ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል 的分析概览
频道 ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል (@mkpublicrelation) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 50 977 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 1 084,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 621 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 50 977 名订阅者。
根据 22 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 509,过去 24 小时变化为 24,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 16.67%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.25% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 8 495 次浏览,首日通常累积 4 715 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 54。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 23 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
50 977
订阅者
+2424 小时
+1947 天
+50930 天
帖子存档
50 977
ዶ/ር አሸብር ጎግሌ አክለውም የግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዘመናዊ ትምህርት የተማረው የኅብረተሰብ ክፍል በአሁኑ ጊዜ ለሀገር የሚያስፈልገውን ብቁ ባላሙያ ማፍራት ብቻ ሳይሆን በሥነ ምግባሩ የቀና፣ ፈሪሃ እግዚአብሔር ያለው፣ ዘመኑን የዋጀ፣ ንቁ /መሪ/ ትውልድ በማፍራት ረገድ ማኅበሩ ከፍተኛ ሚናውን እየተወጣ የሚገኝ ሲሆን በዚህም የዛሬ ተመራቂዎችም በዚህ ሂደት ውስጥ ያለፋችሁ እንደመሆናችሁ መጠን የሚጠበቅባቸሁ ብዙ ነውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያቱ እንደነገራቸው ሁሉ እናንተም የዛሬ ተመራቂዎች ያለዋጋ የተቀበላችሁትን ያለዋጋ እንድትሰጡ የአደራ ምክራችንን እናቀርባለን በማለት መልእክት አስተላልፈዋል።
የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ''በተማራችሁበት ጸንታችሁ ኑሩ'' ሲሉ ተማሪዎች በመንፈሳዊም ሆነ በዘመናዊ ትምህርት ባገኙት ሙያ ቤተ ክንርስቲያንና ሀገራቸውን በትጋ ትና በቅንነት እንዲያገለግሉ አጽንኦት ሰጥተው አሳስበዋል።
በመጨረሻም መርሐ ግብሩ ለተማሪዎች የአደራ መስቀል ተሰጥቶ በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ አባታዊ ቡራኬና ቃለ ምዕዳን ተፈጽሟል።
ዘገባው በማኅበረ ቅዱሳን የወላይታ ሶዶ ማእከል ነው።
50 977
+2
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የኦቶና የጤና ሳይንስ እና የህክምና ኮሌጅ ግቢ ጉባኤ 95 ተማሪዎች መመረቃቸው ተገለጸ።
ሰኔ ፲፮/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን ወላይታ ሶዶ ማእከል ሥር ካሉት ግቢ ጉባኤያት አንዱ የሆነው የኦቶና የጤና ሳይንስ እና የሕክምና ካምፓስ ተማሪዎችን በአቡነ መልከ ጼዴቅ ቤተ ክርስቲያን ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም አስመርቋል።
በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ እንዲሁም የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሰላም ቀሲስ ቦክቻ ኤንጋ፣ ካህናትና ምእመናን ተገኝተዋል።
የወላይታ ሶዶ ማእከል ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር አሸብር ጎግሌ ማኅበረ ቅዱሳን ከተመሠረተበት ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት (በዩኒቨርሲቲዎች እና በኮሌጆች) የሚማሩ ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶችን በሥሩ በማደራጀት፣ የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ ሥርዓት፣ ትውፊት በማስተማር ለግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ሥርዓተ ትምህርት እና መማሪያ መጻሕፍትን በማዘጋጃት፣ መምህራንን በመመደብ እና ቦታ በማመቻቸት እያስተማረ በርካታ ተማሪዎችን በአባቶች ቡራኬ ሲያስመርቅ ቆይቷል፣ አሁንም በማስመረቅ ላይ ይገኛል በማለት የገለጹ ሲሆን የተመረቁትም ራሳቸውን እና ቤተሰቦቻቻውን፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እንዲሁም ሀገራቸውን በማገልገል ላይ ናቸው ብለዋል።
50 977
"ግቢ ጉባኤያት ለሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት" በሚል መሪ ቃል ቅዳሜ ሰኔ 20 ከ12:00 ሰዓት ጀምሮ የቀጥታ ስርጭት መርሐ ግብር በማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ይጠበቁን።
በቀጥታ ስርጭቱ እየገቡ የግቢ ጉባኤ ትዝታዎን ያካፍሉ ።
50 977
+2
የአዲስ አበባ ማእከል 500 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች መመረቃቸውን ገለጸ።
ሰኔ ፲፭/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዋና ክፍል ቅዱስ ገብርኤል ማስተባበሪያ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ ሲያስተምራቸው የነበሩ የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች በደብረ ጽጌ ፋንታ ቅድስት አርሴማ ወቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን ማስመረቁን የማስተባበሪያው ኃላፊ አቶ ተሾመ ሙሉጌታ ገለጸዋል።
በዕለቱም ትምህርተ ወንጌል በመጋቤ ሐዲስ መምህር ጥላሁን ታዬ ፣መዝሙርና ወረብ በተመራቂ ተማሪዎች የቀረበ ሲሆን የደብሩ አስተዳዳሪና ካህናት ፣የማእከሉ ሰብሳቢና የማእከሉ ጽ/ቤት ኃላፊ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ሰብሳቢ ዲ/ን ኃይለ ማርያም መድኅን እንኳን አደረሳችሁ በማለት የማኅበሩን መልእክት ያስተላለፋ ሲሆን በመልእክታቸውም በብዙ ውጣ ውረድ አልፋችሁ ለዚህ ለምረቃ ዕለት በመድረሳችሁ እንኳን ደስ አላችሁ እያልን በቀጣይ ጉዟችሁ ቤተሰብን፣ ቤተ ክርስቲያንንና ሀገርን እንድታገለግሉ አደራ እንላለን በማለት ለተመራቂዎች አደራ ብለዋል።
በመጨረሻም ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች የዕውቅናና የምስክር ወረቀት እንዲሁም ለሁሉም የግቢ ጉባኤው ተመራቂዎች የአደራ መስቀል ተሰጥቷል።
ዘገባው በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ነው።
50 977
በማኀበረ ቅዱሳን የወላይታ ማከእል ትምህርትና ዜማ አገልግሎት ክፍል ተወካይ ዲ/ን ወደፊት አላቸው ባስተላለፉት መልእክት ላለፉት ስምንት ወራት የበገና ተማሪዎችን ለማስተማር ብቃት ያላቸው መምህራንን መድበው መቆየታቸውን ገልጸው የዜማ ትምህርት ቤቱ ቅርንጫፎቹን አሳድጎ ለብዙዎች ተደራሽ እንደሆነ ገልጸዋል።
የትምህርት እና ዜማ አገልግሎት ክፍል ተጠሪው አክለውም በገና ተምረው የሚመረቁ በርካታ ቢሆኑም ነገር ግን በአገልግሎት ለመጽናት ግን መንፈሳዊነትና ትጋት ይጠይቃል በማለት ሲያስተምሩ የነበሩ መምህራንን እና የአገልግሎት ዘርፍ አስተባባሪዎችን አመስግነዋል።
በመጨረሻም የዜማ እና ኪነ ጥበብ ተመራቂዎቹን በማእከሉ መዝሙር ክፈሉ ውስጥ አባል ሆነው ጠንክረው በአገልግሎት እንዲቀጥሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ዘገባው የማኅበረ ቅዱሳን ወላይታ ሶዶ ማእከል ነው።
50 977
+1
የወላይታ ሶዶ ማእከል ለ8 ወራት ያስተማራቸውን 45 የበገና ዘማርያንን አስመረቀ።
ሰኔ ፲፭/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን ወላይታ ሶዶ ማእከል በልማት ተቋም ሥር ለ8 ወራት ሲያስተምራቸው የቆዩ 45 የበገና ዘማርያንን በወላይታ ሶዶ በኦቶና ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም አስመረቋል።
በመርሐ ግብሩ የወላይታ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሰላም ቀሲስ ቦክቻ ኤንጋ፣ የኦቶና ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ አርያም ዮሐንስ አያሌው የተገኙ ሲሆን የበገና ዝማሬ እና የማኅበረ ቅዱሳንን መልእክት ቀርቧል።
በማኅበረ ቅዱሳን የወላይታ ሶዶ ማእከል ጸሐፊ ዲ/ን እርዳቸው ዮሴፍ በመልእክታቸው ማኅበረ ቅዱሳን በመዝሙርና በዜማ መሣሪያዎች ትኩረት አድርጎ በመሥራት ላለፉት አሥርት ዓመታት የበገናና የመሰንቆ ዘማርያንን አሠልጥኖ ማስመረቁን ጠቅሰው ወላይታ ሶዶ ማእከልም የበኩልን ድርሻ በመወጣት በዕለቱ የተመረቁትን 45 የበገና ዘማርያን ጨምሮ ከ1500 በላይ የበገናና የመሰንቆ ዘማርያንን አስተምሮ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን አበርክቷል ብለዋል።
ጸሐፊው አክለውም የሠለጠኑትን የበገና ዜማ መሣሪያ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ብቻ እንዲያውሉ አጽንኦት በመሥጠት ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
50 977
✝️የጾም ቁርሳችን፣
ለወገኖቻችን✝️ +++
በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች እያጋጠሙ ባሉ ማኅበራዊ ቀውሶች( ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች፣ መፈናቀልና ጦርነት ) ብዙ ወገኖቻችን ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል።
እርስዎም ለእነዚህ ወገኖች የጾም ቁርስዎን በመለገስ ቸርነትን ያድርጉ!
ድጋፍ ለማድረግ :-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በወገን ፈንድ ፡- https://Www.wegenfund.com/mknu መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት
50 977
በማኀበረ ቅዱሳን የታርጫ ማእከል ሰብሳቢ የሆኑት መ/ርት መድኃኒት አለማየሁ ማኀበረ ቅዱሳን ዋናዉ ማእከል በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር በተለይ በአውሮፓ የሚገኙ በጎ አድራጊ ምእመናንን በማስተባበር ከ600 ሺ ብር በላይ ለደቀ መዛሙርቱና ለመምህሩ ድጎማ በማድረግ ደቀ መዛሙርቱ ለዚህ ደረጃ እንዲደርሱ ላበረከተው አስተዋጽኦ አመስግነው ለተመራቂ ደቀ መዛሙርት እና ቤተሰቦቻቸው የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
በዚህ የምርቃት መርሐ ግብር የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ለሁሉም ተመራቂ ደቀ መዛሙርት የመጽሐፍ ቅዱስ ስጦታ ሰጥተዋል።
ሀገረ ስብከቱም ማኀበረ ቅዱሳን ዋናዉ ማእከል እና ታርጫ ማእከል ላበረከቱት አስተዋጽኦ የምስጋና ምስክር ወረቀት አበርክቷል።
ማኅበረ ቅዱሳን የታርጫ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አብነት ት/ቤትን ገንብቶ ጥር 23 ቀን 2016 ዓ.ም ለሀገረ ስብከቱ ማስረከቡ ይታወቃል።
ዘገባው በማኅበረ ቅዱሳን ታርጫ ማእከል ነው።
50 977
+4
ማኅበረ ቅዱሳን ያስተማራቸውን ደቀ መዛሙርት ማስመረቁ ተገለጸ።
ሰኔ ፲፬/፳፻፲፰ ዓ.ም
ማኀበረ ቅዱሳን በዳዉሮ ሀገረ ስብከት ታርጫ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አብነት ት/ቤት ለሁለት ዓመታት ያስተማቸራቸውን አስር ደቀ መዛሙርት ሰኔ 12/2018 ዓ/ም አስመርቋል፡፡
በምርቃት መርሐ ግብሩ ተገኝተው ቃለ በረከት የሰጡት የዳዉሮ፤ ኮንታ፣ ከምባታ፣ ጠምባሮ እና ሀላባ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ “በአሁኑ ጊዜ በሀገረ ስብከታችን የአገልጋይ ካህናት እጥረት በመኖሩ ቤተ ክርስቲያን ችግር ላይ ናት ያሉ ሲሆን ተመራቂ ደቀ መዛሙርት ኃላፊነት እንዳለባቸዉ በመግለጽ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል’’፡፡
አክለዉም “ ማኀበረ ቅዱሳን የዛሬ 34 ዓመት ሲመሠረት በእግዚአብሔር ዓላማ የተቋቋመ መሆኑን ዛሬ በተግባር አረጋግጠናል” ብለዋል፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን ቤተ ክርስቲያንን የመጠበቅ፣ ወንጌልን ለምእመኑ የማዳረስ፣ አብነት ት/ቤቶችን የማስፋፋት፣ ተተኪ መምህራነ ወንጌልን የማፍራት፣ የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን የመክፈትና የጠፉትን የመመለስ ዋና ሥራዉ በመሆኑ በእኛ ሀገረ ስብከት ይህንን በተግባር አሳይቶናል ሲሉ ብፁዕነታቸው ጨምረው ተናግረዋል።
