ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል
تُعد قناة ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል (@mkpublicrelation) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 51 316 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 069 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 622 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 51 316 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 07 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 699، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 32، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 15.00%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 8.13% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 7 696 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 4 171 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 55.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 08 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
51 316
المشتركون
+3224 ساعات
+1567 أيام
+69930 أيام
أرشيف المشاركات
51 316
ይህ በእንዲህ እንዳለ የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በበኩሉ በየዓመቱ ለካህናት የሚሰጠውን የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ሥልጠና 15 ዲያቆናትን ሲያሠለጥን የቆየ ሲሆን ከሥልጠናው ጎን ለጎን ለማዕረገ ቅስና የሚያበቃቸውን ትምህርት በመስጠት ማዕረገ ቅስና እንዲቀበሉ አድርጓል።
ሥልጠናው በአርባ ምንጭ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ገዳም ጽርሐ ተዋሕዶ የካህናት ማሠልጠኛ ተቋም ሲሰጥ የቆየ ሲሆን ተቋሙ ለ58ኛ ጊዜ ማሠልጠኑ ተነግራል።
ማኅበረ ቅዱሳን በያዘው መርሐ ግብር 11 ሠልጣኞችን በማስተማር ስምንቱ ማዕረገ ቅስና እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን በሀገረ ስብከቱ መርሐ ግብር ከሠለጠኑት 15 ዲያቆናት መካከል ስምንቱ ማዕረገ ቅስና እንዲያገኙ በማድረግ በአጠቃል ከ26 ሠልጣኞች መካከል 16ቱ ከብፁዕ አቡነ ኤልያስ ማዕረገ ቅስና ተቀብለዋል።
ሠልጣኞች ወደየ አካባቢያቸው ሲመለሱ ወንጌልን በማስፋፋት፣ የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን በመክፈትና የክህነት አገልግሎት በመስጠት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናቸውን ያገለግላሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ መረጃው አመላክቷል።
51 316
+3
ማኅበረ ቅዱሳን ያስተማራቸውንና ያሠለጠናቸውን ዲያቆናት አስመረቀ።
ሐምሌ ፩/፳፻፲፰ ዓ.ም
የማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል ከአርባ ምንጭ ማእከል ጋር በጋራ በመሆን ከጋሞና አከባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት፣ ከጎፋና ባስኬቶ ዞኖች ሀገረ ስብከት እና ከወላይታ ሀገረ ስብከት ከተለያዩ ወረዳዎች የተወጣጡ 11 ዲያቆናትን ሲያስተምርና ሲያሰለጥን ቆይቶ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ/ም ማዕረገ ቅስና እንዲቀበሉ በማድረግ አስመርቋል።
በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በአርባ ምንጭ ቅድስት ማርያም ገዳም አዳሪ አብነት ት/ቤት ሥልጠና ሲወስዱ የነበሩ ዲያቆናት ከሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ከብፁዕ አቡነ ኤልያስ ማዕረገ ቅስና ተቀብለው ተመርቀዋል ።
ሠልጣኝ ዲያቆናቱ የአገልጋይ እጥረት ካሉባቸው የሀገረ ስብከቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተወጣጡ ሲሆኑ ማኅበረ ቅዱሳን የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ እና በማስተባበር ዲያቆናቱ ለማዕረገ ቅስና እንዲበቁ አድርጓል።
ማኅበረ ቅዱሳን አዳዲስ ተጠማቂያንና የአገልጋይ ካህናት እጥረት ካሉባቸው አካባቢዎች የተወጣጡ 11 ዲያቆናትን በመመልመል አሠልጥኖ ወደ አገልግሎት ማሠማራት በያዘው ስልታዊ ዕቅዱ መሠረት ሙሉ ወጫቸውን በመሸፈን ሲያሰለጥን ቆይቷል።
ዲያቆናቱ ለማዕረገ ቅስና የሚያበቃቸውን ኪዳን፣ ሊጦን ፣ መስተብቁዕ እና ዋና ዋና የቅዳሴ ዜማዎችን ያካተተ ትምህርት ሲማሩ የቆዩ ሲሆን ከመሠረታዊው የክህነት ትምህርት ጎን ለጎን የትምህርተ ሃይማኖት ሥልጠናዎች ማለትም ትምህርተ ሃይማኖት መግቢያ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ፣የቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን፣ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን፣ ነገረ ቅዱሳንና ነገረ ማርያም፣ ክርስቲያናዊ ሥነ-ምግባር፣ ሐዋርያዊ ተልእኮ፣ የስብከት ዘዴዎች እንዲሁም ተግባቦት ተሰጥተዋል።
51 316
በመጨረሻም የየካ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት ዘካሪያስ ሐዲስ ከማእከሉ እና ከሰንበት ት/ቤት አንድነት ጋር ለመሥራት ያላቸው ፍላጎት እና ሁልጊዜም ለሚያደርጉት ቀና ትብብር ምስጋና ቀርቦ ሌሎች ክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ይህን አብሮ የማገልገል ተሞክሮ ልምድ ቢወስዱ ለቤተ ክርስቲያን ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑ ተገልጾ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።
መረጃው የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ሚዲያ ነው።
51 316
+4
ለዲያቆናት ፣ ካህናት እና ሰባክያነ ወንጌል ሥልጠና መሰጠቱ ተገለጸ።
ሐምሌ ፩/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል የምሥራቅ ማስተባበሪያ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት እና ከሰ/ት /ቤት አንድነት ጋር በመተባበር ከ23 አድባራት ለተውጣጡ 291 ዲያቆናት፣ካህናት ፣ሰባክያነ ወንጌል በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሥልጠና መሰጠቱን ማስተባበሪያው ገልጿል።
የሥልጠናው ዓላማ ካህናት የንስሓ ልጆቻቸውን አያያዝ በተመለከተ፣ በቤተ ክርስቲያን የውስጥ ሥርዓት ላይ ማለትም ማሕሌት፣ ሰዓታት ፣ ኪዳን፣ ቅዳሴ ፣የዐውደ ምሕረት መርሐ ግብርና ሌሎች አገልግሎቶችም የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት በጠበቀ መልኩ እንዲከወኑ ማስቻል ዋና ዓላማ ተደርጎ እንደተዘጋጀ ተገልጿል።
