ch
Feedback
SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

前往频道在 Telegram
8 909
订阅者
+624 小时
+217
+3630
帖子存档
ዓርብ ሰኔ 5 Jun 12 ተጨማሪ ሀሳብ ከእግዚአብሔር ጋር የበለጠ መጣበቅ የሚያስፈልገን የሕይወትን ፈተናዎች ስንጋፈጥ ነው። በዚህ ሩብ ዓመት ውስጥ የተመለከትናቸው ርዕሶች በሙሉ ከእግዚአብሔር ጋር ጠንካራ ጉዞን ለመጠበቅ ወይም ለማደስ አስተዋጽኦ ያደርጋሉ። እንደ የጤና ችግር፣ የገንዘብ ችግሮች፣ የጋብቻ መፍረስ፣ የቅርብ ሰው ሞት ወይም ደስታን የሚነጥቅዎት ሌላ ችግሮች ሲያጋጥምዎት፣ የሚከተሉትን ጥያቄዎች ያስቡና እስካሁን በተማሩት ትምህርቶች ላይ ያሰላስሉ። የመወያያ ጥያቄዎች 1. የሚያጋጥምዎት ወይም ያጋጠመዎት ማንኛውም ችግር በውስጥዎ በያዙት የእግዚአብሔር ምስል ላይ ተፅዕኖ ያሳደረው እንዴት ነው? የእግዚአብሔርን እውነተኛ ባህሪ የበለጠ በግልፅ ማየት የሚችሉት እንዴት ነው? 2. በሕይወትዎ ውስጥ የእግዚአብሔር ድምጽ ከጠላት የበለጠ ጠንካራ እንዲሆን ለመጨረሻ ጊዜ የጸለዩት መቼ ነው? ሌባው (ሰይጣን) ሊሰርቅ፣ ሊገድል እና ሊያጠፋ እንደሚመጣ፣ ነገር ግን እግዚአብሔር የተትረፈረፈ ሕይወት እንደሚሰጠን (ዮሐንስ 10፡10) ያስታውሱ። 3. ልብዎ ትሑት ነው? እግዚአብሔር አሁንም በሕይወትዎ ውስጥ ሉዓላዊ እና መሪ እንደሆነ ያምናሉ? ካልሆነስ፣ ይህንን ትሑት እምነት በግልዎ በእግዚአብሔር ቸርነትና ፍቅር ውስጥ መማር የሚችሉት እንዴት ነው? 4. በእግዚአብሔር ቃል ላይ በየቀኑ ራስዎን እያፀኑ ነው? አስቸጋሪ ጊዜያትን እያለፉ ሲሄዱ፣ እግዚአብሔር የመጀመሪያ ፍቅርዎን እንደገና እንዲያድስልዎ ይጠይቁት። 5. ለመጨረሻ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር የዞሩት፣ እንደማይተዎት ቃል የገባልዎትን እንደሚጠብቅ በመተማመን፣ በጸሎት አጽናኝና አማካሪዎ ወደሆነው ወደ እርሱ የዞሩት (ዕብ. 13:5) መቼ ነው? 6. እምነትዎ ደካማ ከሆነ፣ “ጌታ ሆይ፣ አምናለሁ፤ አለማመኔን እርዳው!” ብለው ይጸልዩ (ማርቆስ 9:24)። ተስፋ ከማስቆረጥ ይልቅ ሊያበረታቱ በሚችሉ ሰዎች ራስዎን ይክበቡ። 7. ዓለም በአብዛኛው ለደካሞች፣ ለማያውቁ፣ ለቆሰሉ እና ለተሰበሩ ሰዎች ግድ የለውም። “ደካማ ስትሆን፣ እኔ ጠንካራ ነኝ” የሚለው የእግዚአብሔር መልእክት የሰዎችን ሕይወት በከፍተኛ ሁኔታ ሊለውጥ የሚችል መልእክት ነው። ዛሬ በዚህ መልእክት ሊያበረታቱት የሚችሉትን ሰው ያስቡ። ማጠቃለያ፡ አሁንም በህመምና በመከራ በተሞላው በኃጢአተኛ ዓለም ውስጥ እያንዳንዳችን በሕይወታችን ውስጥ በሆነ ወቅት ላይ መከራ ይደርስብናል፤ ይህም የእግዚአብሔርን ፍቅር እንድንጠራጠር ሊያደርገን ይችላል። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሱ የተለያዩ ግለሰቦች በሕይወት ውስጥ ለሚያጋጥሙ ችግሮች እንዴት ምላሽ እንደሰጡ መለስ ብለን ስንመለከት፣ በእንደዚህ ዓይነት ጊዜያት የምንሰጠው ምላሽ እና ፍቅሩ ከማይለወጠው አምላክ (ሚል. 3:6) ጋር ያለንን ጉዞ ሊያጠናክር እንደሚችል ድፍረት ሊኖረን ይችላል። @SabbathSchool @TekalignSorato

