ru
Feedback
እድገትጮራ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት🎓

እድገትጮራ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት🎓

Открыть в Telegram

“Education is the key to unlock the golden door of freedom.” – George Washington Carver

Больше
7 308
Подписчики
+4024 часа
+947 дней
+21530 день
Архив постов
1_መፅሐፍ እየመለሳችሁ የክረምት ትምህርት ይቀጥላል ። 2_ ከፕሮግራሙ ወጪ መፅሃፍ አይመለስም። 3_ለሁለም ክፍሎች ከ9_12 በየሳምንቱ ፕሮገራም ይወጣል። 4_ የልማት ክፍያ ከምዝገባ በኋላ መታወቂያ ሲሰጥ ወይም እድሳት ሲደረግ ይሆናል ። 5_ የአዲስ ተመዝጋቢዎች ነባር ከተመዘገቡ በኋላ ፕሮግራም የሚወጣ ይሆናል

ለትምህርት ቤታችን የ2019 የ12ኛ ክፍል ነባር ተማሪዎች የትምህርት ዘመኑን ምዝገባ እንድታደርጉ ቀደም ብለን ማስታወቃችን ይታወቃል። በመሆኑም ከዚህ ቀጥሎ በተቀመጠው ፕሮግራም መሰረት ምዝገባ እንድታደርጉ እየገለፅን መተባለው እለት የማይገኝ ሰው የማይስተናገድ መሆኑን አስቀድመን እናሳውቃለን። በ21/11/2018 11-1 እና 11-2 የነበራችሁ ተማሪዎች በ22/11/2018 11-3፣11-4 እና 11-5 በ23/11/2018 11-6 እና 11-7 በ24/11/2018 ደግም 11-8 እና 11-9 የነበራችሁ ተማረዎች በፕሮግራሙ መሰረት የ11ኛ ክፍል መፅሐፍ እየመለሳችሁ የ12ኛ ክፍል በመውሰድ ምዝገባ እንድትፈፅሙ በጥብቅ እናሳስባለን።

የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መፅሐፍ መመለሻ ኘሮግራም ሰኞ (20/11/2018) ጠዋት (ከ2:30 -6:30) ማሀህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች፣ ከሰዓት(7:30 - 10:30) የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች መፅሐፍ የምትመልሱበት ሰዓት መሆኑን አውቃችሁ በእለቱ ሰዓታችሁን ጠብቃችሁ መፅሐፍ በማስረከብ ከንብረት ክፍል የነፃ ወረቀት(clearance)

የክረምት ትምህርት ላይ የማትሳተፉ የ11 እና 12 ክፍል ተማሪዎች በራሳችሁ ላይ ችግር እንዳትፈጥሩ። እየተማራችሁ ያላችሁ በቂ ደብተር ያዙ። ሰአት አክብራችሁ ተገኙ ።የተማራችሁትን ዉጤት መጨረሻ ካርድ ይረጣል። በመምህራን በኩል ጥሩ ስነምግባር ያላችሁ ጥያቄ የምትጠይቁ መሆኑ ተነስቷል ። በጣም ጥሩ ነዉ። በርቱ ጥቅሙ ለራሳችሁ ነዉ።

አብርሆት ለተፈተናችሁ የ12ኛ ክፍል የ5ኛ ዙር አንዳንድ የቀንና የማታ የሶሻል ተማሪዎች ከፈተና ስትመለሱ በፈጠራችሁት ጩኸት እነማን ሞንታርቦ እንደያዛችሁ ስልክ ይዛችሁ እንደነበረ መረጃዉ ስለደረሰንና የተያዛችሁም ስለነበራችሁ የአካባቢው ማህበረሰብ ስትጮሁ ፎቶ ያነሱአችሁ በመሆኑ ይህን የፈፀማችሁ ምንም አይነት ትራንስክሪፕት የማይሰራ ስርተፍኬት የማይሰጥ መሆኑን እንድታወቁ።

