራዊ ኃላፊነት በቁርጠኝነት እየተወጣ ይገኛል። ይህን ትልቅ ሀገራዊ ተልዕኮ ይበልጥ ወደ ላቀ ስኬት ለማሸጋገርእንደ በዓሉ እሴቶች ሁሉ የሁላችንም የጸና ቁርጠኝነት፣ የጋራ ትብብርና ሙያዊ መስዋዕትነት እጅግ አስፈላጊ ነው። ሀገራችንን የብርሐን ማማ ላይ ለማድረስ ቀን ከሌሊት ለምትተጉ መላው የተቋማችን አመራሮችና ሠራተኞች ለምታበረክቱት ተቋማዊና ሀገራዊ ውለታ ተቋሙ ታላቅ ክብርና እውቅና ይሰጣል። የዘንድሮው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል ለሀገራችን ሰላምና አንድነትን ለተቋማችን አዳዲስ ስኬቶችን ለሁላችንም ደግሞ የስራ ተነሳሽነታችንን የሚያድስ እንዲሆን ከልብ እመኛለሁ። ዒድ ሙባረክ! ኢ/ር አሸብር ባልቻ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም

የውጤት ማሳወቂያ ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት/Child Caregivers /የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በቁጥር ኢ.ኤ.ኃ/8.4/169/18 የካቲት 30
የውጤት ማሳወቂያ  ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት/Child Caregivers /የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በቁጥር ኢ.ኤ.ኃ/8.4/169/18 የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ አውጥቶ ሚያዚያ 13 ቀን 2018 ዓ.ም የፅሁፍ የተግባር ፈተና መሰጠቱ  ይታወቃል፡፡   ስሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከተራ.ቁ1 እስከ 5 የተገለጸው አመልካቾች ከግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5/አምስት/ ተከታታይ የስራ ቀናት ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ  á‹¨á‰ľáˆáˆ…áˆ­á‰ľ ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ማመንጫ ግድቦች በጥሩ የደህንነት ቁመና ላይ ይገኛሉ የኃይል ማመንጫ ግድቦች በአስተማማኝ እና በጥሩ የደህንነት ቁመና ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በተቋሙ ጀኔሬሽን
+4
የኃይል ማመንጫ ግድቦች በጥሩ የደህንነት ቁመና ላይ ይገኛሉ የኃይል ማመንጫ ግድቦች በአስተማማኝ እና በጥሩ የደህንነት ቁመና ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በተቋሙ ጀኔሬሽን ቢዝነስ የግድብ ደህንነት ክትትል እና ቁጥጥር ሼል አስኪያጅ አቶ ኤሊያስ ደላሽ እንዳስታወቁት የግድቦችን ደህንነት ለማረጋገጥና ሊከሰቱ ለሚችሉ ችግሮች አስቀድሞ የመፍትሔ እርምጃዎችን ለመውሰድ በግድቦችና ተያዥ አካላት ላይ በየጊዜው የክትትልና ቁጥጥር ሼል ይከናወናል፡፡   በዚህም ባለፉት አስር ወራት በመበልካ ዋከና፣ በግልገል ጊቤ አንድና ሁለት፣ ጊቤ ሶስት፣ ጢስ አባይ፣ ጣና በለስ፣ ቆቃ፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፣ ገናሌ ዳዋ፣ ተከዜ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እና በኮይሻ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ፕሮጀክት ግድብ እና ተያያዥ ህዳጎች ላይ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል፡፡   ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-ማመንጫ-ግድቦች-በጥሩ-የደህንነት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም