ar
Feedback
ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል

ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል

الذهاب إلى القناة على Telegram

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል

تُعد قناة ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል (@mkpublicrelation) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 51 383 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 065 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 618 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 51 383 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 12 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 689، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 27، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 13.95‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 7.73‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 7 167 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 3 973 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 55.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

وصف القناة غير متوفر.

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 13 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

51 383
المشتركون
+2724 ساعات
+1437 أيام
+68930 أيام
أرشيف المشاركات
• #ክርስትና በማኀበራዊ ዐምድ ሥር ደግሞ "#በጋብቻ ውስጥ የሚታዩ ችግሮችና መፍትሔዎቻቸው " ክፍል ፪ በሚል ርእስ ዐቢይ ርእስ በመልአከ ሰላም ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራው በትዳር ውስጥ ለሚፈጠሩ ችግሮች መፍትሔዎች በሚል ሰፊት ትምህርት ታሰተምራለች። • #በእናስተዋውቃችሁ ዐምድ ሥር “# የጥንቷ «አናቶሊያ» የክርስትና መልክና የዘመናት ማዕበል ክፍል ሁለት " በሚል ርእስ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት እና የጉባኤያቱ ስፍራዎች በስፋት ታስቃኛለች ። • #በነገዋ ቤተ ክርስቲያን #ዐምድ ሥር “ በውጭ ሀገር ያለችው ቤተ ክርስቲያን ዕድገት፣ አሁናዊ ዕድሎችና ተግዳሮቶች ክፍል ሁለት " በውጭ ያለችው ቤተ ክርስቲያን መልካም አጋጣሚዎችና ዕድሎች ፤መፍትሔዎች በስፋት ይዛለች ። #በኪነ ጥበብ ዐምድ "#የታቦት ትከሻዎች ክፍል_፪ "በሚል ርእስ ታስነብባለች ። • #የጥያቄዎቻችሁ መልስ ዐምድ “የክርስትና ጉዞ በቱርክ ጥንታዊና አሁናዊ ሁኔታ # ክፍል _፪" በሚል ርእስ #በቱርክ የነበሩት ታሪካዊና ኦርቶዶክሳዊ ቅርሶች በምን ሁኔታ እንደሚገኙ ፣በአሁኑ ወቅት በቱርክ የክርስትና ሕይወት ምን እንደሚመስል፤በቱርክ የደረረው የክርትና መውደቅ ለእኛ ለኦርቶዶክሳውያን ምን ያስተምረናል? መምህራን ተጉዘው ነበር፡፡ በዚህም መሠረት ባደረጉት ጉብኝት የተመለከቱትንና የተረዱትን ያካፍሉን ዘንድ የመጻሕፍተ ሐዲሳት መምህር የሆኑትን መምህር ኀይለ ማርያም ዘውዱን ጋብዘናል፡፡ ያካፍሉን ዘንድ የመጻሕፍተ ሐዲሳት መምህር የሆኑትን መምህር ኀይለ ማርያም ዘውዱን ጋብዘናል፡፡ ሐመር መጽሔት ፴፫ኛ ዓመት ቍጥር ፯ በማሰራጨት ፡በማንበብና በማስነበብ የድርሻችን እንወጣ ! Magazine @eotcmk.org #ሐመር #መጽሔትበ ዝግጅት ክፍል

# ሥርዐተ ምንኵስናን መታደግ የሚቻለው ወቅታዊ መግለጫዎችን በማውጣት ወይም ጊዜያዊ ውይይቶች ን በማካሄድ ብቻ አይደለም ።" ሐምሌ ዕትም በ፳፻፲፰ ዓ.ም ዐቢይ ጉዳይ ዐምድ ✍️ ༺ ༻ #የኅትመት ዘመ
# ሥርዐተ ምንኵስናን መታደግ የሚቻለው ወቅታዊ መግለጫዎችን በማውጣት ወይም ጊዜያዊ ውይይቶች ን በማካሄድ ብቻ አይደለም ።" ሐምሌ ዕትም በ፳፻፲፰ ዓ.ም ዐቢይ ጉዳይ ዐምድ ✍️ ༺ ༻ #የኅትመት ዘመን ፦#ሐምሌ ፳፻፲፰ ዓ.ም #አዘጋጅ ፦በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን በሚዲያ አገልግሎት ተቋም በመጽሔት ዝግጅት ክፍል የሚዘጋጅ ትምህርታዊ መጽሔት • ገጽ ብዛት፦፳፰ ዋጋ ፦፶ ብር •ሐመር መጽሔት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት ሥርዓትና ትወፊት ጠብቃ በሚዲያ አገልግሎት ተቋም በመጽሔት ዝግጅት ክፍል የሚዘጋጅ ትምህርታዊ መጽሔት በየወሩ የምትወጣ መንፈሳዊ መጽሔት ናት፡፡ •ሐመር መጽሔት ፴፫ኛ ዓመት ቍጥር ፮ ሰኔ ፳፻፲፰ ዓ.ም. ዓ.ም መልእክት ዘማኅበረ ቅዱሳን " እነሆ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ ›› በሚል ታስነብባለች ። .#ዐውደ ስብከት ሥር” # ‹‹ጫማህን ከእግርህ አውጣ ›› ” በሚል ርእስ ታስነብባለች። #በትምህርተ ሃይማኖት ዐምድ ሥር “# ሐዋርያው ቅዱስ " በሚል ዐቢይ ርእስ በመልአከ ሰላም ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራው ስለ ቅዱሰ ጳውሎስ ትምህርትና ሰፊ ትምህርት ይሰጣል ። #ዐቢይ ጉዳይ ዐምድ ሥር ደግሞ “# የሥርዓተ ምንኵስና ቀኖናዊ መሠረቶች፣ ተግዳሮቶችና ተቋማዊ መፍትሔ ዎቹ " ክፍል ሁለት " በሚል ርእስ የምንኵስና ተቋማዊ አደረጃጀት ና ቀኖናዊ ትግበራ፤ መፍትሔ በተመለከተ በዝርዝር ያሳያል ።

ዜና ገዳማት

ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው። ---***--- ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ
ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው። ---***--- ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር   ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ። https://zoom.us/j/93407133345 ድጋፍ ለማድረግ ፡- 1.   Mahibere Kidusan in Europa e.V. IBAN: DE14 3704 0044 0307 8037 00 BIC: COBADEFFXXX Reason of payment – 007   2.   Mahibere Kidusan in UK Banking - NatWest Sort Code - 60 12 51 Acc. No - 364 25 591 Reason of Payment: 007   3.   በስዊድን ለምትገኙ፡- ACCOUNT NUMBER - 9960 3421234653 BIC - NDEASESS IBAN - SE15 9500 0099 6034 2123 4653 ACCOUNT HOLDER - MAHIBERE KIDUSAN I SVERIGE NORDEA BANK Reason of Payment: 007   4.   በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648 በአቢሲኒያ ባንክ 37235458 በአሐዱ ባንክ 0025393810901

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ …›› (ማቴ፲፣፳፰) ከዲ/ን ተስፋዬ ቻይ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ሥጋንም የሚገድሉትን  ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ …›› (ማቴ፲፣፳፰)   ከዲ/ን ተስፋዬ ቻይ  ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን የምሥራቹን ወንጌል ሰብከው የጨለመውን የሰው ልጅ ልቡና በወንጌል ብርሃንነት ያበሩ ዘንድ፣ ከጣዖተ አምልኮ አውጥተው የፈጠራቸውን የሚመግባቸውን እግዚአብሔር ያውቁና ያመልኩ ዘንድ፣ በጠላት ዲያቢሎስ አሳሳችነት የመረረ ሕይወታቸውን በወንጌል ጨውነት ያጣፍጡ ዘንድ ወደ ዓለም በላካቸው ጊዜ ጠላት ዲያሎስ በክፉዎች እያደረ መከራ እንደሚያመጣባቸው፣ ይህንንም እንደ እባብ ብልህ ፣እንደ ርግብ የዋህ ሆነው እንዲያልፉ ፣ሳይፈሩና ሳይሰቀቁ እንዲመሰክሩ አዘዛቸው ፤ መከራቸው ስደት ፣መጠማት፣ ግርፋትና ረኀብ ባቻ ሳይሆን ሥጋዊ ሞት( የነፍስ ከሥጋ መለየት) እንደሚገጥማቸውና ይህም አንዳች እንዳያስፈራቸው ነገራቸው፤ ምድራዊ ሩጫቸው በሰማዕትነት ቢገታም ሰማየያዊ መኖሪ ዘለዓለማዊ ሕይወት እንዳለ የታመነውን ተስፋ ሰጣቸው፡፡ ቅዱሳን አበው ሐዋርያት ጌታችን ሞትን ድል አድርጎ በተነሣ በአርባኛው ቀን፣ ካረገ በአሥረኛው ቀን ባናገረው ትንቢት ፣በገባላቸው ቃል መሠረት የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ላከላቸው፣በጾም በጸሎ መንፈሳዊ ተግባራቸውን ጀመሩ ፤እምነታቸው ጸንቶ፣ፍርሃት ርቆላቸው ጥቡዐን ( ደፋሮች) ሆነው የእውቀት ተከፍሎ ሳይኖርባቸው ፤ዓለምን በዕጣ ተከፋፍለው የምሥራቹን ወንጌል ማስተማር ጀመሩ፡፡ https://eotcmk.org/a/በስመ-አብ-ወወልድ-ወመንፈስ-ቅዱስ-አሐዱ-አ-3/

ማኅበረ ቅዱሳን ለደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገለጸ ሐምሌ ፫ /፳፻፲፰ ዓ.ም ማኅበረ ቅዱሳን በጎ አድራጊ አካላትን በማስተባበር በሰሜን ጎንደር ሀገ
ማኅበረ ቅዱሳን ለደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገለጸ   ሐምሌ ፫ /፳፻፲፰ ዓ.ም  ማኅበረ ቅዱሳን በጎ አድራጊ አካላትን በማስተባበር በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ደባርቅ ከተማ የደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገልጿል።   ማኅበረ ቅዱሳን በቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች አገልግሎት የፕሮጀክት ዝግጅትና ትግበራ ምክትል ኃላፊ የሆኑት ኢ/ር ማስተዋል አበበ (ወ/ሪት) እንደገለጹት የደብረ ሐዊ የቅዱስ ያሬድ ገዳም በኢኮኖሚ ዐቅሙን ለማሳደግና አገልግሎቱን ለማስቀጠል የሚረዳ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት በሁለት ዙር  እንደሚከናወን ተናግረዋል።  ይህም በመጀመሪያው ዙር B+G+4 ወለል ሕንጻ እየተገነባ እንደሚገኝ የተጠቀሰ ሲሆን ማኅበሩ በዚህ ዙር  የሚጠበቅበትን ድርሻ ለማጠናቀቅ በመወጣት ረገድ 75.79% መድረሱን ተገልጿል።   ግንባታው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚገኙ ድጋፍ አድራጊ አካላትን በማስተባበር የተከናወነ ነው ተብሏል።  በመጨረሻም ቅዱስ ያሬድ ለቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሀገር  ባለውለታ  እንደመሆኑና ገዳሙ ጥንታዊ በመሆኑ ለመናንያኑ የዕለት ጉርስ፣ የዓመት ልብስ እንዲሁም ለአገልግሎቱ የሚያስፈልጉ ነገሮችን በማድረግ ገዳሙ ያለበትን ደረጃ ለማቆየት ሁሉም ምእመን በሐሳብ፣ በጉልበትና በገንዘብ የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል ሲሉ ኢ/ር ማስተዋል አበበ  ጥሪ አቅርበዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ለደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገለጸ   ሐምሌ ፪/፳፻፲፰ ዓ.ም  ማኅበረ ቅዱሳን በጎ አድራጊ አካላትን በማስተባበር በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ደባርቅ ከተማ የደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገልጿል።   ማኅበረ ቅዱሳን በቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች አገልግሎት የፕሮጀክት ዝግጅትና ትግበራ ምክትል ኃላፊ የሆኑት ኢ/ር ማስተዋል አበበ (ወ/ሪት) እንደገለጹት የደብረ ሐዊ የቅዱስ ያሬድ ገዳም በኢኮኖሚ አቅሙን ለማሳደግና አገልግሎቱን ለማስቀጠል የሚረዳ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት በሁለት ዙር  እንደሚከናወን ተናግረዋል።  ይህም በመጀመሪያው ዙር B+G+4 ወለል ሕንጻ እየተገነባ እንደሚገኝ የተጠቀሰ ሲሆን ማኅበሩ በዚህ ዙር  የሚጠበቅበትን ድርሻ ለማጠናቀቅ በመወጣት ረገድ 75.79% መድረሱን ተገልጿል።   ግንባታው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚገኙ ድጋፍ አድራጊ አካላትን በማስተባበር የተከናወነ ነው ተብሏል።  በመጨረሻም ቅዱስ ያሬድ ለቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሀገር  ባለውለታ  እንደመሆኑና ገዳሙ ጥንታዊ በመሆኑ ለመናንያኑ የዕለት ጉርስ፣ የዓመት ልብስ እንዲሁም ለአገልግሎቱ የሚያስፈልጉ ነገሮችን በማድረግ ገዳሙ ያለበትን ደረጃ ለማቆየት ሁሉም ምእመን በሀሳብ፣ በጉልበትና በገንዘብ የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል ሲሉ ኢ/ር ማስተዋል አበበ  ጥሪ አቅርበዋል።

"የአኀት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ" የፓናል ውይይት ዘገባ ክፍል ፫ ሐምሌ ፫/፳፻፲፰ ዓ.ም የአኀት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት ግንቦት ፳፱/፳፻፲፰ ዓ.ም ተካሄዶ የነበረ ሲሆን በውይይቱም የሚክትሉተ ሦስት ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። ፩ኛ - የአኀት አብያተ ክርስቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ - በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል በመንበረ ፓትርያሪክ ጠ/ቤ/ክ ጥናት፣ ምርምርና መረጃ መምሪያ ኀላፊ እና የቅ/ሲኖዶስ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ኀላፊ እንዲሁም የሊቃውንት ጉባኤ አባል ፪ኛ - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት፣ ትግበራ፣ ክትትልና ግምገማ ከትናንት እስከ ዛሬ - በመ/ር ባሕረ ጥበባት ሙጨ ፫ኛ - የቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት ትግበራና የማኅበረ ቅዱሳን ድርሻ - በዶ/ር በሪሁን ተፈራ የማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ጽሑፎችና አጠቃላይ ውይይቱ በሦስት ክፍል የቀረበ ሲሆን የነበረው የማጠቃለያ ውይይት ሦስተኛው ክፍል እንደ ሚከተለው ቀርቧል፡፡ https://youtu.be/x3hRmh2hDPY?si=UpIKdQymapn-yg-I

