SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )
Открыть в Telegram
9 033
Подписчики
+124 часа
+417 дней
+15030 день
Архив постов
ሐሙስ
ሰኔ 25
Jul 2
የጳውሎስ መልእክቶች ለቆሮንቶስ ሰዎች
1ኛ ቆሮንቶስ 1:11–13፣ 1ኛ ቆሮንቶስ 4:14፣ 1ኛ ቆሮንቶስ 5:11፣ 1ኛ ቆሮንቶስ 7:1፤ እና 1ኛ ቆሮንቶስ 14:37፣ 40 እንዲሁም 2ኛ ቆሮንቶስ 1:12፣ 2ኛ ቆሮንቶስ 2:9፣ 2ኛ ቆሮንቶስ 11:3 እና 2ኛ ቆሮንቶስ 13:10ን አንብቡ። እነዚህ ጥቅሶች ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች ደብዳቤ የጻፈው ለምን እንደሆነ እንድንገነዘብ የሚረዱን እንዴት ነው?
Save Notes
ጳውሎስ 1ኛ ቆሮንቶስን ሲጽፍ በኤፌሶን ነበር (1ኛ ቆሮ. 16:5–9)። እነርሱ በነበሩበት በቆሮንቶስ ነገሮች በጣም ጥሩ እንዳልነበሩ የቀሎዔ ቤተሰብ ወደ እርሱ መረጃውን ይዘው ሄዱ (1ኛ ቆሮ. 1:11)። በ1ኛ ቆሮንቶስ 1–6 ላይ፣ ጳውሎስ ቀሎዔ ይዛ ስለመጣችው ጉዳዮች ተናግሯል። ከችግሮቹ መካከል የቡድንተኝነት፣ የፆታ ብልግና፣ መካሰስ እና ዝሙት አዳሪነት ይገኙበታል። ጳውሎስ የተወሰኑ ጥያቄዎችን የያዘ ደብዳቤም ደርሶታል (1ኛ ቆሮ. 7:1)። የእርሱ ምላሽ ከምዕራፍ 7 ጀምሮ ያለውን ቦታ ይይዛል። ጥያቄዎቹ ከጋብቻ፣ ከፍቺ፣ ሳያገቡ ከመኖር፣ ለጣዖት ከተሠዋ ምግብ፣ ከአምልኮ ሥነ ምግባር፣ ከመንፈሳዊ ስጦታዎች አጠቃቀምና አንዲሁም ስለ ትንሣኤ ከነበረ የተሳሳተ ግንዛቤ ጋር የተያያዙ ነበሩ። የቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን በጣም ችግር ያለባት እና ያልበሰለች ነበረች። አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናችሁም ምናልባት ብዙ ችግሮች ሊኖሩባት ትችላላች። ሆኖም የቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን ግን ከዚህም የከፋች ነበረች።
ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች የጻፈው የመጀመሪያ መልእክት ለዘመናችንም ጠቃሚ ነው። ደግሞስ ዛሬም በተወሰነ ደረጃ በብዙ አብያተ ክርስትያኖቻችን ውስጥ አንዳንድ ተመሳሳይ ጉዳዮች አያጋጥሙንምን? ይህ ደብዳቤ ብዙ የሚነግረን አለው። እርሱ “ከጻፋቸው ደብዳቤዎች ሁሉ በመረጃ የዳበሩ፣ አስተማሪና በጣም ኃይለኛ ከሆኑት አንዱ ነው” (ኤለን ጂ. ኋይት፣ The Acts of the Apostles, ገጽ. 301)።
ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች ሦስት ወይም አራት መልእክቶችን ጽፎ ሊሆን ይችላል (ከ2ቆሮ. 10:9 ጋር አወዳድሩ)። 1ኛ ቆሮንቶስን ከመጻፉ በፊት አንድ የመነሻ ደብዳቤ ጽፎ ነበር፣ ነገር ግን ጠፍቷል። ከ2ኛ ቆሮንቶስ በፊት ምሁራን “ከባድ ደብዳቤ” በማለት የገለጹትን ደብዳቤ ጽፏል (2ኛ ቆሮ. 2:3፣ 4፣ 9፤ 2ኛ ቆሮ. 7:8)፤ ይህም ደግሞ ጠፍቷል። አንዳንዶች እርሱ የሚናገረው ስለ 1ኛ ቆሮንቶስ ነው ወይም ይህ መልእክት በከፊል በ2ኛ ቆሮንቶስ ውስጥ ይገኛል ብለው ያስባሉ።
ከ2ኛ ቆሮንቶስ እንደምንረዳው፣ የቆሮንቶስ [ቤተ ክርስቲያን] አባላት በዙሪያው ባለው ባህል ተጽዕኖ ውስጥ እንደነበሩ እንገነዘባለን። ዛሬም ቤተ ክርስቲያናችንን ሊፈታተኑ ለሚችሉ እንደ ፉክክር፣ ሥልጣንና ሀብት የመሳሰሉ ነገሮች ከፍ ያለ ዋጋ ይሰጡ ነበር። በተቃራኒው፣ ጳውሎስ በክርስቶስ ላይ ያተኮረ ባህል፣ ዓለም በወንጌል መነጽር የሚታይበትን መንገድ ለመፍጠር ይፈልግ ነበር። እኛም አሁን ያለንበትን ዓለም በወንጌል መነጽር መመልከታችን ምንኛ ወሳኝ ነው። 2ኛ ቆሮንቶስ 2:4ን እንደገና አንብቡ። ጳውሎስ ለእነዚህ ሰዎች ምን ያህል ያስብላቸው እንደነበር ይህ ምን ይነግረናል? ነገር ግን ከዚህ በተቃራኒ የኛ ልብ ለሌሎች ምን ያህል ቀዝቃዛ ሊሆን ይችላል?
@SabbathSchool @TekalignSorato
ረቡዕ
ሰኔ 24
Jul 1
"ብዙዎች በዚህች ከተማ ውስጥ"
የሐዋርያት ሥራ 18:4–8ን አንብቡ። የጳውሎስ ስብከት ውጤቶች ምን ነበሩ?
Save Notes
ጳውሎስ በቆሮንቶስ በነበሩት አይሁዶች መካከል ያከናወነው ሥራ የፈለገውን ያህል ፍሬያማ አልነበረም። አንዳንድ ጠላትነትን እና ጥላቻን መጋፈጥ ነበረበት። መጽሐፍ ቅዱስ “በተቃወሙትና በተሳደቡ ጊዜ” ይላል (የሐዋርያት ሥራ 18:6)። ‹ስድብ› (blasphēmeō) የሚለው የግሪክ ግስ የሚፈጸመው በሰው ላይ ሲሆን “በሚያዋርዱ ቃላት ማጥቃት” ወይም “ስም ማጥፋት” ማለት ነው። በሌላ አነጋገር የጳውሎስን ስም ለማጉደፍና የሚስዮናዊነት ሥራው እንዳይሳካ ለማድረግ አስበው ነበር ማለት ነው።
እንደ እድል ሆኖ፣ በቆሮንቶስ ምኩራብ ውስጥ የጳውሎስ ሥራ ከንቱ አልነበረም። ምንም ሆነ ምን፣ የተልእኮው ኃላፊ እግዚአብሔር ነበር። “[ቃሌ] የላክሁትንም ይፈጽማል እንጂ ወደ እኔ በከንቱ አይመለስም” (ኢሳ. 55:11) ሲል ቃል ገባ። አንዳንድ አይሁዶች የምኩራቡ አለቃ ቀርስጶስ እና ቤተሰቡ የሱስን መሲህ አድርገው እንደሚቀበሉና እንደሚጠመቁ አልጠበቁም ነበር (የሐዋርያት ሥራ 18:8)። እነርሱ ብቻ ሳይሆኑ “ከቆሮንቶስ ሰዎች ብዙዎች ሰምተው አምነው ተጠመቁ” (የሐዋርያት ሥራ 18:8)፤ ይህ የሆነው ደግሞ ምናልባት በቀርስጶስ ተጽዕኖ ምክንያት ሊሆን ይችላል። የሐዋርያ ሥራ 18:9፣ 10ን አንብቡ። ጳውሎስ በቆሮንቶስ ያጋጠሙትን ፈታኝ ሁኔታዎች በመጋፈጡ ስለተሰማው ስሜት ምን ማለት እንችላለን? እግዚአብሔር አገልጋዩን ያበረታው እንዴት ነበር?
Save Notes
ጳውሎስ ከምኵራብ ከወጣ በኋላ ወዲያውኑ የሚያበረታታ ተሞክሮ አግኝቶ ነበር። ክርስቶስ ራሱ ኢሳይያስ 41:10ን በመድገም፦ “እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ” ሲል በሌሊት ራእይ ተገለጠለት። በእርግጥም ጳውሎስ በቆሮንቶስ “በድካምና በፍርሃት በብዙ መንቀጥቀጥ” እንደነበረ ተናግሯል (1ኛ ቆሮ. 2:3)። ከባድ ተቃውሞ ስለገጠመው ከቤርያ ወደ አቴንስ መሄድ ነበረበት። በተመሳሳይ በከባድ ተቃውሞ ምክንያት ቆሮንቶስን ለቅቆ መውጣት እንዳለበት ያሰበ ይመስላል። ያን ጊዜ የሆነው ግን እንደዚያ አልነበረም። የሱስም እንዲህ አለው፦ “በዚህች ከተማ ብዙ ሰዎች አሉኝ” (የሐዋርያት ሥራ 18:10)። ጳውሎስ የመዳንን ዜና ወደ እነርሱ ይዞ የሚሄድ የየሱስ መሳሪያ ነበር። ኢሳይያስ 41:10ን አንብቡ። በዚህ አጭር ክፍል ውስጥ ምን አስደናቂ ተስፋዎች ተሰጡን? በዕለት ተዕለት ሕይወታችን ላይ ምን ተጽዕኖ ያሳድራሉ?
@SabbathSchool @TekalignSorato
Repost from SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )
ቅድስናን የጠበቀ እጮኝነት፦ በመንፈሳዊ ስነ-ምግባር መተዋወቅና መፍቀር
የህይወት አጋር ምርጫ፦ የእግዚአብሔርን ፍቃድ እንዴት እናውቃለን?
የብቸኝነት (Singlehood) ዘመንን በጥበብ መኖር፦ እራስን ለትልቅ አላማ ማዘጋጀት
ከስሜታዊነት መውጣት እና እውነተኛ ፍቅርን ማወቅ
ለትዳር ራስን በንፅህና ማዘጋጀት
@SabbathSchool @TekalignSorato
ማክሰኞ
ሰኔ 23
Jun 30
የቆሮንቶስ ከተማ
የሐዋርያት ሥራ 18:1–3፣ 1 ቆሮንቶስ 5:9–11 እና 1 ቆሮንቶስ 8:4ን አንብቡ። ስለ ቆሮንቶስ ኢኮኖሚ፣ ሥነ ምግባር እና ሃይማኖታዊ ሕይወት ምን ማለት እንችላለን?