ሰባክያነ ወንጌል የአገልግሎት ድርሻቸው በዐውደ ምሕረት ላይ በተመደቡበት ዕለት በማስተማር ብቻ ተገድቦ እንዳይቀር ከካህናቱ ጋር በመመካከር የንስሓ ልጆቻቸውን ማስተማር ፣ ምእመናንን ማስተማር ፣ማነጽ እና ያላመኑትን አስተምሮ መመለስ እንደሚያስፈልግ እና ኀላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ለማድረግ ዓላማ ያደረገ መሆኑ በሥልጠናው ላይ ተጠቁሟል።
ሥልጠናው በጠቅላይ ቤተ ክህነት የመሪ ዕቅድ መምሪያ ዐቢይ ኮሚቴ አባል በሆኑት ቀሲስ ብሩህ ተስፋ ሥዩም የተሰጠ ሲሆን ከመርሐ ግብሩ ታዳሚዎች አስተያየትና ጥያቄ ተነሥቶ ምላሽ ተሰጥቷል።
ከዚህ ሥልጠና በኋላ በቀጣይ ከየአድባራቱ አስተዳዳሪዎችእና ጸሓፊዎች ጋር ውይይት ለማድረግ የታቀደ መሆኑን እና በየአጥቢያው የሚገኙ ካህናት፣ መሪጌቶች ፣ዲያቆናት፣ ሰባክያነ ወንጌል አገልግሎቱን በሚጠበቀው ልክ ለማድረግ እንደሚሠራ የክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት ዘካሪያስ ሐዲስ ገልጸዋል።
51 316
ሁሉም አደነቁ ያን ጊዜም አንደበቱ ከድዳነት ተፈትቶለት ተናገረ፣ እግዚአብሔርንም ፈጽሞ አመሰገነው። ስለ ልጁና ስለ መድኃኒታችን መምጣት ልጁ ዮሐንስም የልዑል ነቢይ እንደሚባልና በእግዚአብሔርም ፊት እንደሚሄድ ትንቢት ተናገረ።http://www.eotcmk.org
51 316
ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ
ሰኔ ፴ በዚች ዕለት ነቢይ ሰማዕትና ሐዋርያ የሆነ መጥምቁ ዮሐንስ ተወለደ።
ዮሐንስ ማለት እግዚአብሔር ጸጋ ነው ማለት ነው፡፡ትርጓሜ ወንጌልም መጥምቀ መለኮት ዮሐንስን ፍሥሐ ወሐሴት (ተድላናደስታ) ይለዋል ፤ወላጆቹ በእርሱ መወለድ ተደስተዋልና /ሉቃ.፩፥፲፬/፡፡በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ ሄሮድስ የመድኀኒታችን የክርስቶስን መወለድ ከሰብአ ሰገል ሲሰማ መንግሥቴን ይወስድብኛል ብሎ ስለሠጋ ጌታችንን ያገኘሁ መስሎት የቤተልሔም ሕፃናትን መግደል ጀመረ/ማቴ.፪፥፩-፲፮/፡፡
በዚህ ጊዜ ቅድስት ኤልሳቤጥ ልጇን ከሞት ለማዳን ስትል ሕፃኑ ዮሐንስን ይዛ ወደ በረሃ ተሰደደች።
በበረሃም ድንጋይ ቤት ሆኖላቸው፣እግዚአብሔርም ከብርድ፣ከፀሐይና ከአራዊቱ አፍ እየጠበቃቸው መኖር ጀመሩ፡፡ ወደ በረሃ ሲገቡ ቅዱስ ዮሐንስ የሁለት ዓመት ከመንፈቅ ሕፃን ነበር፡፡ ሕፃኑም አደገ ፤በመንፈስም ጠነከረ፤ ለእስራኤል እስከታየበት ቀን ድረስ በምድረ በዳ ኖረ /ሉቃ.፩፥፹/ተብሎ እንደተጻፈ፡፡
ይህም በእናቱ ማኅፀን ውስጥ ሳለ ለእግዚአብሔር ልጅ የሰገደው ነው፣ በመድኅነ ዓለም ክርስቶስ ራስ ላይ እጁን ጭኖ በውኃ ያጠምቀው ዘንድ የተገባው ነው። በቅዱስ ወንጌል እንደ ተነገረ ወንድ ልጅን ትወልድ ዘንድ የኤልሳቤጥ የፅንሷ ወራት በተፈጸመ ጊዜ ወንድ ልጅን ወለደች፤ ዘመዶቿና ጐረቤቶቿ እግዚአብሔር ቸርነቱን እንዳበዛላት በሰሙ ጊዜ ስለእርስዋ ደስ አላቸው።
በስምንተኛውም ቀን ሊገዝሩት መጡ፣ በአባቱም ስም ዘካርያስ ብለው ጠሩት እናቱ ግን አይሆንም ዮሐንስ ይባል አለች። ”ከዘመዶችሽ ስሙ እንዲህ የሚባል የለም” አሏት። አባቱንም ጠቅሰው ”ማን ሊባል ትወዳለህ?”አሉት፤ እርሱም ብራና ለምኖ ስሙ ዮሐንስ ይባል ብሎ ጻፈ ።
51 316
✝️የጾም ቁርሳችን፣
ለወገኖቻችን✝️ +++
በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች እያጋጠሙ ባሉ ማኅበራዊ ቀውሶች( ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች፣ መፈናቀልና ጦርነት ) ብዙ ወገኖቻችን ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል።
እርስዎም ለእነዚህ ወገኖች የጾም ቁርስዎን በመለገስ ቸርነትን ያድርጉ!