ዜና ገዳማት

ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው። ---***--- ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ
ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው። ---***--- ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር   ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ። https://zoom.us/j/93407133345 ድጋፍ ለማድረግ ፡- 1.   Mahibere Kidusan in Europa e.V. IBAN: DE14 3704 0044 0307 8037 00 BIC: COBADEFFXXX Reason of payment – 007   2.   Mahibere Kidusan in UK Banking - NatWest Sort Code - 60 12 51 Acc. No - 364 25 591 Reason of Payment: 007   3.   በስዊድን ለምትገኙ፡- ACCOUNT NUMBER - 9960 3421234653 BIC - NDEASESS IBAN - SE15 9500 0099 6034 2123 4653 ACCOUNT HOLDER - MAHIBERE KIDUSAN I SVERIGE NORDEA BANK Reason of Payment: 007   4.   በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648 በአቢሲኒያ ባንክ 37235458 በአሐዱ ባንክ 0025393810901

ለበለጠ መረጃ፡- በአካል 5 ኪሎ ማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 1ኛ ወለል         ወይም ·  በስልክ.ቁ፡- +251 921803238 ·  በኢሜል፡- yagelgilotber@eotcmk.org ·  በቴሌግራም፡- @Zeyklekulu   ·  WhatsApp:- +251 91 352 8494       · ለመመዝገብና አገልግሎትን ለማግኘት :- 👇 👇 👇 https://forms.gle/CgYYC5gX6oxd3HGS7                          ዘመነ ክረምትን በአገልግሎት በር!

ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው። ---***--- ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ
ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው። ---***--- ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር   ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ። https://zoom.us/j/93407133345 ድጋፍ ለማድረግ ፡- 1.   Mahibere Kidusan in Europa e.V. IBAN: DE14 3704 0044 0307 8037 00 BIC: COBADEFFXXX Reason of payment – 007   2.   Mahibere Kidusan in UK Banking - NatWest Sort Code - 60 12 51 Acc. No - 364 25 591 Reason of Payment: 007   3.   በስዊድን ለምትገኙ፡- ACCOUNT NUMBER - 9960 3421234653 BIC - NDEASESS IBAN - SE15 9500 0099 6034 2123 4653 ACCOUNT HOLDER - MAHIBERE KIDUSAN I SVERIGE NORDEA BANK Reason of Payment: 007   4.   በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648 በአቢሲኒያ ባንክ 37235458 በአሐዱ ባንክ 0025393810901

ለበለጠ መረጃ፡- በአካል 5 ኪሎ ማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 1ኛ ወለል ወይም · በስልክ.ቁ፡- +251 921803238 · በኢሜል፡- yagelgilotber@eotcmk.org · በቴሌግራም፡- @Zeyklek
ለበለጠ መረጃ፡- በአካል 5 ኪሎ ማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 1ኛ ወለል         ወይም ·  በስልክ.ቁ፡- +251 921803238 ·  በኢሜል፡- yagelgilotber@eotcmk.org ·  በቴሌግራም፡- @Zeyklekulu   ·  WhatsApp:- +251 91 352 8494       · ለመመዘገቢና አገልግሎትን ለማግኝት :- 👇 👇 👇 https://forms.gle/CgYYC5gX6oxd3HGS7                          ዘመነ ክረምትን በአገልግሎት በር!

ይህ በእንዲህ እንዳለ የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በበኩሉ በየዓመቱ ለካህናት የሚሰጠውን የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ሥልጠና 15 ዲያቆናትን ሲያሠለጥን የቆየ ሲሆን ከሥልጠናው ጎን ለጎን ለማዕረገ ቅስና የሚያበቃቸውን ትምህርት በመስጠት ማዕረገ ቅስና እንዲቀበሉ አድርጓል።   ሥልጠናው በአርባ ምንጭ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ገዳም ጽርሐ ተዋሕዶ የካህናት ማሠልጠኛ ተቋም ሲሰጥ የቆየ ሲሆን ተቋሙ ለ58ኛ ጊዜ ማሠልጠኑ ተነግራል። ማኅበረ ቅዱሳን በያዘው መርሐ ግብር 11 ሠልጣኞችን በማስተማር ስምንቱ ማዕረገ ቅስና እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን በሀገረ ስብከቱ መርሐ ግብር ከሠለጠኑት 15 ዲያቆናት መካከል ስምንቱ ማዕረገ ቅስና እንዲያገኙ በማድረግ በአጠቃል ከ26 ሠልጣኞች መካከል 16ቱ ከብፁዕ አቡነ ኤልያስ ማዕረገ ቅስና ተቀብለዋል።   ሠልጣኞች ወደየ አካባቢያቸው ሲመለሱ ወንጌልን በማስፋፋት፣ የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን በመክፈትና የክህነት አገልግሎት በመስጠት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናቸውን ያገለግላሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ መረጃው አመላክቷል።