ሐሙስ ሰኔ 4 Jun 11 ኢየሱስን ይመልከቱ ኢየሱስን ይመልከቱ ተስፋ መቁረጥ ሲሰማዎ ኢየሱስን ማየት ፈልገው ያውቃሉ? በዚህ ህልም ውስጥ ራስዎን ያስገቡ። “በከፍተኛ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ ተቀምጬ፣ ፊቴን በእጄ አድርጌ፣ እንዲህ እያሰላሰልኩ ነበር፡- ኢየሱስ በምድር ላይ ቢሆን ኖሮ ወደ እርሱ እሄድ ነበር፣ እራሴን በእግሩ ስር እጥል ነበር፣ እናም ሥቃዬን ሁሉ እነግረው ነበር። ከእኔ ፊቱን አያዞርም፣ ይራራልኝ ነበር፣ እና ሁልጊዜም እወደዋለሁ እና አገለግለዋለሁ። በዚያን ጊዜ በሩ ተከፈተ፣ እና የሚያምር መልክና ሞገስ ያለው ሰው ገባ። በርህራሄ ተመለከተኝና “ኢየሱስን ማየት ትፈልጋለህ? እዚህ አለ” አለኝ። እና ማድረግ ከፈለግክ እሱን ማየት ትችላለህ። ያለህን ሁሉ ተሸከምና ተከተለኝ።” “ይህንን በማይነገር ደስታ ሰማሁ፣ እና ትንንሽ ንብረቶቼን፣ እያንዳንዱን ውድ ዋጋ ያላቸውን ጌጣጌጦች በደስታ ሰብስቤ መሪዬን ተከተልኩት። ወደ ዳገት እና አድካሚ ደረጃ መራኝ።” ደረጃዎቹን መውጣት ስጀምር፣ እንዳልዞርና እንዳልወድቅ ዓይኖቼን ወደ ላይ እንዳተኩር አስጠነቀቀኝ። ሌሎች ብዙ ሰዎች ዳገቱን ሲወጡ ወድቀዋል። “በመጨረሻም የመጨረሻውን ደረጃ ደርሰን በበሩ ፊት ቆምን። ከዚያ መሪዬ የያዝኳቸውን ነገሮች ሁሉ በዚያ እንድተው ነገረኝ። በደስታ አስቀመጥኳቸው፤ ከዚያም በሩን ከፈተና እንድገባ አዘዘኝ። ከጥቂት ጊዜ በኋላ በኢየሱስ ፊት ቆምኩ። ያን ውብ ፊት ምንም ልስተው አልችልም። እንዲህ ያለ የደግነትና የክብር አንጸባራቂ መግለጫ የሌላ ሊሆን አይችልም። እይታው በእኔ ላይ ሲያርፍ፣ በሕይወቴ ውስጥ ያለውን እያንዳንዱን ሁኔታ እና ውስጣዊ ሀሳቤን እና ስሜቴን ሁሉ እንደሚያውቅ ወዲያውኑ አወቅኩ።” “ከዓይኑ ለመሸሽ ሞከርኩ፣ የሚመረምሩ አይኖቹን መቋቋም እንደማልችል ተሰማኝ፣ ነገር ግን በፈገግታ ቀረበ፣ እጁንም በራሴ ላይ አድርጎ “አትፍራ” አለ። የጣፋጭ ቃሉ ድምፁ ድምፅ ልቤን ከዚህ በፊት አግኝቼው በማላውቀው ደስታ ሞላው። በጣም ደስተኛ ከመሆኔ የተነሳ አንድም ቃል ለመናገር አልቻልኩም ፣ ነገር ግን በማይነገር ደስታ ተሸንፌ፣ በእግሩ ስር ተደፋሁ።” ምንም ማድረግ ባልቻልኩበት ጊዜ፣ የውበትና የክብር ትዕይንቶች ከፊቴ አለፉ፣ እናም ወደ ሰማይ ደህንነትና ሰላም የደረስኩ መሰለኝ። በመጨረሻም ኃይሌ ተመለሰ፣ እኔም ተነሳሁ። የኢየሱስ አፍቃሪ ዓይኖች አሁንም በእኔ ላይ ነበሩ፣ ፈገግታውም ነፍሴን በደስታ ሞላው። መገኘቱ በቅድስና አክብሮትና በማይገለጽ ፍቅር ሞላኝ። . . . . . . . “ይህ ሕልም ተስፋን… እና እምነትን ሰጠኝ። . . . እናም በእግዚአብሔር የመታመን ውበትና ቀላልነት በደነዘዘው ነፍሴ ላይ መታየት ጀመረ።”—ኤለን ጂ. ዋይት፣ ቀደምት ፅሑፎች፣ ገጽ 79-81። በሕይወት መሰናክሎች መካከል፣ በኢየሱስ እና እርሱ ስለ እግዚአብሔር ፍቅር ለኛ በሚገልጸው ነገር ላይ ማተኮር አለብን። በሮሜ 8:18፣ 28 ላይ ከተጻፈው ውስጥ አሁን ለራስዎ ምን ተስፋ መውሰድ ይችላሉ? @SabbathSchool @TekalignSorato

ረቡዕ ሰኔ 3 Jun 10 የኤማሁስ መንገድ የኤማሁስ መንገድ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ያጋጠሟቸውን አንዳንድ ክስተቶችና ውይይቶች በአእምሯቸው ሲያመላልሱ ይደነቁ ነበር። ወደ ኢየሩሳሌም እንደ ንጉስ መግባት፣ ቤተ መቅደሱን ማጽዳት፣ በላይኛው ክፍል የፋሲካ በዓል፣ በጌቴሴማኒ የኢየሱስ ጸሎት፣ የይሁዳ አስቀያሚ ክህደት፣ የፍርድ ሂደቱ፣ መሳለቁ፣ ግርፋቱ፣ ኢየሱስ በመስቀል ላይ መሰቀሉ እና ከሰዓት በኋላ የመጨረሻ ቃላቱን ከመናገሩ በፊት ሰማዩ ወደ ጥቁር መለወጡ፣ የቤተ መቅደሱ መጋረጃ በከፍተኛ ድምፅ መቀደዱ፣ የጻድቃን መቃብር መከፈቱ፣ የኢየሱስን አስከሬን በቀስታ ከመስቀሉ ላይ አውጥተው ሰንበት ከመግባቱ በፊት በመቃብር ውስጥ ማስቀመጣቸው። ከዚያም ግራ መጋባቱ፣ ተስፋ መቁረጡ እና በደቀ መዛሙርቱ አእምሮ ውስጥ የተመላለሱት ጥያቄዎች። እንዴት ይህን ያህል ተሳሳቱ? የኢየሱስ ተከታዮች አዝነው፣ ተስፋ ቆርጠው እና ግራ ተጋብተው ነበር። ይህ በሕይወታቸው ውስጥ ትልቁ መሰናክል ነበር። ያላስተዋሉት ነገር ቢኖር ይህ በዓለም ታሪክ ውስጥ ታላቅ ጊዜ መሆኑን ነው። ሁለቱ ወደ ኤማሁስ በሚወስደው መንገድ ላይ ሲሄዱ፣ ኢየሱስ ተገለጠና አብሯቸው መሄድ ጀመረ። በሉቃስ 24:13-27 ላይ ያለውን ውይይት ያንብቡና ስለ ሁለቱ ደቀመዛሙርት እና ስለ ኢየሱስ አመለካከቶች ያስቡ። Save Notes ዓይኖቻቸው እንደ ተከፈቱ፣ ሁለቱ ተከታዮች በመንገድ ላይ ስለተከሰቱት ነገሮች ለመንገር ወደ ኢየሩሳሌም ሮጡ (ሉቃስ 24:33-34)። ኢየሱስ መጥቶ በመካከላቸው ሲቆሞ ፈርተው ነበር። እነርሱን የጠየቃቸውን ጥያቄዎች ልብ ይበሉ፡- “ለምን ትጨነቃላችሁ? ለምንስ ጥርጣሬ በልባችሁ ይገባል?”(ሉቃስ 24:38)። ይህ ዛሬም ለእኛ ያለው የኢየሱስ መልእክት ነው። ብዙ ጊዜ፣ ኢየሱስ በሸለቆዎቻችን ውስጥ ከጎናችን እንደሚሄድ እንረሳለን። ብዙ ጊዜ እሱን አናውቀውም። ብዙ ጊዜ በታሪኩ ውስጥ ብዙ ተጨማሪ ነገሮች እንዳሉ እንረሳለን። ኢየሱስ ሕይወታችንን በእጁ ውስጥ በአስተማማኝ ሁኔታ እንደያዘው በመርሳት ብዙ ጊዜ እንጨነቃለን እና በልባችን ውስጥ ጥርጣሬ እንዲፈጠር እንፈቅዳለን። እና ብዙ ጊዜ በሕይወታችን ውስጥ ስለሚሆነው ነገር ከኢየሱስ የተሻለ እናውቃለን ብለን እናስባለን (ሉቃስ 24:18)። መጽሐፍ ቅዱስ እኛ ክርስቲያኖች ለተግዳሮቶች እና ለችግር እንዴት ምላሽ መስጠት እንደምንችል ጥሩ ምክር ይሰጣል። እነዚህን አጫጭር ምንባቦች ለማጥናት ጊዜ ይውሰዱ፡ ሮሜ 8:28፤ ፊልጵ.4:4-13፤ ያዕቆብ 1:2-4፣ 12፤ እና 2 ቆሮ. 12:9-10። እንደ ጥናትዎ አካል፣ 2 ቆሮንቶስ 1:4ን በአእምሮዎ በመያዝ አሁን ችግር ላጋጠመው ሰው ሊያካፍሏቸው የሚችሏቸውን ሶስት ቁልፍ መልዕክቶች ይፃፉ። @SabbathSchool @TekalignSorato

ማክሰኞ ሰኔ 2 Jun 9 ኢዮብ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስላሉ መሰናክሎች ስናስብ፣ ምናልባት መጀመሪያ ወደ አእምሮዋችን የሚመጣው ሰው ኢዮብ ሊሆን ይችላል። ሀብቱን ሁሉ አጥቷል (ኢዮብ 1:14- 17)፣ ልጆቹን (ኢዮብ 1:18-19) እና ጤንነቱንም አጥቷል (ኢዮብ 2:7)። ከዚያም ሚስቱ እግዚአብሔርን እንዲረግምና እንዲሞት ልታሳምነው ሞከረች (ኢዮብ 2:9)። ከተወሰነ ጊዜ በኋላ፣ ሦስት ጓደኞች ከኢዮብ ጋር ለመቀመጥ መጡ። ሲያዩት በጣም ስለ ደነገጡ ከእሱ ጋር ለሰባት ቀናት ምንም መናገር ሳይችሉ ተቀመጡ (ኢዮብ 2:13)። በመጨረሻም ሲናገሩ፣ እንዲህ ዓይነቱ መከራ ለምን እንደመጣበት ሰውኛ ምክንያቶችን ለማቅረብ ቢሞክሩም ይህን ሲያደርጉ ስቃዩን ጨመሩበት። ሦስት ጓደኞቹ “በሕይወትህ ውስጥ ያልተናዘዝከው ኃጢአት ቢኖር ነው” ብለው ወቀሱት (ኢዮብ 8፣ 11፣ 15)፣ እንዲያውም “በእውነት የኃጢአተኞች ቤት እንዲሁ ናት፥ እግዚአብሔርንም የማያውቅ ሰው ስፍራ ይህ ነው።” (ኢዮብ 18:21) ብለው በድፍረት ተናገሩ። ኢዮብ ምላሽ የሰጠው እንዴት ነበር? ኢዮብ 19:23-27ን እና ኢዮብ 23:8ን ያንብቡ። Save Notes በአሳዛኝ ክስተቶች ቢከበብም እና ባያስተውላቸውም፣ ኢዮብ ታማኝ ሆኖ ቀጠለ፣ ጸና። እግዚአብሔርን አልወቀሰም፣ አልረገመውም። በምትኩ፣ እግዚአብሔርን ለመውቀስ ሲፈተን፣ “ራቁቴን ከእናቴ ማኅፀን ወጥቻለሁ፣ ራቁቴንም ወደዚያ እመለሳለሁ።እግዚአብሔር ሰጠ እግዚአብሔርም ነሳ፤ የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን” (ኢዮብ 1:21) ብሎ አወጀ። እኛም በዚሁ ጦርነት መካከል እንኖራለን። ሰይጣን ስለ አፍቃሪው አምላካችን ያለንን ምስል ለማዛባት ባለው እቅድ መሠረት በህመም፣ በመከራ፣ በኪሳራ እና በችግር ያጠቃናል። በዚህ ጊዜ፣ በሁለት መንገዶች ምላሽ መስጠት እንችላለን፡ እግዚአብሔርን መውቀስ እና መካድ ወይም በሙሉ ኃይላችን ከእርሱ ጋር መጣበቅ። ጦርነቱ በዙሪያችን ቢበዛም፣ ከዘላለም አንፃር፣ ጊዜያዊ ችግሮቻችን ጊዜያዊ ፈተናዎች መሆናቸውን ማስታወስ አለብን (2ኛ ቆሮ. 4:16-18)። እዚህ እና አሁን ከምናየው በላይ ብዙ ነገሮች አሉ፣ እና ለአማኝ ከሚገጥሙት ታላላቅ ፈተናዎች አንዱ በጣም ጨለማ በሆነ ጊዜም ቢሆን እግዚአብሔርን ማመን ነው። እግዚአብሔር በብዙ መንገዶች የፍቅሩን እውነታ ገልጦልናል። አሁን ባንረዳውም እንኳ እግዚአብሔር ፍቅር ነው ከሚለው ከዚህ ወሳኝ እውነት ጋር መጣበቅ አለብን። @SabbathSchool @TekalignSorato

ሰኞ ሰኔ 1 Jun 8 ተፈወሺ በገሊላ ዳርቻ የነበሩትን ሰዎች አስቧቸው። ከጠዋት ጀምሮ የኢየሱስን መመለስ ሲጠባበቁ ቆይተዋል፣ከጀልባውም ሲወርድ፣ ወደ ቅፍርናሆም መንደር ተከትለውት ገቡ። በድንገት የምኩራብ አለቃ የሆነው ኢያኢሮስ መጥቶ ልጁን እንዲያድንለት ለመነው። ከሕዝቡ መካከል አንዷ ደግሞ ለብዙ ዓመታት ጤነኛ ያልነበረች ሴት ነች። ከብዙ ባለ መድኃኒቶችም ብዙ ተሠቃየች፤ ገንዘብዋንም ሁሉ ከስራ “ባሰባት እንጂ ምንም አልተጠቀመችም” (ማርቆስ 5:26)። ስለዚህ የገሊላ ታላቅ ሰው ሰምታ በልቧ ተስፋ ይዛ፣ በዚያ ጠዋት ከሕዝቡ ጋር ለመቀላቀል የነበራትን ትንሽ ጥንካሬ አሰባስባ ከቤቷ ወጣች። ወደ ኢየሱስ ስትቀርብ ከሕዝቡ መጨናነቅ የተነሳ ሊታፈን ተቃርቧል። ከዚያም በመገፋፋት ውስጥ አየችው። “ልብሱን ብነካ እድናለሁ” (ማርቆስ 5:28) ብላ ራሷን አበረታታች። ማርቆስ 5:21-34ን ያንብቡ። እዚህ ቦታ ላይ ምን ተፈጠረ፣ እኛስ ምን እንማራለን? Save Notes ይህ ክስተት ለታመሙት፣ ብቸኝነት ለሚሰማቸው እና በሕዝቡ መካከል ሆነው ለጠፉት ሰዎች የኢየሱስን እንክብካቤ እና ርህራሄ ያሳያል። በዚያ ቀን ብዙዎች ከሕዝቡ ጋር ሲጋፉ ከኢየሱስ ጎን ሲያጨናንቁት የነበሩ ቢሆንም በጣም የምትፈልገውን በረከት ለመቀበል አንዲት ሴት ብቻ ኢየሱስን ለመንካት እጇን ዘረጋች። ሆኖም፣ የፈወሳት የእሷ መንካት አልነበረም፤ ያዳናት በክርስቶስ ላይ የነበራት እምነት ነበር (ማርቆስ 5:34)። “አዳኙ የእምነትን መንካት በቸልታ ከተደረገው የሕዝብ ተራ መነካካት መለየት ችሏል።”