እድገትጮራ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት🎓
前往频道在 Telegram
“Education is the key to unlock the golden door of freedom.” – George Washington Carver
显示更多7 754
订阅者
+1524 小时
+597 天
+45830 天
帖子存档
እንዴት ዋላችሁ????
የባዮሎጂ ውጤት ተማሪዎች በተገቢው እንዲያዩ ንገሯቸው።የተለያየ ቦታና አካባቢ ተማሪዎች ችግር አለ እየተባለ ነው።
ማስታወቂያ፡
የሁሉም ክፍል ደረጃ ደጋሚ ፣ በሲስተም ችግር ምዝገባው የተጓተተ፣ ፊልድ ያልመረጠ የ11ኛ ክፍል ተማሪ እንዲሁም በየትኛው ክፍል ደረጃ እስካሁን ድረስ ያልተመዘገበ ተማሪ በሙሉ ምዝገባ ነገ በ22/12/2018 ዓ.ም ብቻ መሆኑን እናሳዉቃለን።
ስትመጡ የዘንድሮውን ሰርቲፊኬት እና የት/ቤቱን መታወቂያ መያዝ ይኖርባችኋል።16:01
ለት/ቤታችን ነባር የ10-1 እስከ 10-3 ክፍል ለሆናችሁ ተማሪዎች በሙሉ
ነገ ማለትም በ22/12/18 ጧት 2፡30 ጀምሮ uniform ስለሚስጥ ከ10-1 እስከ 10-3 ክፍል የነበራችሁ ተማሪዎች የተመዘገባችሁ መፅሀፍ የወስዳችሁበትን በመያዝ እንድትገኙ፡ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
ውድ ተመራቂ ተማሪዎች ምርቃት በ24/12/2018 ዓ.ም ነው። ሰዓት ጠዋቱ 4:00 ቦታ ሲኤምሲ(CMC) የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ አሶሴሽን አዳራሽ ። ገዋን የሚወሰደው አርብ በ22/12/2018) ሲሆን፡ ጠዋት ማህበራዊ ሳይንስ ከ3:00 እስከ 4:30 ተፈጥሮ ሳይንስ ደግም ከ5:00 እስከ 6:30 ብቻ መሆኑን አውቃችሁ በሰዓቱ ትምህርት ቤት ግቢ በመገኘት እንድትወስዱ እናሳስባለን። ማሳሰቢያ፡ ገዋን የሚመለሰው በ26/12/2018 ሲሆን ጠዋት ማህበራዊ ሳይንስ ከ3:00 እስከ 6:00 ተፈጥሮ ሳይንስ ከ7:00 እሰከ 9:00 የሚመልሱ ይሆናል። ገዋን ለመውሰድ ስትመጡ ለመያዣ የሚሆን እና ገዋኑ ሲመለስ ተመላሽ የሚደረግ ብር 500(አምስት መቶ) በካሽ እና የት/ቤት መታወቂያ መያዝ የግድ ነው።
፨ በ2019 እድገት ጮራ ትምህርት ቤት እየተመዘገባችሁ ያላችሁ ተማሪዎች ከሩቅ ነዉ የምንመጣው በማለት አርፍደው የሚመጡ ተማሪዎች ከአሁኑ በአቅራቢያቸው በሚገኝ ትምህርት ቤት መመዝገብ አለባቸው ።
፨ ነገ በትምህርት ቤቱ የኦላይን ተፈታኞ ስላሉ ምዝገባ አይኖርም ።
፨ ነባር ተማሪ እስካሁን ያልተመዘገቡ ትምህርት ቤቱ ሃላፊነት አንወስድም ።
፨ ከዚህ ቀደም የማርፈድ የመቅረት የስነ ምግባር ችግር ውስጥ የነበራችሁ ያለምንም ማስጠንቀቂያ ከትምህርት ቤት ይሰናበታሉ ።
፨ በ2018 በተለይ ወንድ ተማሪዎች ሹራብ ራሱ ላይ የሚጠመጥም እና የመጀመሪያው ቀን ዩኒፎርም ለብሶ መምጣት አለበት ።
ስለዚህ ይህን ታሳቢ የማያደርግ ተማሪ ከወዲሁ ቦታዉን ሙምረጥ አለበት ።
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+1
የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ውጤታቸውን ዛሬ ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምረው ማየት ይችላሉ - የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት
የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸውን ማስፈንጠሪያዎች የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጓል፡፡
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን በመጠቀም ውጤታቸውን ማየት የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ አስታውቋል፡፡
በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ
https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ማቅረብና ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡
ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡- በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et፣ ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram፣ አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡
https://result.eaes.et/sms መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መረጃ ያመላክታል፡፡
የየካ ጣፎ ቦሪ የተመደቡ እና የጨፌ የካ ቦሌ የተመደበ እንዲሁም የመሪ ህዳሴ በሻሌ ወይም ጋራ ጉሪ የተመደቡ ወደ እድገት ጮራ መምጣት አያስፈልግም ።
ማስታወቂያ
በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን 9ኛ ክፍል ለመማር በክ/ከተማ ወደ እድገት ጮራ ት/ቤት የተመደባችሁ ተማሪዎች ምዝገባው የሚካሄደው ነሀሴ 14 ፣15 እና 18/2018 ሲሆን ለምዝገባ ስትመጡ:
1. አንድ ክላሴር
2. 3*4 አንድ የተማሪ እና አንድ የወላጅ ጉርድ ፎቶ
3. የ8ኛ ክፍል ካርድ ዋናው
4.ፋይዳ መታወቂያ የተማሪ
5. የወላጅ/ አሳዳጊ መታወቂያ ኮፒ
6. የተማሪ የልደት ካርድ ኮፒ
7. ከነበሩበት ት/ቤት መረጃ በሲስተም መላኩን አረጋግጦ መምጣት እንደሚያስፈልግ አስቀድመን እናሳስባለን።
በ13/12/2018 ከ10 - 12 እስካሁን ድረስ ያልተመዘገባችሁ ነባር ተማሪዎች የመጨረሻ ማጣሪያ ስለሚደረግ እንድትመዘገቡ ጥሪ እናቀርባለን።
ለ11 እና 12 ክፍል ተማሪዎች በቀጣይ ሐሙስ እና አርብ ማለትም ከ 14_15/12/2018 የሚድ ፈተና ስለሚሰጥ ቅድመ ዝግጅት ይደረግ:: ክረምቱን በተገቢው ሲከታተል የቆየ ተማሪ በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የተዘጋጀውን ካርድ የሚሰጥ ይሆናል ።
በ12/12/2018 n2018 ከ9-1 እስከ 9-15 ስትማሩ የነበራችሁ እና ወደ 10ኛ ክፍል አልፋችሁ በተለያ ምክንያት ምዝገባ ያለፋችሁ ተማሪዎች የማጣሪያ ምዝገባ የሚደረግ ይሆናል። ሰሰለሆነም ያልተመዘገባችሁ ተማሪዎች በት/ቤት ተገኝታችሁ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን።
ሰላም ተማሪዎች