ማኀበሩን በመደገፍ እና ተቀናጅቶ በመሥራት አገልግሎለቱን የማጠናከርና የማስፋት ግዴታን መወጣት እንደሚገባ ተመላክቷል ፡፡
50 977
ዐውደ ትሩፋት || ኦርቶዶክሳዊ የምክክር ተቋም ለማቋቋም የተደረገ ውይይት https://youtu.be/5h_quFBrzW8?si=YJWvdOUAbE2IJyea
50 977
ከዚህ በኋላ ባለ ጠጋው ከሄደበት በተመለሰ ጊዜ በደስታ የሆነውን የመሰንቆና የእንዚራ ድምፅ ሰምቶ ‹‹ይህ የምሰማው ምንድነው›› ብሎ ጠየቀ፡፡ እነርሱም ‹‹ስሙ ባሕራን ለተባለ የአንተን ደብዳቤ ላመጣ ጐልማሳ ሰው ልጅህ ዕገሊትን አጋቡት፡፡ እነሆ ዓርባ ቀናት በሰርግ ላይ ነው፡፡ ገንዘብህንና ጥሪትህን ሁሉ ወንዶችና ሴቶች ባሮችህን አንተ እንዳዘዝህ ሰጥተውታል›› አሉት፡፡ ይህንም በሰማ ጊዜ ደንግጦ ከፈረሱ ላይ ወደቀ በድንገትም ሞተ፡፡
ባሕራንም ከዚህ በኋላ የቅዱስ ሚካኤልን ዝክር በሚገባ እየዘከረና ለቤተ ክርስቲያኑም እየታዘዘ የሚያገለግል ሆነ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዓሉን በሚገባ አክብረን በረከት እንድንቀበል ይርዳን፤ የቅዱስ ሚካኤል የረድኤቱ ኀይል በሀገራችን በሃይማኖታቸው ምክንያት ለከተሠውት የክርስቲያን ወገኖች ጋር ይሁን፤ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
ምንጭ፡– ድርሳነ ቅዱስ ሚካኤል፣ ስንክሳር ዘወርኃ ሰኔ
50 977
ሚካኤል ማለት በዕብራይስጥ ቋንቋ ሚ-መኑ፣ካ-ከመ፣ኤል-አምላክ መኑ ከማከ አምላክ? እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው? ማለት ነው።(ኪ.ወ.ክ)።
ቅዱስ ሚካኤል ዲያብሎስ በትዕቢቱ ፈጣሪነትን ሽቶ በዓለመ መላእክት ሁከት ባስነሣ ጊዜ የቅዱሳን መላእክት ፊታውራሪ ሆኖ ዲያብሎስን የተዋጋ ጽኑዕ መልአክ ነው።
"በሰማይም ሰልፍ ሆነ ሚካኤልና መላእክቱ ዘንዶውን ተዋጉት፣ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ አልቻላቸውም። ከዚያም ወዲያ በሰማይ ሥፍራ አልተገኘላቸውም።"(ራእይ ፳፪:፯)
ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት ነው። ይሁዳ በመልእክቱ "የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በማለት ሊቀ መላእክትነቱን ገልጾአል። (ይሁዳ ፱)
ይህችውም ቅሩበ መንበር ተደርጎ የተፈጠረው ዲያብሎስ የተዋት ክብሩ ናት።
ቅዱስ ሚካኤል ይቅር የሚል ከመዓት የራቀ ነው።(ሄኖ፥፲፥፩፪)
ለሰው ባደረገው በጎነት ለሕዝቡ ሁሉ ታዛዥ ነው። የቅዱስ ሚካኤል ሹመት በነገደ መላእክት ላይ ብቻ አይደለም፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሆኑት ላይ ጭምር ነው፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል፣ ለእኛ ለሰዎች አማላጅ ሲሆን ለቅዱሳ ጻድቃንና ሰማዕታት ደግሞ አጋዣቸው ነው፤ በሕይወታቸውና በተጋድሏቸውም እስከ መጨረሻው ይረዳቸዋል፡፡