ማስታወቂያ ለተማሪዎች እና ወላጆች የትምህርት ቤታችን የ2018 ዓ.ም የ10ኛ እና የ11ኛ ክፍል ታማሪዎች በትምህርት ዘመኑ ትምህርታችሁን ስትከታተሉ ቆይታችሁ ወደ ቀጣዩ ክፍል ያለፋችሁ ተማሪዎች ሁላችሁም በትምህርት ቤታችን የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት መጀመሩ ይታወቃል፡፡ ከትምህርቱ ጎን ለጎን የ2019 ዓ.ም የነባር ተማሪዎች ምዝገባም እየተደረገ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ብዙ ተማሪዎች ምዝገባ ያላደረጋችሁ ሰለሆነ በ13/11/2018 ዓ.ም በምእራፍ አካዳሚ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመገኘት እንድትመዘገቡ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡ በተጨማሪም የክረምት ማጠናከሪያ ላይ መገኘት በቀጣይ አመት በትምህርት ቤቱ ለመቀጠል ቅድመ ሁኔታ መሆኑን አውቃችሁ ስትመጡ ዩኒፎርም በመልበስ፣ ማስታወሻ ደብተር እና የማጠናከሪያ ትምህርት ክፍያ 1000 (አንድ ሺህ ብር) በመያዝ ከጠዋቱ 2፡00 ጀምሮ በመገኘት ተማዝግባችሁ ትምህርቱን እንድትቀጥሉ በጥብቅ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ ማንኛውም 11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ነባር ተማሪ ምዝገባ በዚሁ እንደሚካሄድ እና በቀጣይ ሌላ ምዝገባ እንደማይደረግ ማወቅ ይገባል፡፡ ማሳሰቢያ፡ የ11ኛ ክፍል ተማሪዎች ቀድሞ መመዝገብ ለሞያና ተግባር ትምህርት () የምትፈልጉት ፊልድ ለማግኘትም ጠቀሜታ እንዳለው ግንዛቤ ይወሰድ፡፡                                         ት/ቤቱ

+1
እስካሁን ድረስ ትምህርት ያልጀመሩ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ቶፕ 30 ተማሪዎች፡፡

ውድ ተማሪዎች እንደምን አላችሁ በተላለፈው መልእክት መሰረት ምዝገባ አካሂዳችሁ በአግባቡ የማጠናከሪያ ትምህርታችሁን እየተከታተላችሁ ያላችሁትን በርቱ እና በትኩረት ተከታተሉ እያልን እስከ አሁን ድረስ ምዝገባ አድርጋችሁ የማጠናከሪያ ትምህርት ያልጀመራችሁ እና የሚጠበቅባችሁን ክፍያ ያልከፈላችሁ የትምህርት ቤታችን ተማሪዎች ለሚገጣማችሁ የትኛውም ችግር ሀላፊነት የምትወስዱት እራሳችሁ መሆናችሁን ከወዲሁ እናሳውቃለን፡፡ በመሆኑም በፍጥነት መጥታችሁ እንድትመዘገቡ እና ትምህርት ላይ እንድትገኙ፤ የተማሪ ወላጆችም በቀጣይ ከሚመጣባችሁ ውጣ ውረድ እና አላስፈላጊ ውጣ ውረድ እራሳችሁን እንድትጠብቁ እና ልጆችን ወደ ትምህርት ቤት በመላክ ሃላፊነታችሁን በአግባቡ እንድትወጡ እናሳውቃለን፡፡ ወደ ትምህርት ቤት ስትመጡ ዩኒፎርም በአግባቡ መልበስ፣ ደብተር /ማስታወሻ መያዝ እና የክፍያ ብር መያዝ አትርሱ፡፡ ክፍያውን በባንክ ቁጥር ኢትዮጵያ ንግድ ባንም 1000731978232 በማስገባት ደረሰኝ ይዛችሁ መምጣት ትችላላችሁ፡፡

ወድ የ12ኛ ክፍል የ5ኛ ዙር የሶሻል የቀንና የማታ ተፈታኞች ነገ ሐሙስ በቀን 9/11/2018 ፈተና የሚጀመርበት ቀን ስለሆነ አብርሆት የምትሄዱ 12:00 እና እድገት ጮራ ተፈታኞች 1:00 እንድትገኙ። አብርሆት የምትሄዱ አርፍዶ የሚመጣ መከናወ የማይጠብቅ መሆኑ ይታወቅ።

የክረምት ተማሪዎች የምስክር ወረቀት
የክረምት ተማሪዎች የምስክር ወረቀት

ውድ ወላጆች እንደምን ሰነበታችሁ በ21/10/2018 ባደረግነው ውይይት መሰረት የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ከሀምሌ 6/2018 ጀምሮ በይፋ እንደሚጀመር መልዕክት የተላለፈ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ልጆቻችሁን በእለቱ ወደ ትምህርት ቤት በመላክ ሀላፊነታችሁን የተወጣችሁ ወላጆችን እያመሰገንን እስካሁን ድረስ ልጆቻችሁን ያላካችሁ እና በማጠናከሪያ ትምህርት ላይ እንዲገኙ ያላደረጋችሁ ወላጆች የሚጠበቅባችሁን ሀላፊነት እንድትወጡ እና በቀጣይ ከሚከሰት አላስፈላጊ ውጣ ውረድ እራሳችሁን እንድትጠብቁ ከወዲሁ እናሳስባለን እናሳስባለን፡፡