—ኤለን ጂ. ኋይት፣ የዘመናት ምኞት፣ ገጽ 344። የኢየሱስ ልብስ ምንም ልዩ ኃይል አልነበረውም፤ ይልቁንም እንድትፈወስ ያስቻላት የሴቲቱ እምነት እና እሱን ለመንካት መነሳቷ ነበር። ያች ደካማ ሴት፣ በሥቃዩና በጭንቀቷ ውስጥ፣ በዚያ ጠዋት ቤት ውስጥ አልጋ ላይ ልትቆይ ትችል ነበር፣ ነገር ግን በምትኩ፣ ኢየሱስ ይፈውሰኛል ብላ ተስፋ በማድረግ ወዳጁ ለመሆን ፈለገችው። እርሱን በሩቅ ማየት ብቻ በቂ አልነበረም፤ ወደ እርሱ ቀርባለች። ኢየሱስ ዛሬም እንዲሁ እንድናደርግ ይጋብዘናል። እንዲህ ይላል፡-“እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ። ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤” (ማቴ. 11፡28-29)። ለመዳን እጅግ ፍላጎት የነበራት ይህች ሴት በሮሜ 5፡3-5 ላይ ያሉትን ሀሳቦች በተግባር የገለፀችው እንዴት ነበር? ይህ በሕይወትዎ ውስጥ ምን ሊመስል ይችላል? @SabbathSchool @TekalignSorato

እሑድ ግንቦት 30 Jun 7 የሕይወት አውሎ ነፋሶች ኢየሱስ ቀኑን በገሊላ ዳርቻ ላይ ብዙ ሕዝብ ሲያስተምር አሳልፏል። የኢየሱስ ቃላት በሰዎች አእምሮ ውስጥ ለረጅም ጊዜ እና ለዘላለም ይስተጋባሉ። ቀኑ ሲመሽ፣ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ አብረውት ጉዞ እንዲጀምሩ ጋበዛቸው። “ወደ ማዶ እንሻገር” (ማርቆስ 4:35)። ኢየሱስ አውሎ ነፋስ እንደሚመጣ ያውቅ ነበር ነገር ግን ቢሆንም አብረው እንዲሄዱ ሐሳብ አቀረበላቸው። ለቅርብ ተከታዮቹ የሚያስተምራቸው አስፈላጊ የሕይወት ትምህርት ነበረው። ቀጥሎ ምን እንደተከሰተ ታውቃላችሁ። ስለዚህ አውሎ ነፋስ በማርቆስ 4:35-41 ላይ እንደገና ያንብቡ። ከዚህ ስለ እምነት ምን ትምህርቶችን መውሰድ እንችላለን? Save Notes እነዚህን ነጥቦች ያስቡባቸው፡- 1. ኢየሱስ በጀልባው ውስጥ ባለው ብቸኛ ትራስ ላይ ተኝቷል። የዓሣ ማጥመጃ ጀልባዎቹ ከኋላ ለሚቀመጠው የጀልባው ሹፌር የተዘጋጀ ብዙውን ጊዜ አንድ ትራስ ነበራቸው። በኋለኛው በኩል ያለው ሰው ጀልባውን ወደ መድረሻው ይመራው ነበር። ስለዚህ እዚህ፣ ኢየሱስ የጀልባው “ሹፌር” ቦታ ላይ ነው፣ ነገር ግን በመሽከርከሪያው በኩል ተኝቶ ነበር። 2. ሁሉም ደቀ መዛሙርት ለመርከብ ጉዞ አዲስ አልነበሩም። ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ እና ዮሐንስ ልምድ ያላቸው ዓሣ አጥማጆች ነበሩ። የገሊላን ባሕር እንደ እጃቸው ቆዳ ያውቁ ነበር፣ እና አውሎ ነፋስን እንዴት መቋቋም እንደሚችሉም ያውቁ ነበር። 3. ይህ ኢየሱስ እንቅልፍ እንደ ወሰደው የሚገልፅ ብቸኛው የወንጌል ዘገባ ነው። በሕይወታቸው ውስጥ ካሉት እጅግ አስከፊ አውሎ ነፋሶች አንዱ በሆነው በዚህ ወቅት፣ ደቀ መዛሙርቱ ሲፈሩና ሊሞቱ እንደሆነ ሲያስቡ፣ ኢየሱስ በኋለኛው በኩል ተኝቷል። ... 