ድጋፍ ለማድረግ :-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በወገን ፈንድ ፡- https://Www.wegenfund.com/mknu መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
51 316
+3
የአዲስ አበባ ማእከል 109 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች በደረጃ አንድ ተተኪ መምህራን መመረቃቸውን ገለጸ።
ሰኔ ፳፱/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዋና ክፍል የግቢ ጉባኤያት ተቋማዊ ልማት ክፍል በደረጃ አንድ ሲያሠለጥናቸው የቆዩ የግቢ ጉባኤ ተማሪዎችን ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓም ማስመረቁን በዋና ክፍሉ የግቢ ጉባኤያት ተቋማዊ ልማት ምክትል ኀላፊ መምህር መስፍን ግርማ ገልጸዋል።
የሥልጠናው ዓላማ የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች ከቀለም ትምህርታቸው ጎን ለጎን የማስተማር ዐቅም ያላቸውን ተማሪዎች ሥልጠና በመስጠት በግቢ ጉባኤ የሚያገለግሉ ተተኪ መምህራንን ማፍራትና ማሰማራት ላይ ያለመ ነው።
በዕለቱም ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶክተር ሙሉጌታ ሥዩም የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ አመራር አባል ምክርና የአገልግሎት ልምዳቸውን ያካፈሉ ሲሆን በሥልጠናው ጥሩ አርአያ ላሳዩ ሁለት መምህራን የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል ።
በመጨረሻም የአዲስ አበባ ማእከል ሰብሳቢ ዲያቆን ኃይለ ማርያም መድኅን ለተመራቂዎች "ዛሬ የተመረቃችሁት የመጨረሻ ሳይሆን የመጀመሪያ መሆኑን አውቃችሁ ተጠያቂ መምህር ለመሆን እያነበባችሁና ከሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እየጠየቃችሁ እራሳችሁን አሳድጉ፣ በተሰጣችሁ መክሊት በማገልገል እንድታተርፉ፣ አገልግሎታችሁ በፍቅርና በትሕትና ይሁን" በማለት መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በሥልጠናው ጥሩ ውጤት ላመጡ 3 ተማሪዎች የመጽሐፍት ሽልማትና ለተመራቂዎች የአደራ መስቀል በቀሲስ ገዛኸኝ በቀለ ተሰጥቷቸው መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።
መረጃው ፦ በማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ሚዲያ ነው
51 316
ከዚህ ባሻገር ብፁዕነታቸው የብፁዕ አቡነ አብርሃምን መልእክት በሚያጠናክር መልኩ "ሊቃውንቱ ለቅድስት ቤተክርስቲያን አንድነት ፣ ከቀድሞው በበለጠ በጋራ ሊቆሙ ፣ አንድ ድምፅ ሁነውም ሊመክሩ ፣ ምክረ ሐሳባቸውንም ለቅዱስ ሲኖዶስ በትጋት ሊያቀርቡ" እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የተመራቂ ደቀመዛሙርት መምህር የሆኑት ሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ መልአክ ተማሪዎቻቸው ለዚህ ደረጃ በመብቃታቸው መደስታቸውን ገልጸው በቀጣይም በምስክር ጉባኤ ቤቱ በነበራቸው ቆይታ የቀሰሙትን ጥንታዊ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ዕውቀት ተግባር ላይ በማዋል ለቤተ ክርስቲያንና ለሀገር የሚጠቅም አገልግሎት እንዲሰጡ አሳስበዋል።
የምስክር ጉባኤ ቤቱ ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን እያከናወነ ስለመሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን በምርቃት በዓል ላይ ለመምህራን ማረፊያ እንዲሁም ወደ ምስክር ጉባኤ ቤቱ ለሚመጡ እንግዶች መቀበያ የሚሆን ሕንጻ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