Save Notes
ቆሮንቶስ የጥንቱ ዓለም አስፈላጊ ማዕከል እንዲሁም በበለጸገ ንግድዋ የታወቀች ነበረች። ከተማዋ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ146 ዓመተ ዓለም በሮም ተደምስሳ የነበር ሲሆን፣ የሮማውያን ቅኝ ግዛት በመሆን እንደገና በጁሊየስ ቄሳር በ44 ዓመተ ዓለም ተገንብታለች። በአዲስ ኪዳን ውስጥ የምናገኛት ይህች ከተማ የሮም ቆሮንቶስ ናት ማለት ነው። በጳውሎስ ዘመን ቆሮንቶስ ከአቴንስ ተቀናቃኞች መካከል አንዷ የነበረች ሲሆን፤ እንዲያውም በተለያዩ ገጽታዎቿ ከሌሎች ትበልጥ ነበር። ቆሮንቶስ የንግድ ልውውጥን እና እንቅስቃሴን ቀላል የሚያደርጉ ሁለት ጠቃሚ ወደቦች ነበሯት።
በእርግጥም፣ ጳውሎስ ቆሮንቶስን የመረጠው በመልክአ ምድራዊ አቀማመጥዋ ጠቃሚ እና አመቺ በመሆኗ ነው። “ስለዚህ ወንጌልን ለማዳረስ የሚያስችል አጋጣሚ ተፈጠረ። [ወንጌል] በቆሮንቶስ ከተቋቋመ በኋላ ለሁሉም የዓለም ክፍሎች በቀላሉ ለማዳረስ ይቻል ነበር” (ኤለን ጂ. ኋይት፣ Sketches From the Life of Paul, ገጽ. 99)።
እያበበ የነበረው የቆሮንቶስ ንግድ፣ ጳውሎስ በዚያ ከተማ ወንጌልን እየሰበከ ድንኳን በመስፋትና በመሸጥ ራሱን መደገፍ ቀላል እንዲሆንለት አድርጎታል። በአንድ ትልቅና የበለጸገ ከተማ ውስጥ የሚስዮናዊነት ሥራ ከችግር የጸዳ እንዳልሆነ ግልጽ ነው። ቆሮንቶስ በሃይማኖታዊ ብዝሃነቷ ተለይታ ትታወቅ ነበር (1ኛ ቆሮ. 8:5)፤ ይህም እንደ አፖሎ፣ አቴና፣ እና አፍሮዳይት ያሉ አማልክቶችን፣ እንዲሁም እንደ ሳራፒስ እና አይሲስ ያሉ ሌሎች የግብፅ አማልክትን ለማምለክ በተገነቡት በርካታ መቅደሶች በግልጽ ይታያል።
ከዚህ ሃይማኖታዊ ግራ መጋባት በተጨማሪ ቆሮንቶስ በጾታዊ ልቅነትዋ ትታወቅ ነበር። ግሪካዊው የጂኦግራፊ እና የታሪክ ምሁር ስትራቦ በቆሮንቶስ በሚገኘው ቤተ መቅደሷ ውስጥ ለአፍሮዳይት አምልኮ ያደሩ 1,000 ዝሙት አዳሪዎች እንደነበሩ ተናግሯል። ምንም እንኳን ብዙ ሊቃውንት ይህንን በጥርጣሬ ቢመለከቱትም እና አባባሉንም አቴናውያን በቆሮንቶስ ላይ ከሚያሰራጩት ፕሮፓጋንዳ ጋር ቢያገናኙም፣ በጥንቱ ዓለም ዝሙት አዳሪነት የተለመደ ነበር። ፆታዊ እርኩሰት እንደ ሌሎች ቦታዎች ሁሉ በቆሮንቶስም ችግር ነበር። ጣዖት አምልኮ እና ርኩሰት የዕለት ተዕለት ሕይወት አካል ነበሩ፣ እና ይህ አሳዛኝ እውነታ አብዛኛውን የአንደኛ እና ሁለተኛ ቆሮንቶስ መልእክት ይዘት ይገልጻል። ጳውሎስ በቆሮንቶስ በሚስዮናዊነት ባደረገው እንቅስቃሴ ከጣዖት አምላኪና ሴሰኛ ማኅበረሰብ ፈተና ገጥሞት ነበር። በዛሬው ጊዜ ባለው ባሕል ወንጌል መስበክን አስቸጋሪ የሚያደርጉት ተፈታታኝ ሁኔታዎች የትኞቹ ናቸው? እንዴትስ ልናሸንፋቸው እንችላለን? ዛሬ በቆሮንቶስ እና በእኛ ከተሞች መካከል ምን ያህል ልዩነት አለ?
@SabbathSchool @TekalignSorato
ቅድስናን የጠበቀ እጮኝነት፦ በመንፈሳዊ ስነ-ምግባር መተዋወቅና መፍቀር
የህይወት አጋር ምርጫ፦ የእግዚአብሔርን ፍቃድ እንዴት እናውቃለን?
የብቸኝነት (Singlehood) ዘመንን በጥበብ መኖር፦ እራስን ለትልቅ አላማ ማዘጋጀት
ከስሜታዊነት መውጣት እና እውነተኛ ፍቅርን ማወቅ
ለትዳር ራስን በንፅህና ማዘጋጀት
ሰኞ
ሰኔ 22
Jun 29
ከአቴንስ እስከ ቆሮንቶስ
የሐዋርያት ሥራ 17:16–34ን አንብቡ። ጳውሎስ ወደ ቆሮንቶስ ከመሄዱ በፊት የት ነበር? እዚያስ ምን አደረገ?
Save Notes
የሐዋርያት ሥራ 17:16–34 ጳውሎስ ወደ ቆሮንቶስ ከመሄዱ በፊት ለአቴናውያን የሰበከውን ስብከት ይገልጻል። በግልጽ፣ በዚያን ጊዜ አቴንስን ለመጎብኘት አላሰበም፣ ነገር ግን በቤርያ ባጋጠመው ተቃውሞ ምክንያት በአንዳንድ ጓደኞቹ እርዳታ ወደዚያ ሄደ (ሐዋ. 17:13–15)።
ከጳውሎስ ጋር ወደ አቴና የሄዱት ሰዎች፣ ጢሞቴዎስና ሲላስ በተቻለ ፍጥነት ወደ እርሱ በመሄድ አብረውት ይሆኑ ዘንድ ትእዛዝ ይዘውላቸው ወደ ቤርያ ተመለሱ (ሐዋ. 17:15)። የሐዋርያት ሥራ 17:16-34 ጳውሎስ ሲጠብቃቸው ሳለ ያደርግ ስለነበረው ነገር ይናገራል። ስለ የሱስ በምኩራብ፣ በገበያ ቦታና በአርዮስፋጎስ ተናግሯል። ስለ የሱስ መናገሩን ማቆም አልቻለም እናም ያገኘውን አጋጣሚ ሁሉ ተጠቅሞበታል። የሐዋርያት ሥራ 18:1-11ን አንብቡ። ጳውሎስ ወደ ቆሮንቶስ ሲደርስና በዚያች ከተማ በነበረው የቆይታ ጊዜ ሁሉ ምን አደረገ?