ይህንንም በቤተ ክርስቲያናችን በመጽሐፈ ስንክሳር እና በድርሳነ ሚካኤል ሰኔ ፲፪ ቀን ተጽፎ እናገኘዋለን። ይህም ቀን መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ተከብሮ የሚውልበት ታላቅ ዕለት ነው፡፡ በእስክንድርያ ከተማ ክላወባጥራ የተባለች ንግሥት የበጥሊሙስ ልጅ ዙሐል በሚባል ኮከብ ስም ያሠራችው ታላቅ ምኲራብ ነበር፤ ሕዝቡም ሰኔ በገባ በዐሥራ ሁለት የዚህን ጣዖት በዓል ያከብሩ ነበር። ይህንንም ግብራቸውን እንዲተው አባታችን እለ እስክንድሮስ ቢነግራቸው አይሆንም አሉት።
በኋላም ጻድቅ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ሲነግሥ አብያተ ክርስቲያናት ይትረኃዋ ወአብያተ ጣዖታት ይትአጸዋ የሚል አዋጅ ስለወጣ በዚህ ምቹ ጊዜም የጣዖት አምልኮ እንደምን ያለ ክፉ ግብር እንደሆነና በጎ ዋጋም እንደሌለው ነግሮ እንዲተዉ ቢጠይቃቸው እኛስ ይህን አንተውም አሉት። እርሱም በጥበብ እንዲህ አላቸው፤ ‹‹ይህን ግብር ብትተው በዚህች ቦታ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልን ቤተ ክርስቲያን እንሠራለን። መሥዋዕታችሁንም በዚያ ለቅዱስ እግዚአብሔር ታቀርባላችሁ አላቸው።›› በዚህ ተደስተው ተመለሱና ያንን የጣዖት ቤት አፍርሰው እጅግ ያማረች ቤተ ክርስቲያንን በመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ስም ሠሩ። የመልአኩንም በዓለ ንግሥ በዚህች ዕለት አከበሯት። ከዚያን ጊዜም ጀምሮ የከበረ የመላእክት አለቃ የመልአኩ የሚካኤል የመታሰቢያውን በዓል በሰኔ ዐሥራ ሁለት ቀን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይከበራል፡፡ዳግመኛም ንዑድ ክቡር የሚሆን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ባሕራንን በሰኔ ዐሥራ ሁለት ቀን ያዳነበት ድንቅ ተአምርም ይህ ነው። አንድ ደግ ሰው በዚያች ሀገር ይኖር ነበር። ክፉ ጎረቤትም ነበረው። ይህም ደግ ሰው ነዳያንን እጅግ የሚወድ የቅዱስ ሚካኤልንም ዝክር ሳያስታጉል የሚዘክር ሰው ነው። በዚህ ሥራው ግን ይህ ክፉ ጎረቤቱ ይዘብትበት ነበር። በኋላም ያ ደግ ሰው የሚሞትበት ቀን ሲደርስ ሚስቱን ዝክረ ሚካኤልን እንዳታቋርጥና ነዳያንን እንዳትዘነጋ ነግሯት ያርፋል። እርሷም ፀንሳ ነበርና እርሱ ከሞተ በኋላ የመውለጃዋ ጊዜ ደረሰ። ምጥም ቢጠናባት ወደ መልአኩ ጮኸች፤ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤልም ተራዳትና መልከ መልካም የሆነ ወንድ ልጅ ወለደች። መልአኩም እንዲህ አላት። ‹‹ልጅሽ የዚህ የጎረቤትሽን ሀብት ይወርሳል።›› መልአኩም ለጎረቤታቸው ጆሮውም ከፍቶለት ነበርና ይህን ነገር ሰማ። በዚህም ‹‹በምን ምክንያት ወስጄ ላጥፋው›› ብሎ ሲያስብ ሴቲቱ ልጅዋን ብቻዋን ለማሳደግ ተቸገረች፤ ‹‹ላሳድግልሽ፤ ለአንቺም ይኸው ገንዘብ እሰጥሻለሁ›› ብሎ ብዙ ወርቅ ሰጣት። እርሱም ‹‹ከእንግዲህ አርፋለሁ›› ብሎ ልጁን መጣያ ሳጥን ያዘጋጅና ወደ ባሕር ቢጥለው ባሕሩም ሩቅ ሀገር ወስዶት ከዳር ይጥለዋል።