ይህ አዲስ ሕንጻ የጉባኤ ቤቱን የትምህርት ሥርዓት ለማጠናከር፣ ለተማሪዎችም የተሻለ የአስተዳደርና አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያግዝ ተጠቁሟል።
©ፈለገ ገነት ሚዲያ
51 316
+9
የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የ፬ቱ ጉባኤያት የምስክር ጉባኤ ቤት 19 ደቀ መዛሙርትን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት አስመረቀ።
ሰኔ ፳፱/፳፻፲፰ ዓ.ም
በምርቃት መርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕር ዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የስካንዲቪያንስ እና የግሪክ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የምስክር ጉባኤ ቤቱ መምህር ሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ መልአክ ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የሥራ ኀላፊዎች ፣ የምስክር ጉባኤ ቤቶች መምህራን ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፣ ተመራቂዎችና የተመራቂ ደቀመዛሙርት ወዳጅ ዘመዶች እንዲሁም ጥሪ የተረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም በመርሐ ግብሩ ላይ ለተመራቂ ደቀ መዛሙርት እና ለቤተ ክርስቲያን የእንኳን ደስ ያላችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈው "የዛሬ ተመራቂ ደቀ መዛሙርት የነገ መምህራን የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሉዓላዊነትነት ተከብሮ እንዲዘልቅ ፣ ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ የቅዱስ ሲኖዶስ የተዘረጋው የቤተ ክርስቲያን ሰንሰለት ይበልጥ ጠንካራ እንዲሆን ለሐዋርያዊ አገልግሎት በምትጓዙበት ሁሉ በርትታችሁ ልትሠሩ ይገባል" ብለዋል።
ብፁዕነታቸው አክለውም "በማያስፈልገው መልኩ የጥንቱን እውቀታችሁን አታዘምኑት" የአባቶቻችን ትርጓሜም ወደ ቀጣይ ትውልድ ተጠብቆ እንዲተላለፍ ተግታችሁ ሥሩ ፣ ከእውቀት ባሻገር ለመንፈሳዊነትም ልዩ ትኩረት እንድትሰጡ ደግሞም የምታስተምሩትን በተግባር መኖር ከተመራቂ ደቀመዛሙርት እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።
ብፁዕ አቡነ ኤልያስ በበኩላቸው ተመራቂ ደቀመዛሙርት ለፍሬ እንዲበቁ ምኞታቸውን በመግለፅ ሊቃውንት በዚህ መልኩ መመረቃቸው ጥንት ያልነበረ አሁን ግን የተለመደ ታላቅ ተግባር ነውና "ትልቅ ዕድል" ነው ብለዋል።
51 316
+4
የዲላ ማእከል ለ7ኛ ዙር ያሠለጠናቸውን 63 የበገና ሠልጣኞች አስመረቀ።
ሰኔ ፳፱/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የዲላ ማእከል ለ7ኛ ዙር ያሠለጠናቸውን 63 የበገና ሠልጣኞች ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም አባቶች ካህናት፣የተመራቂ ቤተሰቦች እና የዲላ ማእከል አባላት በተገኙበት አስመርቋል ።
በዕለቱ መዝሙርና ትምህርተ ወንጌል የቀረበ ሲሆን መ/ር ታሪኩ ወንድማገኝ በማኅበረ ቅዱሳነን የዲላ ማእከል ሰብሳቢ ላለፉት ስድስት ወራት የበገና ሥልጠና ሲወስዱ ለነበሩ ተመራቂዎች እና የተመራቂ ቤተሰቦች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈው ተመራቂዎች እግዚአብሔርን በበገና ከማመስገን ባሻገር በሕይወታቸው መልካም ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ሊኖራቸው ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