Save Notes
ጳውሎስ በሁለተኛው ሚስዮናዊ ጉዞው ወደ ቆሮንቶስ ሄደ። ጳውሎስ እዚያ አንድ ዓመት ተኩል እንደቆየ ሉቃስ ገልጾልናል።
እንደተለመደው፣ ጳውሎስ የሚስዮናዊነት ስራውን በምኩራብ ጀመረ (ሐዋ. 18:4-6)። የሐዋርያት ሥራ 17:1፣2 ይህ ልማዱ እንደሆነ ይጠቅሳል። የሱስ ለሐዋርያቱ እንዳዘዛቸው (የሐዋርያት ሥራ 1:8 ይመልከቱ) “በመጀመሪያ ለአይሁድ” የሚለውን ስልት (ሮሜ 1:16፣ የሐዋርያት ሥራ 13:46) ተከተለ።
በመጨረሻ ሲላስና ጢሞቴዎስ በቆሮንቶስ ከጳውሎስ ጋር ሲገናኙ፣ “የሱስ እርሱ ክርስቶስ እንደ ሆነ ለአይሁድ እየመሰከረ ለቃሉ ይተጋ ነበር።” (ሐዋ. 18:5)። በቆሮንቶስ በነበረው ቆይታ፣ “የእግዚአብሔርን ቃል በማስተማር” ተጠምዶ ነበር (ሐዋ. 18:11)። በዚህ አውድ ውስጥ ነበር በቆሮንቶስ ሰዎች መካከል ሳለ እነዚያን “ከየሱስ ክርስቶስ በቀር እርሱም እንደ ተሰቀለ” የሚሉ ዝነኛ የሆኑ ቃላቶችን በመጠቀም (1ኛ ቆሮ. 2:2) “ሌላ ነገር እንዳላውቅ ቆርጬ ነበርና” ሲል የገለጸው። ጳውሎስ በአቴናና በቆሮንቶስ ካደረገው ሚስዮናዊ እንቅስቃሴ የሱስን ለማካፈል ሁሉንም ዕድሎችና ምቹ አጋጣሚዎች ስለ መጠቀም ምን እንማራለን? የሱስን ለሌሎች ለማካፈል ስላሏችሁ ዕድሎችና እንዴት ልትጠቀሙባቸው እንደምትችሉ አስቡ።
@SabbathSchool @TekalignSorato
እሑድ
ሰኔ 21
Jun 28
የየሱስ ሐዋርያ ተብሎ የሚጠራው ጳውሎስ
ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ክርስቲያኖች የጻፈውን መልእክት የጀመረው ‹በእግዚአብሔር ፈቃድ› የየሱስ ሐዋርያ መሆኑን በመግለጽ ነው (1ኛ ቆሮ. 1:1፤ ከ2ኛ ቆሮ. 1:1 ጋር አወዳድሩ)። ከየሱስ ጋር ባለው ማንነቱ ላይ ያለው እምነት በጣም ጽኑ ስለሆነ፣ ከጥቂቶች ሥፍራዎች በስተቀር ደብዳቤዎቹን የሚጀምረው በዚህ ዓይነት መንገድ ነው። 1ኛ ቆሮንቶስ 1:1 እና ሮሜ 1:1ን አንብቡ። በእነዚህ ምንባቦች ውስጥ ሁለት አጽንዖት የተሰጣቸው የጳውሎስ አገልግሎት ጉዳዮች የትኞቹ ናቸው? (ገላ. 1:1ን ተመልከቱ።)
Save Notes
ጳውሎስ ጥሪውና ሐዋርያነቱ የእግዚአብሔርን ፈቃድ መፈጸም እንደሆነ ተናግሯል። ጥሪው ከእግዚአብሔር እንጂ ከሰው እንዳልሆነ እርግጠኛ ሆኗል (ገላ. 1:1)። እንደ ኤርምያስ ሁሉ (ኤር. 1: 5) ጳውሎስም እንደ እግዚአብሔር የጸጋ ሥራ ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ በእግዚአብሔር ለጥሪው ተለይቷል (ገላ. 1: 15)፤ ስለዚህም የክርስቶስን ወንጌል በአሕዛብ መካከል እንዲሰብክ ሆነ።
በ1ኛ ቆሮንቶስ 15:8 ላይ፣ ጳውሎስ ራሱን ከትንሣኤ በኋላ ክርስቶስ ከተገለጠላቸው መካከል አንዱ እንደሆነ ይናገራል (1ኛ ቆሮ. 15:5-7)። ከጥቂት ጥቅሶች በኋላ፣ የሐዋርያነት ጥሪው የመጣው በዚያን ጊዜ ክርስቶስ ከተገለጠለት በኋላ መሆኑን ገልጿል (1ኛ ቆሮ. 15:9–11)።
“የየሱስ ሐዋርያ” የሚለው ማዕረግ ተከታታይ ጽንሰ-ሐሳቦችን ያካትታል። በዋነኛነት የሱስ የላከውን ሰው የመሆንን ሐሳብ ያስተላልፋል። ደግሞም፣ ጳውሎስ ራሱን የክርስቶስ አገልጋይ (ሮሜ 1:1፣ ቲቶ 1:1፣ ገላ. 1:10) ፣ እንዲሁም ሰባኪና አስተማሪ (1ጢሞ. 2:7፣ 2ጢሞ. 1:11) መሆኑን ለመግለጽ ይህን ሐረግ ይጠቀማል። ቢሰብክም ቢያስተምርም ክርስቶስ ምንጊዜም ማስረጃ ነው። በአጭሩ፣ ጳውሎስ የየሱስ ሐዋርያ ነው።
የሱስ የጳውሎስ ሐዋርያነት ማዕከል ብቻ አይደለም። እርሱ የጳውሎስ የሕይወቱ ማዕከልም ነው። የጳውሎስ ሀሳቦች እና ስሜቶች በየሱስ መገኘት ተሞልተዋል። ለዚህም ማስረጃው የሱስን በ1ኛ ቆሮንቶስ የመክፈቻ እና የምስጋና ክፍል (በዘጠኝ ቁጥሮች ዘጠኝ ጊዜ ማለት ነው) ደጋግሞ መናገሩ ነው። ጳውሎስ የሱስን በጣም ይወደው ስለነበር ስለ እርሱ ማሰብና መናገር ማቆም አልቻለም። በእርሱ እንክብካቤ ሥር ላሉትም፣ ሕይወታቸው ክርስቶስን ያማከለ ይሆን ዘንድ የሱስን ለማካፈል ይፈልግ ነበር። እርሱ ለሐዋርያነት ሲጠራ፣ እነርሱም ደግሞ ጌታ በጠራቸው በማናቸውም አገልግሎቶች ታማኝ የየሱስ ተከታዮች እንዲሆኑ ተጠርተዋል። ጳውሎስ ሐዋርያ እንዲሆን ተጠርቷል። እኛስ ጥሪያችን ምንድን ነው? ጥሪያችን መሆኑንስ እንዴት እናውቃለን? ጥሪ የሌለን ከመሰለን፣ ከእግዚአብሔር ጋር ባለን ጉዞ ውስጥ ያለብን ችግር ምንድን ነው?