4. ደቀ መዛሙርቱ በችግር ጊዜ የሰጡት ምላሽ “ግድ አይልህም ወይ?” የሚል ነው። የኢየሱስን ባህሪ እና ለእነሱ ያለውን ፍቅር በጥያቄ ውስጥ አስገቡ። ብዙ ጊዜ፣ አስቸጋሪ ጊዜያት ሲያጋጥሙን ይህ የእኛ ምላሽ ነው። እንደ ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ ራሳችንን ለማዳን መሞከር የምንችለው በተስፋ መቁረጥ መካከል ነው፣ ወይም አንዳንድ ጊዜ ህመም ወይም ኪሳራ ሲመጣብን የእግዚአብሔርን ፍቅር እና እንክብካቤ መጠየቅ ወይም መጠራጠር እንጀምራለን። ከሰብአዊ እይታችን አንጻር እኛ በምናስበውና በምናየው ነገር ላይ በመመስረት በተወሰነ መንገድ እርምጃ መውሰድ እንዳለበት እንገምታለን። ነገር ግን፣ እንደ ደቀ መዛሙርቱ፣ እግዚአብሔር ታላላቅ ተአምራትን ሊያደርግ የሚችለው በህይወት አውሎ ነፋሶች ውስጥ እንደሆነ ማየት እንችላለን። በግልጽ አለመንቀሳቀሱ ለእኛ ትርጉም ባይሰጥም እግዚአብሔር ሁልጊዜ ታማኝ ነው። ከእኛ ጋር በማዕበላችን ውስጥ ነው፤ እናም እኛ ማቆም የማንችለውን ወጀብ ፀጥ ማድረግ ይችላል። በህይወትዎ ውስጥ ወጀብ ሲመጣ የሁልጊዜ ምላሽዎ ምንድነው? እንደዚህ አይነት ጊዜያት ከእግዚአብሔር ጋር ባለዎት ግንኙነት ላይ እንዴት ተጽዕኖ ያሳድራሉ? 2ኛ ቆሮንቶስ 5፡7ን መቼ ነው የኖሩት? @SabbathSchool @TekalignSorato

ግንቦት 29 - ሰኔ 5 11ኛ ትምህርት Jun 6 - 12 መሰናክሎች ሰንበት ከሰዓት በኋላ ለዚህ ሳምንት ጥናት የሚከተሉትን ጥቅሶች ያንብቡ፡ ማርቆስ 4:35-41፣ ማርቆስ 5:21-34፣ ሮሜ 5:3-5፣ ኢዮብ 19:23-27፣ ኢዮብ 23:8-12፣ ሉቃስ 24:13-27፣ ሮሜ 8:18፣28። የመታሰቢያ ጥቅስ፡ “በዚህ ብቻ ሳይሆን በመከራችንም ሐሤት እናደርጋለን፤ ምክንያቱም መከራ ትዕግሥትን እንደሚያስገኝ እናውቃለን። ትዕግሥት ጽናትን፣ ጽናት የተፈተነ ባሕርይን፣ የተፈተነ ባሕርይ ተስፋን፤ ይህም ተስፋ ለዕፍረት አይዳርገንም፤ እግዚአብሔር በሰጠን በመንፈስ ቅዱስ ፍቅሩን በልባችን አፍስሶአልና።” ሮሜ 5፡3-5 አንድ ምሽት፣ ፀሐይ ከአድማስ በላይ ስትጠልቅ፣ አንዲት ወጣት ልጅ ወደ ቤት እየሄደች በጨለማ አውሎ ነፋስ መጣ። የሚያሳልፍ መንገድ እንዳለ ስላወቀች፣ ፍጥነቷን ጨመረች። አንድ የዝናብ ጠብታ በጉንጯ ላይ ወደቀ፣ ከዚያም ሌላ፣ እና ሳታውቀው፣ በሰበሰች። የቤቷ በር ጋ እስክትደርስ ድረስ ሮጠች፤ አባቷም ከፊት ለፊት በር ወደ እሷ እየሮጠ መጣ። ብርድ ልብሱን በትከሻዋ ላይ ሲያሳርፍ፣ “አሁን በዝናብ ውስጥ አየሁሽ። ለምን በእያንዳንዱ የመብረቅ ብልጭታ ውስጥ አልሮጥሽም? ወደ ላይ ለማየትና ፈገግ ለማለት ነበር እንዴ?” ሲል ጠየቃት። “ኦህ፣ ወደ ላይ ለማየት ቆሜ ነበር” አለች፣ “ምክንያቱም እግዚአብሔር ፎቶ እያነሳኝ ነበር!” የሕይወት አውሎ ነፋሶች ሲመጡ ወይም ከእግዚአብሔር ጋር ባለን ግንኙነት ውስጥ አንዳንድ መሰናክሎች ሲኖሩ ምላሻችን ምንድን ነው? ዝናቡ ጀርባችንን ሲደበድበን ጭንቅላታችንን ዝቅ እናደርጋለን ወይስ እግዚአብሔር እንዳለ በማወቅና በማመን ወደ ላይ እንመለከታለን? በዚህ ሳምንት፣ ሕይወት ፈታኝ በምትሆንበት ጊዜ ብዙ ጊዜ የምንሰጣቸውን አንዳንድ ምላሾች እንመረምራለን። የሕይወትን መሰናክሎች በጣም አስፈላጊ የሆነውን ግንኙነታችንን፣ ለማዳከም ሳይሆን ለማጠንከር እንዴት እንደምንጠቀም እናስባለን።  @SabbathSchool @TekalignSorato