በመርሐ ግብሩ የተገኙት የቅ/ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን አገልጋይና የማእከሉ አባል ቀሲስ ተቋም
የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈው ተማሪዎች አልባሌ ቦታ ከመዋል ይልቅ እግዚአብሔርን ለማመስገን በተመረጠ ቦታ መገኘታቸው መልካም ነው ብለዋል።
በተጨማሪ ይህ ዝማሪ መንፈሳዊ በረከት ያለው በመሆኑ ለሌሎች አርአያ በመሆን በመንፈሳዊ ሥነ ምግባር ልትኖሩ ይገባል በማለት ገልጸዋል።
በተመሳሳይ በደሴ ማእከል ለ4ኛ ዙር ያሠለጠናቸውን 38 በገና ደርዳሪዎችን በበደሌ ደ/ሣህል መድኃኔዓለም ካቴድራል አስመርቋል።
51 316
የጥቃት ሰለባ የሆኑ ኦርቶዶክሳውያን እስካሁን የት ወደቃችሁ ምን ደረሰባችሁ ያለን አካል የለም ሲሉ የገለጹ ሲሆን ማኅበረ ቅዱሳን ላደረገላቸው ድጋፍ እና በቦታው ተገኝቶ ስለጎበኛቸው አመስግነው መንግሥት በሕይወት የመኖር ተፈጥሯዊ መብታችንን ያስጠብቅልን ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎትም በ2018 ዓ.ም ያለፉት 10 የአገልግሎት ወራት ብቻ በመላ ሀገራችን 16 የሚደርሱ አስቸኳይ ማኅበራዊ ድጋፍ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ያደረገ ሲሆን በያዝነው ጾመ ሐዋርያትም “የጾም ቁርሳችን ለወገኖቻችን” በሚል መሪ ቃል ሰፊ የማኅበራዊ ድጋፍ ማሰባሰብ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል።
በመጨረሻም አርሲን ጨምሮ፣ በልዩ ልዩ ማኅበራዊ ቀውሶች የተጎዱ ወገኖችን ሕይወት ለመታደግ፣ የምእመናን ተሳትፎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀርቧል።
ድጋፍ ለማድረግ፡-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
በአሐዱ ባንክ 0025393810901
በአቢሲንያ ባንክ 37235458
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648
በወጋገን ባንክ 0837331610101
በአዋሽ ባንክ -01329817420400
እንዲሁም
በወገን ፈንድ፡- https://Www.wegenfund.com/mknu መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
51 316
+3
ማኅበረ ቅዱሳን በምዕራብ ሐረርጌ ዞን አሰቦት ከተማ ፣ በመቻራ ከተማ እና በዶባ ወረዳ ለሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን ተፈናቃዮች አስቸኳይ የምግብ ግብዓቶች ድጋፍ አደረገ
ሰኔ ፳፱/፳፻፲፰ .ም
በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት በተለያዩ ወረዳዎች በሚገኙ ምእመናን ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች ሲደርስ ቆይቷል።
በእነዚህ ጥቃቶች ሰለባ ከሆኑ እና ብዙ ጉዳት ከደረሳበቸው ቦታዎች መካከልም በሚኤሶ ወረዳ የሚገኘው አሰቦት ደብረ ወገግ ቅድስት ሥላሴ ወአባ ሳሙኤል አንድነት ገዳም አካባቢ፣ በዶባ ወረዳ ፣ ከአርሲ ሀገረ ስብከት ሸነን ኮሉ ወረዳ እንዲሁም ከዳሮ ለቡ ወረዳ ተፈናቅለው በመቻራ ከተማ ይገኛሉ።
በአሰቦት ደብረ ወገግ ቅድስት ሥላሴ ወአባ ሳሙኤል አንድነት ገዳም መነኮሳት ላይ ተደጋጋሚ ግድያ ሲፈጸም የቆየው ጥቃት አድማሱን አስፍቶ በአካባቢው ወደሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያ እና ወደ ሌሎች የዞኑ ወረዳዎች በመሻገሩ ምክንያት ኦርቶዶከሳውያን ለሞት፣ ለስደት፣ ለመፈናቀል እና ለርሃብ ተዳርገዋል።
በዚህም ምክንያት የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት ከሚችገን ደብረ ገነት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ቤተ ክርስቲያን እና ከሌሎች በጎ አድራጊ ምእመናን ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ከመኖርያ ቤታቸው ተፈናቅለው ወደ አጎራባች ከተሞች ተሰደው ለሚገኙ ለእነዚህ ተፈናቃዮች በድምሩ ከ1.3 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሆነበት አስቸኳይ የምግብ ግብዓት ድጋፍ አድርጓል።