@SabbathSchool @TekalignSorato
ሰኔ 20 - 26
1ኛ ትምህርት
Jun 27 - Jul 3
የጳውሎስ አገልግሎት በቆሮንቶስ
ሰንበት ከሰዓት በኋላ
ለዚህ ሳምንት ጥናት የሚነበቡ፦ 1ኛ ቆሮ. 1:1 ገላ. 1:1 የሐዋርያት ሥራ 17:16-34 1ኛ ቆሮ. 5:9–11፣ የሐዋርያት ሥራ 18:4–10፣ 2ኛ ቆሮ. 2:4።
የመታሰቢያ ጥቅስ፡ «ጌታም ሌሊት በራእይ ጳውሎስን፡- እኔ ከአንተ ጋር ነኝ፥ ማንም ክፉ ሊያደርግብህ የሚነሣብህ የለምና አትፍራ፥ ነገር ግን ተናገር ዝምም አትበል፤ በዚህ ከተማ ብዙ ሕዝብ አሉኝና አለው» (ሐዋ. 18:9፣ 10)።
ታላቁ እንግሊዛዊ ሚስዮናዊ ዊልያም ኬሪ ኑሮውን ለማሸነፍ ጫማ ይጠግን እንደነበር ይናገር ነበር፤ ነገር ግን እውነተኛው ስራው ነፍሳትን መማረክ ነበር።
በተመሳሳይ፣ ጳውሎስ ለኑሮው ድንኳን ሰፊ ሆኖ ሠርቷል (ሐዋ. 18:1-3)፣ ነገር ግን እውነተኛ ሥራው ሰዎችን ወደ ክርስቶስ ማምጣት ነበር።
በዚህ ሳምንት፣ ጳውሎስ በቆሮንቶስ ከተማ በምትገኘው ቤተ ክርስቲያን ስለነበረው አገልግሎት ፍንጭ እናገኛለን። እንደምናየው ቤተ ክርስቲያኒቱ በብዙ ችግሮች የተሞላች ነበረች፤ ቢሆንም ብዙዎቹ ችግሮች ከሁለት ሺህ ዓመታት በኋላ ዛሬ ቤተ ክርስቲያኖቻችን ከሚገጥሟቸው ነገሮች የተለየ መልክ አልነበራቸውም። በእርግጥም በክርስትና ውስጥ ለረጅም ጊዜ የቆየ ወይም በቤተ ክርስቲያን ሥራ ውስጥ የተካፈለ ማንኛውም ሰው የሚከተለውን ጥያቄ ሊጠይቅ ይችላል፦ ምንም ዓይነት ችግር የሌለበት የክርስቲያን ህብረት አግኝታችሁ ታውቃላችሁ? መልሱ በእርግጥ ግልጽ ነው።
ጳውሎስ በቆሮንቶስ ፈተናዎችን ይጋፈጥ ነበር፤ ነገር ግን ይህን የሚያደርገው በመስቀሉ መልእክት ነበር (1ኛ ቆሮ. 2:2)። ለዚህ መልእክት ታማኝ መሆን በዛሬው ጊዜ ያሉብንን ተግዳሮቶች የምንቋቋምበት መንገድም ነው። በዚህ ሳምንት እና በዚህ ሩብ ዓመት ውስጥ እንደምንመለከተው፣ የ1ኛ እና የ2ኛ ቆሮንቶስ መልእክት በእኛም ሕይወት ላይ ይሠራል።
@SabbathSchool @TekalignSorato
1ኛ እና 2ኛ ቆሮንቶስ - የክርስቲያን ሕይወት እና ምስክርነት ባሕርይ
ደብዳቤ መጻፍ ብዙ ዘመናትን ያስቆጠረ ነገር ግን ያልቀረ ተግባር ነው። እኛ ፊደሎች የሚጻፉበትን መንገድ ብቻ ቀይረናል። አዎ፣ ወረቀት በማህበራዊ ሚዲያ ተተካ። ነገር ግን፣ በይዘታቸው፣ ኢሜይሎች እና ሌሎች የኤሌክትሮኒክ ፊደሎች መሠረታዊ በሆነ መንገድ አንድ አይነት ተግባር ያከናውናሉ፤ ይህም መረጃን፣ ስሜትን እና ሀሳቦችን በማለዋወጥ ሰዎችን ማገናኘት ነው።
ሰዎች ለምን ደብዳቤ ይጽፋሉ? መልሱ የሚናገሩት ነገር ስላላቸው ነው የሚል ሊሆን ይችላል። ለሐዋርያው ጳውሎስም እንዲሁ ነበር። ብዙ የሚናገረው ቢኖረውም ሊያናግራቸው ከሚፈልጋቸው ጋር ፊት ለፊት የመገናኘት ዕድል አልነበረውም።
ከዚያ ይልቅ አንደ ቆሮንቶስ ሰዎች ላሉት፣ አንዳንድ የቅዱሳት መጻሕፍት ጥልቅ እውነቶችን የያዙ ደብዳቤዎችን ጻፈ። ከእነዚህም መካከል፦ “ከየሱስ ክርስቶስ በቀር እርሱም እንደ ተሰቀለ በቀር ምንም እንዳላውቅ ቆርጬ ነበር” (1ኛ ቆሮ. 2፡2) እንዲሁም “የጌታችንን የየሱስ ክርስቶስን ጸጋ አውቃችኋልና እርሱ ባለ ጠጋ ሳለ እናንተ በእርሱ ድህነት ባለ ጠጎች ትሆኑ ዘንድ ስለ እናንተ ድሀ ሆነ” የሚሉት ይገኙበታል (2ቆሮ. 8:9)። በ1ኛ ቆሮንቶስ 13 ላይ የሚገኘው አስደናቂ የፍቅር መዝሙርስ?