ማኅበረ ቅዱሳን ያስተማራቸውንና ያሠለጠናቸውን ዲያቆናት አስመረቀ። ሐምሌ ፩/፳፻፲፰ ዓ.ም የማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል ከአርባ ምንጭ ማእከል ጋር በጋራ በመሆን ከጋሞና አከባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከ
+3
ማኅበረ ቅዱሳን ያስተማራቸውንና  ያሠለጠናቸውን ዲያቆናት አስመረቀ። ሐምሌ ፩/፳፻፲፰ ዓ.ም የማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል ከአርባ ምንጭ ማእከል ጋር በጋራ በመሆን ከጋሞና አከባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት፣ ከጎፋና ባስኬቶ ዞኖች ሀገረ ስብከት እና ከወላይታ ሀገረ ስብከት ከተለያዩ ወረዳዎች የተወጣጡ 11 ዲያቆናትን ሲያስተምርና ሲያሰለጥን ቆይቶ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ/ም ማዕረገ ቅስና እንዲቀበሉ በማድረግ አስመርቋል። በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በአርባ ምንጭ ቅድስት ማርያም ገዳም አዳሪ አብነት ት/ቤት ሥልጠና ሲወስዱ የነበሩ ዲያቆናት ከሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ከብፁዕ አቡነ ኤልያስ ማዕረገ ቅስና ተቀብለው ተመርቀዋል ።   ሠልጣኝ ዲያቆናቱ የአገልጋይ እጥረት ካሉባቸው የሀገረ ስብከቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተወጣጡ ሲሆኑ ማኅበረ ቅዱሳን የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ እና በማስተባበር ዲያቆናቱ ለማዕረገ ቅስና እንዲበቁ አድርጓል።   ማኅበረ ቅዱሳን አዳዲስ ተጠማቂያንና የአገልጋይ ካህናት እጥረት ካሉባቸው አካባቢዎች የተወጣጡ 11 ዲያቆናትን በመመልመል አሠልጥኖ ወደ አገልግሎት ማሠማራት በያዘው ስልታዊ ዕቅዱ መሠረት ሙሉ ወጫቸውን በመሸፈን ሲያሰለጥን ቆይቷል። ዲያቆናቱ ለማዕረገ ቅስና የሚያበቃቸውን ኪዳን፣ ሊጦን ፣ መስተብቁዕ እና ዋና ዋና የቅዳሴ ዜማዎችን ያካተተ ትምህርት ሲማሩ የቆዩ ሲሆን ከመሠረታዊው የክህነት ትምህርት ጎን ለጎን የትምህርተ ሃይማኖት ሥልጠናዎች ማለትም ትምህርተ ሃይማኖት መግቢያ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ፣የቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን፣ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን፣ ነገረ ቅዱሳንና ነገረ ማርያም፣ ክርስቲያናዊ ሥነ-ምግባር፣ ሐዋርያዊ ተልእኮ፣ የስብከት ዘዴዎች እንዲሁም ተግባቦት ተሰጥተዋል።