የክረምት ትምህርት ያለማቋረጥ ስትከታተሉ የነበራችሁ የ11 እና 12 ክፍል ተማሪዎች የምስክር ወረቀት የሚሰጣችሁ ይሆናል ።
ሰላም ተማሪዎች እና የተማሪ ቤተሰቦች ከ 9 ወደ 10 ያለፋችሁ የትምህርት ቤታችን የ2019 ነባር የ10ኛ ክፍል ተመዝጋቢ ተማሪዎች የምዝገባ ፕሮግራማችሁ ከዚህ አንደሚከተለው መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ማክሰኞ(5/12/2018) በ2018 ከ9-1 እስከ 9-3 የነበራችሁ
እሮብ(6/12/2018) በ2018 ዓ.ም 9-4 እስከ 9-6 የነበራችሁ
ሀሙስ(7/12/2018) በ2018 ዓ.ም ከ9-7 እስከ 9-9 የነበራችሁ
አርብ(8/12/2018) በ2018 ከ9-10 እስከ 9-12 የነበራችሁ
ሰኞ(11/12/2018) በ2018 ዓ.ም ከ9-13 እስከ 915 የነበራችሁ ተማሪዎች በወጣው ፕሮግራም መሰረት በትምህርት ቤት በመገኘት እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ፡ ለምዝገባ የሚመጣ ተማሪ የ9ኛ ክፍል መፅሐፍ እየመለስ 10ኛ ክፍል መፅሐፍ መውሰድ ይጠበቅበታል፡፡
- መፅሐፍ ለመመለስ መፅሐፍን በምትወስዱ ጊዜ አብሮ የተሰጣችሁን ወረቀት (የመፅሐፍ ዝርዝር) መያዝ ያስፈልጋል፡፡
- የምዝገባ ፕሮግራሙን በጠበቀ መልኩ መመዝገብ ያስፈልጋል፡፡
- የትምህርት ቤቱን መታወቂያ መያዝ መረሳት የለበትም፡፡
ሰኞ በ4/12/2018 10-13 የነበሩ ተማሪዎች ምዝገባ እና ለ2019 11ኛ ክፍል ነባር ተማሪዎች በተለያየ ምክንያት ምዝገባው ላመለጣቸው የማጣሪያ ምዝገባ ቀን መሆኑን እናሳስባለን፡፡
የትምህርት ቤታችን የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ጀምራችሁ ወጣ ገባ እያላችሁ ያለችሁ ተማሪዎች ስም ጠሪ ተመድቦ የየእለት ቀሪ ክትትል እየተደረገ መሆኑን በመገንዘብ በስተመጨረሻ ዋጋ እንዳያስከፍላችሁ በአግባቡ እና በተከታታይ ያለ ቀሪ ትምህርቱን እንድትከታተሉ ከወዲሁ እናሳስባለን፡፡ የተማሪ ወላጆችም ተማሪ መመዝገቡ ብቻ ወይም ሁለት እና ሶስት ቀን ተምሮ መቅረቱ ተገቢ አለመሆኑን አውቃችሁ ተገቢውን ክትትል በማድረግ ሀላፊነታችሁን ትወጡ ዘንድ ትምሀርት ቤቱ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ በተጨማሪም ማንኛውም ተማሪ በሚሰጠው ተከታታይ ምዘና እና በተሳተፈበት የትምህርት ቀን ብዛት ተለክቶ አግባብነት ሲኖረው ብቻ የምስክር ወረቀቱ የሚሰጠው መሆኑን ከወዲሁ እናስገነዝባለን፡፡ በስተመጨረሻም መማር ሲኖርባችሁ እስካሁን ትምህርት ያልጀመራችሁ ተማሪዎች ከወዲሁ መረጃችሁን አንድትወስዱ በማሳወቅ በቀጣይ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች አለመሆናችሁን እንድታውቁ ለማሳሰብ አንወዳለን፡፡
ወድ ተማሪዎች ነገ ጥብቅ ቁጥጥር ይደረጋል። በየክፍላችሁ አቴንድንስ ፈርሙ ። ወጣ ገባ የምትሉ የምታረፍዱ ደብተር የማትይዙ ያለክፍላችሁ የምትገቡ ነገ ፍተሻ ይደረጋል ። መጨረሻ ሰርተፍኬት የሚሰጠው በተከታታይ የመጡ ብቻ ተለይቶ ነዉ። ስለዚህ ጠንክራችሁ ተማሩ። የሚያጣራ ቡድንም በየክፍሉ ይፈትሻሉ።
ተማሪዎች መፅሐፍ ለመመለስ ስትመጡ መፅሐፉን ስትወስዱ አብሮ የተሰጣችሁን ወረቀት(የመፅሐፍ ዝርዝር ያለበትን ፎርም) ይዛችሁ መምጣት እንዳትረሱ፡፡