በሌላ በኩል፣ የጳውሎስን መልእክት ለቆሮንቶስ ሰዎች ያነበበ ማንኛውም ሰው ግራ መጋባቱ የማይቀር ነው፤ ይህም ግራ መጋባት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ባሉ እንደ ዝሙት ባሉ አንዳንድ ጉልህ ችግሮች ብቻ ሳይሆን፣ በአባላቶቹ መካከል በነበረው ከንቱ መከፋፈል አማካኝነት በተከሰተው መርዝ ምክንያት ጭምር ሊሆን ይችላል። ቤተ ክርስቲያናችሁ ፈታኝ ጉዳዮች እንዳሉባት የምታስቡ ከሆነ፣ ጳውሎስ በቆሮንቶስ ያጋጠመውን አለመግባባት ለማየት ተዘጋጁ። ምናልባት የአጥቢያ ቤተ ክርስቲያናችሁ ችግሮች እናንተ እንደምትገምቱት ጉልህ ላይሆኑ ይችላሉ። ይልቁንም በቆሮንቶስ የነበሩት ነገሮች በጣም የከፉ እንደነበሩ ትገነዘባላችሁ።
በቆሮንቶስ የነበሩት ችግሮች አሳሳቢ እንደሆኑ ሁሉ፣ ለቆሮንቶስ ክርስቲያኖች የጻፋቸው ደብዳቤዎች ትኩረታችንን የሚስቡት ወደ ችግሮቹ ሳይሆን ነገር ግን ጳውሎስ ችግሮቹን በተጋፈጠበት አስደናቂ መንገድ ላይ ነው። ምእመናን ከየሱስ ክርስቶስ ወንጌል አንጻር ራሳቸውን፣ ባህሪያቸውንና የአካባቢያቸውን ባህል እንዲገመግሙ በማሳሰብ የመስቀሉን መልእክት ከፍ ከፍ ያደርጋል። በሌላ ስፍራ የሚገኘውን የጳውሎስን አነጋገር እዚህ ጋ እንጠቀምና፦ ከወንጌል መልእክት ያነሰ ማንኛውም መመዘኛ “የተረገመ” እንደሆነ መታየት አለበት (ገላ. 1:8፣ 9)።
በጳውሎስ ዘመን፣ ቆሮንቶስ በሀብቷ እና በጠንካራ ንግዷ ዝነኛ ነበረች፤ ይህም ሁሉ ደግሞ በወደቧ፣ በሥነ-ሕንጻዎቿ፣ በመርከብ ግንባታዎቿ እና በሸክላ ሥራዎቿ ምክንያት ነበር። ከተማዋ ጠቃሚ የፋይናንስ ማዕከል ነበረች። ቢሆንም፣ በጾታ ብልግና፣ በሃይማኖታዊ መደበላለቋ እና ለተለያዩ አማልክት በተሰየሙ መቅደሶችዋም ትታወቅ ነበር። በእርግጥም፣ በቆሮንቶስ የነበረው የዕለት ተዕለት ኑሮ መናፍቅ ከሆነው ከጣዖት አምልኮ ተለይቶ የሚታወቅ አይደለም። ይህ ታሪካዊና ባሕላዊ ዳራ ጳውሎስ በዚያች ከተማ ስላሉት ክርስቲያኖች ዋና ዋና ጉዳዮች እና በዚህም የተነሳ ለእነርሱ የሰጣቸውን ማሳሰቢያዎች እንድንገነዘብ ይረዳናል።
በዚህ ሩብ ዓመት፣ ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች የላከውን መልእክት እንቃኛለን። በእነዚህ ሁለት አስደናቂ የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ውስጥ፣ ሐዋርያው የወንጌል መልእክትን ለክርስቲያን ሕይወትና ምስክርነት አስፈላጊ፣ እንዲሁም ሌላው ነገር ሁሉ የሚዳኝበት መነጽር አድርጎ አቅርቧል። ወደ መንግሥተ ሰማይ በምናደርገው ጉዞ እያንዳንዳችን በግለሰብ ሆነ በአጠቃላይ በቤተ ክርስቲያን ደረጃ የሚያጋጥሙን ፈተናዎች ምንም ቢሆኑ፣ ለክርስቶስ በምናደርገው ሥራ ውስጥ ላሉ በጣም ግራ የሚያጋቡ ጉዳዮች መልሱ ለቆሮንቶስ ሰዎች የተጻፈው “የሱስ ክርስቶስ… እርሱም እንደ ተሰቀለ” የሚል ነው። (1ኛ ቆሮ. 2:2)
የሱስ በቅርቡ ይመጣል። ይህ ጊዜ በክርስቶስ ሆነን በላቀ አንድነት ውስጥ የምንኖርበት፣ ለመንፈስ ቅዱስ ከመቼውም ጊዜ በላይ ክፍት የምንሆንበት፣ መንፈሳዊ ስጦታዎችን በትጋት የምንጠቀምበት እና ከሞት ከተነሳው ጌታችን ጋር የበለጠ ጥልቅ ልምምድ የምናገኝበት ጊዜ ነው። ጊዜው የእውነተኛ ክርስቲያናዊ አገልግሎት፣ በመጋቢነት እና በተልዕኮ ውስጥ የመሳተፍ፣ ከሐሰት ትምህርቶች ጋር መንፈሳዊ ውጊያ የማድረግና እንዲሁም በጸጋ፣ በፍቅር እና በኅብረት የማደግ ጊዜ ነው። ይህ ጊዜ እምነታችንን አጥብቀን የምንይዝበት እና ለመስቀሉ መልእክት ታማኝ የምንሆንበትም ጊዜ ነው፤ እናም ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች የጻፈው መልእክት ይህን እንድናደርግ የሚስተምረን ነው።
አዴኒልተን ታቫሬስ ደ አጉዋየር (ዶ/ር) በካቾይራ፣ ባሂያ፣ ብራዚል ውስጥ በሚገኘው፣ በሰሜን ምስራቅ የአድቬንቲስት ኮሌጅ ውስጥ የአዲስ ኪዳን ትርጓሜ ፕሮፌሰር ናቸው፤ በዚያም ከ 2010 ጀምሮ ሲያገለግሉ ቆይተዋል።
@SabbathSchool @TekalignSorato
ዓርብ
ሰኔ 19
Jun 26
ተጨማሪ ሀሳብ
“የእግዚአብሔርን ቃል በመመገብ የክርስቶስን ኃይማኖት ካልተቀበልን፣ ወደ እግዚአብሔር ከተማ የመግባት መብት አይኖረንም። ምድራዊ ምግብን በመመገብና ዓለማዊ ነገሮችን የመውደድ ጣዕማችንን እየተለማመድን ከኖርን ለሰማይ አደባባዮች ብቁ አንሆንም፤ በሰማይ የሚዘዋወረውን ንፁህ፣ ሰማያዊ ጅረት ማድነቅ አንችልም። የመላእክት ድምፅና የበገናዎቹ ዜማ አያረካንም። የሰማይ ሳይንስ ለአእምሯችን እንቆቅልሽ ይሆናል። የክርስቶስን ጽድቅ መራብና መጠማት አለብን፤ ለሰማያዊ መላእክት ማኅበር እንድንበቃ በጸጋው ህይወት የመቀየር ተጽዕኖ መቀረጽ አለብን። . . .