ዓርብ ግንቦት 28 Jun 5 ተጨማሪ ሀሳብ መጽሐፍ ቅዱስ ብዙውን ጊዜ የእኛን መንፈሳዊ ሁኔታ ለመግለጽ የግብርና ዘይቤዎችን ይጠቀማል። ሆሴዕ 10፡12 በዚህ ሳምንት የተወያየንበትን የሚይዝ አንድ ምሳሌ ነው፡- “እግዚአብሔር መጥቶ ጽድቅን እስኪያዘንብላችሁ ድረስ እርሱን የምትሹበት ዘመን ነውና ለእናንተ በጽድቅ ዝሩ፥ እንደ ምሕረቱም መጠን እጨዱ፥ ጥጋታችሁንም እረሱ።” (ሆሴዕ 10፥12) እኛ እንዘራለን፥ እናጭዳለን፥ ጠንካራውንም አፈር እናለሰልሳለን፥ እግዚአብሔር ወደ እርሱ እንዲቀርብም እንፈልጋለን። የልባችን አፈር ለዝናብ (መንፈስ ቅዱስ) ዝግጁ መሆን አለበት። እግዚአብሔር አፈሩን ለማዘጋጀት ፍላጎት ሊሰጠን ይችላል፥ ነገር ግን በዋናነት ከእግዚአብሔር ጋር ያለን ግንኙነት አጋርነት ነው (ፊልጵ. 2፡12፣ 13ን ይመልከቱ)። ፊታችንን ወደ እርሱ ማዞር፥ ወደ እርሱ መዘርጋት እና ከእርሱ ጋር መጣበቅ አለብን። ከዚያም የቀረውን ለማድረግ በእኛ ውስጥ ይሠራል። ከእግዚአብሔር ጋር መጣበቅ ምን ማለት እንደሆነ የሚያሳይ አንድ ጥሩ ምሳሌ በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ ይገኛል፡- “ “ብዔልፌጎርን የተከተሉትን ሰዎች ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከመካከላችሁ እንዳጠፋ፥ እግዚአብሔር በብዔልፌጎር ያደረገውን ዓይኖቻችሁ አይተዋል። “እናንተ ግን አምላካችሁን እግዚአብሔርን የተከተላችሁ እስከ ዛሬ ድረስ ሁላችሁ በሕይወት ትኖራላችሁ።”— ዘዳግም 4፥3-4 የመወያያ ጥያቄዎች 1. “ወደ ፈተና አታግባን፥ ከክፉም አድነን እንጂ” (ማቴ. 6:13)። ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን በዚህ መንገድ እንዲጸልዩ በተለይ አስተምሯቸዋል፣ ነገር ግን ይህንን ኃሳብ በዕለት ተዕለት ጸሎታችን ውስጥ እንይዘዋለን? ከፈተናና ከኃጢአት እንዲጠብቀን ምን ያህል አዘውትረን እንጸልያለን? 2. የክርስቶስን የጽድቅ ልብስ ውድ ስጦታ ክርስቲያን ላልሆነ ወይም አዲስ አማኝ የምትገልፁለት እንዴት ነው? 3. የክርስቶስ የጽድቅ ልብስ ንስሐ የገባ ኃጢአተኛን ይቅር ስለ ማለትና ስለ ማንፃት ከሚያተኩረው ከቤተመቅደሱ መልእክት ጋር የሚገናኘው እንዴት ነው? እርስዎ የዚህን መልእክት ውበትና ጥልቀት ምን ያህል ተረድተውታል? ማጠቃለያ፡- ለመንፈስ ቅዱስ ወቀሳ ምላሽ በመስጠት ኃጢአታችንን መለየት እና ራሳችንን በንስሐ ማስገዛት ከእግዚአብሔር ጋር የበለጸገ ግንኙነት ለመፍጠር ወሳኝ እርምጃዎች ናቸው። ሙሉ በሙሉ ይቅር እንደተባልን እና በኢየሱስ የጽድቅ ካባ እንደተሸፈንን ማወቅ ለሰው ልጅ እጅግ በጣም ለውጥ የሚያመጣው ልምምድ ነው። የኃጢአት ሸክም መነሳቱ እንዲሰማን ብቻ ሳይሆን፣ ወደ እርሱ ስንቀርብ የእግዚአብሔር ፍቅር በዙሪያችን እንዳለ ይሰማናል። ይህም ከእግዚአብሔር ጋር ያስተሳስረናል፣ በመንፈሳዊ ረገድ ያጠነክረናል፣ እና በሁለንተናችን እንድንወደው ግድ ይለናል። @SabbathSchool @TekalignSorato