በድጋፍ ርክክቡ ወቅትም የማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል ልኡካን፣ የማኅበረ ቅዱሳን አሰበ ተፈሪ ማእከል ተወካዮች፣ የሚኢሶ ወረዳ ማእከል እና የአሰቦት ገዳም አባቶች ተገኝተው ድጋፎችን ለተፈናቃዮች አስረክበዋል።
51 316
የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት 12 የኬጂ የመማሪያ ማስተማሪያ መጻሕፍት እያዘጋጀ እንደሚገኝ ገለጸ
ሰኔ ፳፯ /፳፻፲፰ ዓ.ም
የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት 12 የኬጂ የመማሪያ ማስተማሪያ መጻሕፍት እያዘጋጀ እንደሚገኝ በማኅበረ ቅዱሳን የትምህርት ፕሮግራም ሱፐርቪዥን አስተባባሪ አቶ ደመላሽ አሰፋ ገልጸዋል።
አቶ ደመላሽ አሰፋ አክለውም መጻሕፍቱ መንግሥት ያዘጋጀውን የመማሪያ ማስተማሪያ መሠረት በማድረግ ከኬጂ 1 እስከ ኬጂ 3 ላሉ ተማሪዎች ሀገር በቀል ምሳሌዎችን በማካተትና ኦርቶዶክሳዊ ዕሴትን በጠበቀ መልኩ የተዘጋጀ ነው ብለዋል።
በዚህም የመጻሕፍት ዝግጅቱ ተጠናቅቆ መስከረም 2019 ዓ.ም በየትምህርት ቤቱ እንደሚሰራጭ የትምህርት ፕሮግራም ሱፐርቪዥን አስተባባሪ ተናግረዋል።
አቶ ደመላሽ አሰፋ አያይዘውም በሀገር ውስጥ በ34 ከተሞች የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች በአራት ክላስተር በሐዋሳ፣ በአዳማ፣ በደብረ ብርሃንና በባሕዳር የተዋቀረ መሆኑን የገለጹት ሲሆን ከ37 ሺህ በላይ ተማሪዎችን እያስተማረ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
51 316
"የአሃት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ" የፓናል ውይይት ዘገባ
ክፍል ፪
ሰኔ ፳፮/፳፻፲፰ ዓ.ም
የአሃት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት ግንቦት ፳፱/፳፻፲፰ ዓ.ም ተካሄዶ የነበረ ሲሆን በውይይቱም የሚከትሉት ሦስት ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
፩ኛ - የአሃት አብያተ ክርስቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ - በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል በመንበረ ፓትርያሪክ ጥናት፣ ምርምርና መረጃ መምሪያ ኃላፊ እና የቅ/ሲኖዶስ ኮምዪኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ እንዲሁም የሊቃውንት ጉባኤ አባል
፪ኛ - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት፣ ትግበራ፣ ክትትልና ግምገማ ከትናንት እስከ ዛሬ - በመ/ር ባሕረ ጥበባት ሙጨ
፫ኛ - የቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት ትግበራና የማኅበረ ቅዱሳን ድርሻ - በዶ/ር በሪሁን ተፈራ የማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ
ጽሑፎችና አጠቃላይ ውይይቱ በሦስት ክፍል የቀረበ ሲሆን በመ/ር ባሕረ ጥበባት ሙጨና በዶ/ር በሪሁን ተፈራ የቀርቡ ጽሑፎች የሁለተኛው ክፍል እንደ ሚከተለው ቀርቧል፡፡
https://youtu.be/NwdXp7I-Prs?si=hUdCdKwvacF4dnCa
51 316
"የአኃት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ" የፓናል ውይይት ዘገባ ፤ ፤ ክፍል ፩
ሰኔ ፳፮/፳፻፲፰ ዓ.ም