“ከዚያም ሕዝቦች ከሰማይ ሕግ ውጪ ሌላ ሕግ አይኖራቸውም። ሁሉም ደስተኛ፣ የተባበረ ቤተሰብ ይሆናሉ፣ የምስጋና ልብስ ለብሰዋል።. . .በትዕይንቱ ላይ የንጋት ከዋክብት አብረው ይዘምራሉ፣ የእግዚአብሔርም ልጆች በደስታ ይዘምራሉ፣ እግዚአብሔር አብ እና ክርስቶስም ‘ከእንግዲህ ኃጢአት አይኖርም፣ ሞትም አይኖርም’ ብለው በአንድነት ያውጃሉ። “ስለ ሰማይ፣ ውብ ስለሆነው ስለ ሰማይ፣ የመናገር ልማድ ማዳበር እንፈልጋለን።
እግዚአብሔር ሕያው እስከሆነ ድረስ የሚቀጥል ሕይወት እንነጋገራለን፣ ከዚያም ትንንሽ ፈተናዎቻችንንና ችግሮቻችንን እንረሳለን። አእምሮአችንም ወደ እግዚአብሔር ይሳብ።”— Ellen G. White, The Faith I Live By, p. 363።
የመወያያ ጥያቄዎች
1. ቀደምት ጽሁፎች ከሚለው መጽሐፍ፣ ገጽ 14-20 ላይ የሚገኘውን ኤለን ጂ. ዋይት ስለ ሰማይ ያየችውን ራዕይ ያንብቡ። በዚህ መግለጫ ውስጥ በጣም የሚያስደንቅዎት ምንድን ነው?
2. ኢየሱስን ፊት ለፊት እስኪያዩት ድረስ ከእግዚአብሔር ጋር ያለዎትን ግንኙነት ኢየሱስን ፊት ለፊት እስኪያዩት ድረስ ከእግዚአብሔር ጋር ያለዎትን ግንኙነት ለማጠንከር ከዚህ የሩብ ዓመት ትምህርት የትኛውን የበለጠ ማስታወስ ያለብዎት ይመስሎታል?
3. በሕይወትዎ ውስጥ ስለ ሰማይ ተስፋ መስማት ያለበት ማን ነው? በተቻለ ፍጥነት በሕይወትዎ ውስጥ ስለ ሰማይ ተስፋ መስማት ያለበት ማን ነው? በተቻለ ፍጥነት ለእነርሱ ለማካፈል ቁርጥ ውሳኔ ያድርጉ። ያስታውሱ፡ እርስዎ ራስዎ የሌለዎትን ተስፋ ለእነርሱ ማጋራት አይችሉም። ማጠቃለያ፡- በግቡ ላይ ስናተኩር፣ በእኛ “መልካም ሥራ የጀመረው እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንደሚፈጽመው እርግጠኞች” እንሁን (ፊልጵ. 1:6)። ከእርሱ ጋር ያለንን ግንኙነት የጀመረው ራሱ እግዚአብሔር ነው፣ እርሱም ይፈፅመዋል። በእምነት ለእኛ በተቆጠረልን በክርስቶስ ጽድቅ ብቻ እያረፍን በፍቅርና በእምነት እንደግ።
@SabbathSchool @TekalignSorato
ሐሙስ
ሰኔ 18
Jun 25
“ኑ!”
ዛሬ በድጋሚ “ኑ” የሚለው ግብዣ ቀርቧል፤ የሚከተሉትን ጥቅሶች ያንብቡና ወደ እርሱ እንድንመጣ የተሰጠውን ግብዣ ያስተውሉ፡ ማቴ. 11:28-30፣ ኢሳ. 55:1-3፣ ዮሐንስ 6:44
Save Notes
መንፈስ ቅዱስ ዛሬ ወደ ኢየሱስ ሊስበን ይፈልጋል። ኢየሱስ እስኪመጣ ድረስ ወደ እርሱ እንድንቀርብ፣ ዛሬም ሆነ በየቀኑ በእርሱ እንድንኖር ይጋብዛል። ምላሽ ስንሰጥና ወደ እርሱ ስንቀርብ፣ ልባችን ለስላሳ ሲሆን አእምሮአችንንም ለርሱ ስናስረክብ፣ በዚህች ምድር የመጨረሻ ቀን ምንም ያህል ብቁ ባንሆን እንደሚያስነሳን ስለምናውቅ ሰላም ይሰማናል።
ኢየሱስ “ወደ እኔም የሚመጣውን ከቶ ወደ ውጭ አላወጣውም” (ዮሐንስ 6:37) ብሏል ። ሌሎች ከኢየሱስ ጋር ወደ መዳን ግንኙነት እንዲመጡ ከቅዱስ መንፈስ ጋር የመሥራት አጣዳፊነት ሊሰማን ይገባል። “መንፈሱና ሙሽራይቱም፦ ና ይላሉ። የሚሰማም፦ ና ይበል።
የተጠማም ይምጣ፥ የወደደም የሕይወትን ውኃ እንዲያው ይውሰድ።”(ራዕ. 22:17)። ግብዣው እንደ ጸጋ ስጦታ በነፃ የሚቀርብ ነው። ወደ ሕይወታችን ስናስገባው እና በልባችን፣ በአእምሯችን፣ በነፍሳችን እና በኃይላችን ሁሉ ስንወደው (ዘዳግም 6:5)፣ ዛሬም ይሁን ለዘላለምም ሕይወታችን ይለወጣል። ኢየሱስ ወደ እርሱ እንድንመጣ እንደሚጋብዘን ሁሉ፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉት የመጨረሻዎቹ ቃላት ይህንን ተስፋ ይሰጡናል፡- “አዎን፥ በቶሎ እመጣለሁ ይላል። አሜን፥ ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ና።” (ራዕ. 22:20)። የሚመጣው እንዴት ባለ ፍጥነት ነው? ከኛ እይታ አንጻር፣ ዓይኖቻችንን በሞት እንደተዘጉ፣ ቀጥሎ የምናውቀው ነገር የክርስቶስ መመለስ ይሆናል። ሕይወታችን ምን ያህል በፍጥነት እንደሚያልፍ ስንመለከት፣ ኢየሱስ ለእኛ በፍጥነት የሚመለስ እንደዚያ ነው።