ከዚህም በኋላ አንድ በጎቹን ያሠማራ ሰው ያገኘዋል። ያንንም ሳጥን ወስዶ ከቤት ያኖረዋል፤ በምን መክፈት እንደሚችል ሲያስብ ዳግመኛ ወደ ባሕሩ እንዲሄድ እግዚአብሔር ሐሳብ ያሳድርበትና ተነሥቶ ይሄዳል። ሲሄድም ዓሣ አጥማጅ ያገኝና ዓሣ ለእርሱና ለቤተሰቡ እንዲያጠምድለት ይነግረዋል። ያም ዓሣ አጥማጅ ሲያጠምድ ታላቅ ዓሣ አገኘና ሰጠው። ዋጋውን ሰጥቶም ወደ ቤት ተመለሰና ሆዱን ቢሰነጥቀው ቁልፉን በዚያ አገኘው። በዚያም ሳጥኑን ቢከፍት መልከ መልካም ልጅ አገኘ። ልጅም ስላልነበረው እጅጉን ተደሰተ። ባሕራን ብሎም ሰየመው።
ከብዙ ጊዜያት በኋላ ያ ክፉ ሰው ከንግድ ተመልሶ በዚያ መንገድ ሲያልፍ መሸበትና ከዚህ ሰው ቤት አደረ። ባሕራንንም ተመለከተውና ሰውየውን ልጁ እንደሆነ ለማወቅ ታሪኩን ጠየቀው፤ ሰውየውም የሆነውን ሁሉ ነገረው። ክፉ ሰውየውም ልጁ እንዳልሞተ ባወቀ ጊዜ ደነገጠና መልእክት ሊልከው ስለሚፈልግ የባሕራንን አባት ልጁን እንዲሰጠው ጠየቀው። እርሱም ተስማምቶ ሰጠው። በክፋትም ተነሣሥቶ ባሕራንን እንዳገኘው እንዲገድለው ለአገልጋዩ ደብዳቤ ጽፎ አገልጋዩና እርሱ ብቻ የሚያውቁትን ማኅተም አድርጎ ሰጠው። ‹‹ይቺን ደብዳቤ በምታነባት ጊዜ ደብዳቤዋን ይዞ የመጣውን ገድለህ በጉድጓድ ውስጥ ጣለው፡፡ ማንም እንዳያውቅ›› ለባሕራንም ለመንገዱ የሚሆነውን ስንቅ ሰጠው፡፡
የራሱን የሞት ደብዳቤ እንደያዘ ሳያውቅ ባሕራን ወደ ታዘዘበት ሥፍራ ተጓዘ፤ ከዚያ ሰው ቤት ለመድረስ ሲቀርብ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል በንጉሥ ጭፍራ አምሳል በነጭ ፈረስ ላይ ተቀምጦ ‹‹አንተ ጐልማሳ የያዝኸው ምንድነው›› አለው፡፡ ‹‹ወደ ዕገሌ ሀገር ወደ ቤቱ ለማድረስ ከአንድ ባለ ጠጋ የተጻፈች መልእክት ናት›› አለው፡፡ ‹‹ያቺን ደብዳቤ አሳየኝ›› አለው፤ እርሱም ስለ ፈራ ሰጠው፡፡ የሞቱን ደብዳቤ ያቺን የሞት መልእክት ደምስሶ በሕይወት ቀየረለት። በእርሱም ፈንታ በንፍሐት ለውጦ እንዲህ ብሎ ጻፈ፤ ‹‹ይቺን ደብዳቤ ይዞ ለመጣ ባሕራን ለሚባል ሰው ይቺ ደብዳቤ ደርሳ በምትነበብበት ጊዜ ልጄ ዕገሊትን አጋቡት፡፡ በውስጥና በውጭ ያለ ንብረቴንና ጥሪቴን፣ ወንዶችና ሴቶች ባሮቼን፣ ጠቅላላ ንብረቴንም አውርሼዋለሁና የፈለገውንም ሊያደርግ ሥልጣን ሰጥቼዋለሁና እኔን አትጠብቁኝ፡፡ እኔ ብዙ እዘገያለሁ የኔ ሹም እገሌ ሆይ! በእኔና በአንተ መካከል ይቺ ምልክት እነኋት፡፡››
አሽጐ ለባሕራን ሰጠውና ‹‹ወደ ባለ ጠጋው ቤት ሂደህ ይቺን ደብዳቤ ለሹሙ ስጠው፡፡ በጎዳናም እኔ እንደ ተገናኘሁህ አትንገረው፡፡ እንዳይገድልህም ይህን የሞት ደብዳቤ ለውጬልሃለሁ›› አለው፡፡ ባሕራንም ‹‹እሺ ጌታዬ ያዘዝኸኝን ሁሉ አደርጋለሁ›› አለ፡፡
ባሕራንም ወደ ባለ ጠጋው ቤት በደረሰ ጊዜ ያቺን ደብዳቤ ለሹሙ ሰጠው፡፡ ካነበባት በኋላም በመካከላቸው ያለውን ምልክት አገኘ፡፡ አስተውሎም እርግጠኛ እንደ ሆነ ዐወቀ፡፡ ለባሕራን ሰርግ አዘጋጅቶ እንደሚገባ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት በተክሊል የባለ ጠጋውን ልጅ አጋቡት፡፡ ዓርባ ቀን ያህልም ደስታና ሐሴት እያደረጉ ኖሩ፡፡ ሀብቱንም ሁሉ አወረሱት።
50 977