የአኃት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት ግንቦት ፳፱/፳፻፲፰ ዓ.ም ተካሄዶ የነበረ ሲሆን በውይይቱም የሚክትሉተ ሦስት ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
፩ኛ - የአኃት አብያተ ክርስቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ - በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል በመንበረ ፓትርያሪክ ጥናት፣ ምርምርና መረጃ መምሪያ ኃላፊ እና የቅ/ሲኖዶስ ኮምዪኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ እንዲሁም የሊቃውንት ጉባኤ አባል
፪ኛ - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት፣ ትግበራ፣ ክትትልና ግምገማ ከትናንት እስከ ዛሬ - በመ/ር ባሕረ ጥበባት ሙጨ
፫ኛ - የቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት ትግበራና የማኅበረ ቅዱሳን ድርሻ - በዶ/ር በሪሁን ተፈራ የማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ
ጽሑፎችና አጠቃላይ ውይይት በሦስት ክፍል የቀረበ ሲሆን በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል ስለ አኃት አብያተ ክርስቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ የቀረበው የመጀመሪያው ክፍል እንደ ሚከተለው ቀርቧል፡፡https://youtu.be/1QC70jI2QDU?si=tlpK_B2CaR-K5mQJ
51 316
+1
“መሠረተ ሃይማኖት” የተባለ የልጆች መጽሐፍ የፊታችን እሑድ እንደሚመረቅ የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ገለጸ
ሰኔ ፳፭ /፳፻፲፰ ዓ.ም
የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎትን በስፋት ተደራሽ ለማድረግ የሚውል “መሠረተ ሃይማኖት” በሚል ርእስ የተዘጋጀ የልጆች መጽሐፍ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በማኅበሩ ሕንጻ 3ኛ ወለል ንቡረ ዕድ ድሜጥሮስ አዳራሽ እንደሚመረቅ በማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዳይሬክተር ዲ/ን ሙሉጌታ ነጋ ገልጸዋል።
መጽሐፉ በዲ/ን ማርኤል ሽመልስ የተዘጋጀ ሲሆን የክርስትና መሠረተ እምነት የሆኑትን አምስቱን አዕማደ ምሥጢራት ለልጆች በሚገባ መልኩ የተጻፈ መሆኑን ዲ/ን ሙሉጌታ ነጋ ተናግረዋል።
በመርሐ ግብሩ ትምህርተ ወንጌል፣ የስብከተ ወንጌል ዘጋቢ ፊልምና የመጽሐፍ ምርቃቱ ይከናወናል ተብሏል።
51 316
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎትም በ2018 ዓ.ም ያለፉት 9 የአገልግሎት ወራት ብቻ በመላ ሀገራችን 15 የሚደርሱ አስቸኳይ ማኅበራዊ ድጋፍ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ አድርጓል። በያዝነው ጾመ ሐዋርያትም “የጾም ቁርሳችን ለወገኖቻችን” በሚል መሪ ቃል ሰፊ የማኅበራዊ ድጋፍ ማሰባሰብ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል። አርሲን ጨምሮ፣ በልዩ ልዩ ማኅበራዊ ቀውሶች የተጎዱ ወገኖችን ሕይወት ለመታደግ፣ የምእመናን ተሳትፎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀርቧል።
ድጋፍ ለማድረግ፡-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
በአሐዱ ባንክ 0025393810901
በአቢሲንያ ባንክ 37235458
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648
በወጋገን ባንክ 0837331610101
በአዋሽ ባንክ -01329817420400 እንዲሁም
በወገን ፈንድ፡- https://Www.wegenfund.com/mknu መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