በመጨረሻም  የየካ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት ዘካሪያስ ሐዲስ ከማእከሉ  እና ከሰንበት ት/ቤት አንድነት  ጋር ለመሥራት ያላቸው ፍላጎት እና ሁልጊዜም ለሚያደርጉት ቀና ትብብር ምስጋና ቀርቦ ሌሎች ክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ይህን አብሮ የማገልገል ተሞክሮ ልምድ ቢወስዱ ለቤተ ክርስቲያን ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑ ተገልጾ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል። መረጃው የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ሚዲያ ነው።

ለዲያቆናት ፣ ካህናት እና ሰባክያነ ወንጌል ሥልጠና መሰጠቱ ተገለጸ። ሐምሌ ፩/፳፻፲፰ ዓ.ም በማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል የምሥራቅ ማስተባበሪያ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካ ክፍለ ከተማ
+4
ለዲያቆናት ፣ ካህናት እና ሰባክያነ ወንጌል  ሥልጠና መሰጠቱ ተገለጸ። ሐምሌ ፩/፳፻፲፰ ዓ.ም በማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል የምሥራቅ ማስተባበሪያ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት እና ከሰ/ት /ቤት አንድነት ጋር በመተባበር ከ23 አድባራት ለተውጣጡ 291 ዲያቆናት፣ካህናት ፣ሰባክያነ ወንጌል በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሥልጠና መሰጠቱን ማስተባበሪያው ገልጿል። የሥልጠናው ዓላማ ካህናት የንስሓ ልጆቻቸውን አያያዝ በተመለከተ፣ በቤተ ክርስቲያን የውስጥ ሥርዓት ላይ ማለትም ማሕሌት፣ ሰዓታት ፣ ኪዳን፣ ቅዳሴ ፣የዐውደ ምሕረት መርሐ ግብርና ሌሎች አገልግሎቶችም የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት በጠበቀ መልኩ እንዲከወኑ ማስቻል ዋና ዓላማ ተደርጎ እንደተዘጋጀ  ተገልጿል።  ሰባክያነ ወንጌል የአገልግሎት ድርሻቸው በዐውደ ምሕረት ላይ በተመደቡበት ዕለት በማስተማር ብቻ ተገድቦ እንዳይቀር ከካህናቱ ጋር በመመካከር የንስሓ ልጆቻቸውን ማስተማር ፣ ምእመናንን ማስተማር ፣ማነጽ እና ያላመኑትን አስተምሮ መመለስ እንደሚያስፈልግ እና ኀላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ለማድረግ ዓላማ ያደረገ መሆኑ በሥልጠናው ላይ ተጠቁሟል።  ሥልጠናው በጠቅላይ ቤተ ክህነት የመሪ ዕቅድ መምሪያ ዐቢይ ኮሚቴ አባል በሆኑት ቀሲስ ብሩህ ተስፋ ሥዩም የተሰጠ ሲሆን ከመርሐ ግብሩ ታዳሚዎች አስተያየትና ጥያቄ ተነሥቶ ምላሽ ተሰጥቷል። ከዚህ ሥልጠና በኋላ በቀጣይ ከየአድባራቱ አስተዳዳሪዎችእና ጸሓፊዎች  ጋር ውይይት ለማድረግ የታቀደ መሆኑን እና በየአጥቢያው የሚገኙ ካህናት፣ መሪጌቶች ፣ዲያቆናት፣ ሰባክያነ ወንጌል  አገልግሎቱን  በሚጠበቀው ልክ ለማድረግ እንደሚሠራ የክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት ዘካሪያስ ሐዲስ ገልጸዋል።

ሁሉም አደነቁ ያን ጊዜም አንደበቱ ከድዳነት ተፈትቶለት ተናገረ፣ እግዚአብሔርንም ፈጽሞ አመሰገነው። ስለ ልጁና ስለ መድኃኒታችን መምጣት ልጁ ዮሐንስም የልዑል ነቢይ እንደሚባልና በእግዚአብሔርም ፊት እንደሚሄድ ትንቢት ተናገረ።http://www.eotcmk.org