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
‘’ከመላእክት አለቆች አንዱ የሆነው ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ።’’ (ት.ዳን. ፲ ፥፱)
እንኳን ለቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ‼️
በዓል “አብዐለ” አከበረ÷ አበለጠ÷ ዕለትን በዓል አደረገ ከሚለው ግስ የወጣ ስም ነው። ይህም የደስታ፥የዕረፍት ቀን ፥በዓመት በወርና በሳምንት የሚከበር፥ ያለፈ ድርጊት የሚታወስበትና ምእመናን የበዓሉን ምሥጢር እያሰቡ ሐሴት የሚያደርጉበት ማለት ነው:: ዕለቱም ምእመናን መደበኛ ሥራቸውን ትተው ለበዓሉ ይገባዋል የሚሉትን ተግባር የሚፈጽሙበት የበዓሉን ባለቤት እግዚአብሔርንና የበዓሉን ምክንያት እያሰቡና እያመሰገኑ ደስ የሚሰኙበት ነው። ቅዱስ ዳዊት “….በዓልን የሚያደርጉ ሰዎች በምስጋናና በደስታ ቃል ሲያመሰግኑ ተሰሙ:: ”(መዝ ፵፩፥፬፡፡) እንዳለው። በዓላት የዕረፍት ቀናት ናቸው ማለት ከሥጋዊ ወይም ምድራዊ (ዓለማዊ) ሥራዎች የሚያርፉባቸው ናቸው ለማለት ነው። በአንጻሩ ግን መንፈሳዊ ሥራዎች ሁሉ እንደየችሎታ የሚከናወንባቸው መሆናቸው መረሳት የለበትም፡፡ እነዚህ ዕለታት እግዚአብሔር በራሱ ወይም በቅዱሳኑ አድሮ ለሠራቸው ድንቅ ሥራዎች (ተአምራት) መታሰቢያዎች ናቸው። (መዝ፻፲፥፬)፡፡ ፻፲፩፥፮፡፡ ሉቃ፳፪፥፲፱፡፡)
በበዓሉ ዋዜማ ለዕለቱ የተሠራውን የምስጋና ቃል እየመሩ፣ እየተመሩ፣ እያነሡ፣ እየዘመሙ፣ መስተብቁዕ እየደገሙ፣ እያመረገዱ፣ እያመለጠኑ፣ እየጸፉ ሊቃውንቱ እግዚአብሔርን ያመሰግናሉ። በዚህ መልኩ ከሚከበሩ ዐበይት በዓላትም አንዱ በዓለ ቅዱስ ሚካኤል ነው።
50 977
"ግቢ ጉባኤያት ለሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት" በሚል መሪ ቃል ቅዳሜ ሰኔ 20/2018 ዓ.ም ከ12:00 ሰዓት ጀምሮ የቀጥታ ስርጭት መርሐ ግብር በማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ይጠበቁን።
50 977
#በትምህርተ ሃይማኖት ዐምድ ሥር “# የራሳችሁን መዳን ፈጽሙ " በሚል ዐቢይ ርእስ ስለ አዳም አወዳደቅ ፣አዳም ወደቅ ስንል ምን ማለት እንደሆነ ፤ እግዚአብሔር ሰውን እንዴት እንደአዳነው፣ ሰው ከምን እንደዳነ ፤ለመዳን ምን እንደሚያስፈልግ የሊቃውንት መጽሐፍ በማጣቀስ ትምህርት ይሰጣል ።
#ዐቢይ ጉዳይ ዐምድ ሥር ደግሞ “# የሥርዓተ ምንኵስና ቀኖናዊ መሠረቶች፣ ተግዳሮቶችና ተቋማዊ መፍትሔ ዎቹ " ክፍል አንድ" በሚል ርእስ የምንኵስና አምላኪዊ መሠረትና ታሪካዊ ፋፈይዳ፤ የዘመናችን የምንኵስና ተግዳሮትና ተቋማዊ ቀውስ በተመለከተ በዝርዝር ያሳያል ።
• #ክርስትና በማኀበራዊ ዐምድ ሥር ደግሞ "#በጋብቻ ውስጥ የሚታዩ ችግሮችና መፍትሔዎቻቸው " ክፍል ፩ በሚል ርእስ ዐቢይ ርእስ በመልአከ ሰላም ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራው ጋብቻ እንዴት እንደተጀመረ፤ የጋብቻ ዓላማዎች፤ በትዳር ውስጥ ጎልተው የሚታዩ ችግሮች በሚል ሰፊት ትምህርት ታሰተምራለች።