ምናልባት በትንሣኤው የመጀመሪያ ሀሳባችን “ዋው፣ ጌታ ሆይ፣ መምጣትህ በእርግጥም ቅርብ ነበር!” የሚል ሊሆን ይችላል። በእርግጥ፣ አሁን ግን በመስታወት ውስጥ እንዳለን በድንግዝግዝ እናያለን። ግን በዚያን ጊዜ ፊት ለፊት እናየዋለን። በመጠበቅ መታከታችን ያቆማል። ይህንን ፍላጎት በእምነት፣ በእግዚአብሔር ፍቅር እና በቸርነቱ በመታመን ሁልጊዜ በፊትዎ ሕያው አድርገው ይጠብቁት። ጌታ ኢየሱስ፣ እባክህ ና! እምነታችን እንዲጸና፣ እምነታችን ላዳነን እና ለእኛም በቶሎ ለሚመጣው ለእርሱ ሙሉ በሙሉ ራሳችንን እንድናስረክብ እንዲያስችለን እንፀልይ።
@SabbathSchool @TekalignSorato
ረቡዕ
ሰኔ 17
Jun 24
በጉን ተከተሉ
በሠማይ ምን ለማየት እንደምትጓጉ ተጠይቃችሁ ታውቃላችሁ? ልጆችን ብትጠይቁ፣“ነብር መጋለብ”፣ “ከቀጭኔ አንገት ላይ ተንሸራትቶ መውረድ” ወይም “ወደተለያዩ ፕላኔቶች መብረር” ሊሉ ይችላሉ። ታዳጊዎችን ብትጠይቁት፣ “ከቤት ሥራና ትምህርት ነክ ነገሮች መገላገላችን” ወይም “ያለ ምንም ጉዳት ከጓደኞቼ ጋር መንግሥተ ሰማያት ውስጥ ሳላቋርጥ መዞር” ሊሉ ይችላሉ። የአዋቂዎችን ቡድን ብትጠይቁ፣ “ከዚህ በላይ ህመም፣ ስቃይ ወይም ሞት በሌለበት ቦታ መሆን” ወይም “ከምንወዳቸው ሰዎች ጋር እንደገና መገናኘት” ሊሉ ይችላሉ። እነዚህ ሁሉ ምላሾች ጥሩ እና እውነት ናቸው፣ እና በአዲሱ ሰማይ እና በአዲሱ ምድር የምንጠብቃቸው ብዙ ነገሮች አሉ። ዘላለማዊነት በልባችን ውስጥ ይቀጣጠላል፣ እና በውስጣችን፣ ከዚህ እና አሁን ካለው የበለጠ ነገር መኖር እንዳለበት እናውቃለን። ከዘላለም ሕይወት ምን ሌሎች በረከቶችን ልንጠብቅ እንችላለን? ኢሳይያስ 25:8፣ ራዕይ 7:17 እና ራዕይ 21:4ን ያንብቡ።
Save Notes
በእርግጥ የሰማይ ታላቅ በረከት በመጨረሻ ኢየሱስን ማየት እና በዚህች በወደቀች ምድር ላይ ላደረገልን ነገር በአካል ማመስገን ነው። ከዘላለም ሞት በመስቀል ላይ ስለዳንን ለእሱ ያለንን ፍቅር እና አምልኮ ማጣጣም እንፈልጋለን። “የታረደው በግ ኀይልና ባለጠግነት፣ ጥበብና ብርታት፣ ክብርና ሞገስ፣ ምስጋናም፣ ሊቀበል ይገባዋል!” (ራእይ 5:12)። መጥምቁ ዮሐንስ ኢየሱስን “የእግዚአብሔር በግ” ሲል አስተዋወቀው (ዮሐንስ 1:35- 37)። ደቀ መዛሙርቱም በቅርበት ተከትለውት ነበር፣እና ዮሐንስ ራዕይ 14:4 እኛም እንዲሁ እናደርጋለን ይላል። “ በጉ ወደሚሄድበት የሚከተሉት እነዚህ ናቸው” (ራእይ 14:4)። ሆኖም ግን፣ በሰማይ እርሱን ለመከተል እንድንፈልግ፣ በመጀመሪያ እዚህ ምድር ላይ እርሱን መከተል አለብን። በጉ የሆነው ኢየሱስ እረኛችን ነው፣ እና ከማንም በላይ መንገዳችንን ይመራናል።
ይህ እራሳችንን በምናገኝባቸው አስቸጋሪ ጊዜያት ውስጥ ስንታገል በጣም የሚያጽናና ነው፣ ነገር ግን ኢየሱስ በሰማይም ቢሆን መምራቱን አያቆምም። ራዕይ 7:17 እንዲህ ይላል፣ “በዙፋኑ መካከል ያለው በጉ እረኛቸው ይሆናልና፥ ወደ ሕይወትም ውኃ ምንጭ ይመራቸዋል።” ለዘላለም በእርሱ መገኘት ውስጥ መሆን ስለምንፈልግ እንደ ሕዝቡ፣ በጎቹ፣ ኢየሱስን በሰማይ እንከተላለን። የእግዚአብሔር ሕዝብ አንድ ገላጭ ባህሪ “ስሙ በግምባራቸው ላይ ይሆናል” (ራዕይ 22:4) የሚለው ነው። ማለትም፣ ሁልጊዜ እርሱን እናስባለን። https://www.youtube.com/watch?v=Nejb7N6mm_w በሚለው ሊንክ በመጠቀም “በጉን ተከተሉ” የሚለውን መዝሙር ያዳምጡ እና ስንኞቹን የግል ጸሎትዎ አካል ያድርጉት።
@SabbathSchool @TekalignSorato
የቅድሜ ጋብቻ ስልጠና
ዛሬ ማታ 2 : 30 በዚህ ቴሌግራም ይጀመራል ። ሁላችሁም ተጋብዛችኋል ።
@SabbathSchool @TekalignSorato
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