ትዕዛዝ በማክበር ትናንት ጀምሮ ተመዝግባችሁ እየተማራችሁ ያላችሁ እናመሠግናለን ። የቀጣይ ክፍል ድልድል በዚሁ የሚሠራላቸሁ ሲሆን እሰካሁን (እስከዛሬው እለት) ድረስ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ላይ ተገኝታችሁ ያልተማራችሁ እና ያልተመዘገባችሁ ተማሪዎች ለመጨረሻ ጊዜ ከ7 – 8/11/2018 ድረስ ብቻ በምእራፍ አካዳሚ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዩኑፎርመ ለብሳችሁ እና ማስታወሻ ደብተር ይዛችሁ በመገኘት ምዝገባ እንድታደርጉ እየገለፅን ከዚህ ቀን ውጭ በምዝገባ የማትስተናገዱ መሆኑንን ደግመን ደጋግመን እንገልፃለን፡፡

ትዕዛዝ በማክበር ትናንት ጀምሮ ተመዝግባችሁ እየተማራችሁ ያላችሁ እናመሠግናለን ። እሰካሁን ያልተመዘገባችሁ። እዚህ መቀጠል ስለማይቻል በወቅቱ መሸኛችሁን እንድትወሰዱ እያልን ትምህርት ቤቱ መልዕክቱን ያስተላልፋል

አስቸካይ ጥብቅ ማሳሰቢያ የ2018 ዓ.ም ከ10 ወደ 11 እና ከ11 ወደ 12 ያለፋችሁ ቶፕ 30 ተማሪዎች ከነገ 7/11/2018 ዓ.ም ጀመሮ በተላለፈላችሁ መልእክት እና ጥሪ መሰረት በምዕራፍ አካዳሚ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ተገኝታችሁ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርቱን እማትከታተሉ ከሆነ በትምህርት ቤቱ በኩል ምንም አይነት  ምዝገባ እንደማይደረግላችሁ እና መሸኛ ወይም ሌላም መረጃ ብትጠይቁ እንደማትስተናገዱ ከወዲሁ እያሳወቅን ቤተሰብም ይህን ጉዳይ አውቆ ሀላፊነቱን እንዲወጣ እና ካላስፈላጊ መንገላታት እራሳችሁንም ሆነ ልጆቻችሁን እንድትጠብቁ  እያሳሰብን ይህ ሳይሆን ቢቀር ግን ትምህርት ቤቱ ሀላፊነት የማይወስድ መሆኑን አስቀድመን እናሳውቃለን፡፡ በመሆኑም ከዚህ በላይ ስማችሁ የተዘረዘረው የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በ7/11/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ጀምሮ በምዕራፍ አካዳሚ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ደብተር በመያዝ እና ዩኒፍርም በመልበስ ተገኝታችሁ ትምህርት እንድትደምሩ በጥቅ እናሳስባለን፡፡

+1
አስቸካይ ጥብቅ ማሳሰቢያ የ2018 ዓ.ም ከ10 ወደ 11 እና ከ11 ወደ 12 ያለፋችሁ ቶፕ 30 ተማሪዎች ከነገ 7/11/2018 ዓ.ም ጀመሮ በተላለፈላችሁ መልእክት እና ጥሩ መሰረት በምዕራፍ አካዳሚ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ተገኝታችሁ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርቱን እማትከታተሉ ከሆነ በትምህርት ቤቱ በኩል ምንም አይነት ምዝገባ እንደማይደረግላችሁ እና መሸኛ ወይም ሌላም መረጃ ብትጠይቁ እንደማትስተናገዱ ከወዲሁ እያሳወቅን ቤተሰብም ይህን ጉዳይ አውቆ ሀላፊነቱን እንዲወጣ እና ካላስፈላጊ መንገላታት እራችሁንም ሆነ ልጆቻችሁን እንድትጠብቁ እያሳሰብን ይህ ሳይሆን ቢቀር ግን ትምህርት ቤቱ ሀላፊነት የማይወስድ መሆኑን አስቀድመን እናሳውቃለን፡፡ በመሆኑም ከዚህ በላይ ስማችሁ የተዘረዘረው የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በ7/11/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ጀምሮ በምዕራፍ አካዳሚ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ተገኝታችሁ ሪፖርት እንድታደርጉ በጥቅ እናሳስባለን፡፡

የክፍያ አካዉንት ከላይ በተጠቀሰዉ ወይም በአካል ይዞ በመቅረብ ይቻላል

1000731978232 Zenebe and Fekadu and sisay

ምዕራፍ ትምህርት የምትማሩት አስከ 13/11/2018 ድረስ ሲሆን ከ14/11/2018 በኋላ እድገት ጮራ የምንቀጥል ይሆናል ።

ከዚህ ዝርዝር ለይ ስማችሁ የተጠቀሰ ተማሪዎች ት/ቤት በመገኘት የክረምት ትምህርት የማትጀምሩ ለሚገጥማችሁ ችግር ሀላፊነት የምትወስዱት ተማሪው እና ቤተሰብ መሆኑን እንገልፃለን።

Summer Student data.doc0.30 KB