• #በእናስተዋውቃችሁ ዐምድ ሥር “#
የጥንቷ «አናቶሊያ» የክርስትና መልክና
የዘመናት ማዕበል ክፍል አንድ " በሚል ርእስ የዛሬዋ ቱርኪዬ ሪፐብሊክ የነበረችበትን ሁኔታዎች ፤የዘመናዊቷ ቱርክ ምሥረታ እና የዛሬዋ እውነታ በስፋት ታስቃኛለች ።
• #በነገዋ ቤተ ክርስቲያን #ዐምድ ሥር “ በውጭ ሀገር ያለችው ቤተ ክርስቲያን ዕድገት፣ አሁናዊ ዕድሎችና ተግዳሮቶች ክፍል አንድ " በውጭ ያለችው ቤተ ክርስቲያን የምታስተናግዳቸውን መሠረታዊ ችግሮች በስፋት ይዛለች ።
#በኪነ ጥበብ ዐምድ "#የታቦት ትከሻዎች "በሚል ርእስ ታስነብባለች ።
• #የጥያቄዎቻችሁ መልስ ዐምድ “የክርስትና ጉዞ በቱርክ ጥንታዊና አሁናዊ ሁኔታ # ክፍል ፩ " በሚል ርእስ #በቅርቡ ጥንት የክርስትና ማእከል በመሆኗ ታላላቅ የቤተ ክርስቲያን ጉባኤያት ተካሂደውባት
ወደ ነበረችው ቱርክ የጉባኤ ቤት መምህራን ተጉዘው ነበር፡፡ በዚህም መሠረት ባደረጉት ጉብኝት የተመለከቱትንና የተረዱትን ያካፍሉን ዘንድ የመጻሕፍተ ሐዲሳት መምህር የሆኑትን መምህር ኀይለ ማርያም ዘውዱን ጋብዘናል፡፡ ያካፍሉን ዘንድ የመጻሕፍተ ሐዲሳት መምህር የሆኑትን መምህር ኀይለ ማርያም ዘውዱን ጋብዘናል፡፡
ሐመር መጽሔት ፴፫ኛ ዓመት ቍጥር ፮ በማሰራጨት ፡በማንበብና በማስነበብ የድርሻችን እንወጣ !
Magazine @eotcmk.org #ሐመር #መጽሔትበ ዝግጅት ክፍል
50 977
ሐመር መጽሔት የሴኔ ወር እትም እንዳታመልጣችሁ
".. # ለምንኵስና የሚያስፈልገውን መንፈሳዊ ብስለት፣ የሥነ መለኮት ዕውቀትና ሥነ ልቡናዊ ዝግጁነት የሌላቸውን ሰዎች ያለ በቂ ማጣራት በችኮላ ማመንኮስ የተለመደ ሆኗል።" ሰኔ ዕትም በ፳፻፲፰ ዓ.ም ዐቢይ ጉዳይ ዐምድ ✍️
༺ ༻
#የኅትመት ዘመን ፦#ሰኔ ፳፻፲፰ ዓ.ም
#አዘጋጅ ፦በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን በሚዲያ አገልግሎት ተቋም በመጽሔት ዝግጅት ክፍል የሚዘጋጅ ትምህርታዊ መጽሔት
• ገጽ ብዛት፦፳፰
ዋጋ ፦፵ ብር
•ሐመር መጽሔት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት ሥርዓትና ትወፊት ጠብቃ በሚዲያ አገልግሎት ተቋም በመጽሔት ዝግጅት ክፍል የሚዘጋጅ ትምህርታዊ መጽሔት በየወሩ የምትወጣ መንፈሳዊ መጽሔት ናት፡፡
•ሐመር መጽሔት ፴፫ኛ ዓመት ቍጥር ፮
ሰኔ ፳፻፲፰ ዓ.ም. ዓ.ም መልእክት ዘማኅበረ ቅዱሳን " ለነገው ትውልድ አስበን እንሥራ ›› በሚል በቅብብሎሽ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የመጣው የአብነት ትምህርት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየተመናመነ በመምህራንና ተማሪዎች እጥረት ምክንያት በበርካታ ቦታዎች፣ በተለይም በገጠሪቱ ኢትዮጵያ
የተዘጉና የመዘጋት አደጋ እያንዣበበባቸው፡ መሆኑን ይጠቁማል ።
.#ዐውደ ስብከት ሥር” # ‹‹ጾምን ቀድሱ ፤ ጉባኤውንም ዐውጁ›› ” በሚል ርእስ ፣የጾም መሠረታዊ ጥቅሞች ፤የሐዋርያት ጾምስያሜና ቀኖና ዐዠበስፋት ታስነብባለች።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