ሐሙስ ግንቦት 27 Jun 4 እጅግ ውድ የሆነው ልብስ በዓለማዊ መመዘኛዎች ጥሩ ልብስ ብዙውን ጊዜ ባለጠጎችን የሚገልፅ ነው። አንዳንድ ሰዎች “እኔ ማን እንደሆንኩ ለመግለጽ በዚህ መንገድ እለብሳለሁ” ይላሉ። ነገር ግን በሰማይ፣ ከግንኙነቶቻችን ውጪ ያለው ነገር ሁሉ ይጠፋል (ማቴ. 6:19-21)። የግል ማንነታችን በኢየሱስ እና ፍጹም በሆነው የጽድቅ ልብሱ መጠቅለል አለበት። ይህንን ለማስረዳት ኢየሱስ በማቴዎስ 22:1-14 ላይ የጻፈውን ምሳሌ ያንብቡ። በዚህ ምሳሌ ውስጥ ምን መልእክቶችን ማግኘት እንችላለን?.. Save Notes ኢየሱስ የሠርግ ልብስ ያልለበሰውን ሰው “ወዳጄ” ብሎ ጠርቶታል፤ ምንም እንኳን ምላሽ ባይሰጥም፣ ግንኙነት ግን ነበራቸው። ሰውየው ስለ ልብሱ ቢያውቅም ላለመልበስ መርጦ ነበር። የኢየሱስ ባሕርይ ፍጹምና እድፍ የለሽ ነው፤ ይህንንም “ “ያጌጠና የተጣራ ቀጭን የተልባ እግር ልብስ እንድትጐናጸፍ ለሙሽራው ሰጥቶአታል” (ራዕ. 19:8) በማለት ለእኛ ሰጥቶናል፣ “እድፍ ወይም መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር” (ኤፌ. 5:27) አይኖርባትም። ነጭ የተልባ እግር “የክርስቶስ ጽድቅ፣ የራሱ የሆነ እንከን የለሽ ባሕርይ ነው፣ ይህም በእምነት አማካይነት እርሱን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው ለሚቀበሉት ሁሉ የሚሰጥ ነው።”—ኤለን ጂ. ኋይት፣ የክርስቶስ ምሳሌያዊ ትምህርቶች፣ ገጽ 310። አዳምና ሔዋን ኃጢአት ከመሥራታቸው በፊት ለስላሳ የብርሃን ነጭ ልብስ ለብሰው ነበር፤ ኃጢአት ከሠሩ በኋላ ግን ራቁታቸውን መሆናቸውን ተገነዘቡ (ዘፍ. 3:7)። ከዚያም እግዚአብሔር በአዳምና በሔዋን የተሠሩትን የበለስ ቅጠሎች ልብስ በእንስሳት ቆዳ ልብስ ለወጠው። ልብሳቸው እንዲሠራ መስዋዕት ያስፈልግ ነበር። በተመሳሳይ መንገድ የኢየሱስን መስዋዕትነት የምንቀበለው የጽድቁን ልብስ በመቀበል ነው። “በራቁትነትና በሀፍረት ሆነው ሰማያዊውን ልብስ ከበለስ ቅጠል በተሰፋ ግልድም ለመተካት ሞከሩ። … የሰው ልጅ ያጣውን የንፅህና መጎናፀፊያ የሚተካ ምንም ነገር ራሱ መሥራት አይችልም። የበለስ ቅጠል ግልድም ያደረጉ ወይም የተንቆጠቆጠ ዓለማዊ ልብስ የለበሱ ማናቸውም ከክርስቶስና ከመላእክቱ ጋር በበጉ የሰርግ እራት ላይ መቀመጥ አይችሉም። ነገር ግን ክርስቶስ ራሱ የሰጠን መጎናፀፊያ ብቻ ነው በእግዚአብሔር ፊት መቆም እንድንችል የሚያደርገን። ክርስቶስ በንስሐ በሚጸጸትና በሚያምን ነፍስ ሁሉ ላይ የራሱ የጽድቅ ልብስ የሆነውን ይህን ልብስ ያለብሰዋል።”—ኤለን ጂ. ኋይት፣ የክርስቶስ ምሳሌያዊ ትምህርቶች፣ ገጽ 174 (በአማርኛው)። ያስቡበት፡- በየቀኑ የኢየሱስን የጽድቅ ልብስ መልበስ አለብን። ይህ በእርግጥ ምን ማለት ነው፣ እና ይህንንስ እንዴት እናደርጋለን? @SabbathSchool @TekalignSorato

ረቡዕ ግንቦት 26 Jun 3 የሚበቃ ፀጋ የኃጢአታችን ክብደት ሲሰማንና መንፈስ ቅዱስ ወደ መስቀሉ እግር እንዲመራን ስንፈቅድ፣ “እግዚአብሔር መሓሪና ይቅር ባይ ነው፥ ከቍጣ የራቀ ምሕረቱም የበዛ ነው” (መዝ. 103:8) የሚለውን ቃል በማመን እግዚአብሔር ይቅር እንዲለን ልንጠይቅ ይገባናል። ይህ ተመሳሳይ ጥቅስ የተመረጠው ሕዝቡ ካሳዘነው በኋላ በእግዚአብሔር በራሱ (ዘጸ. 34:6) ተነግሮ ነበር። ዘጸአት 34:1-10ን ያንብቡ። እዚህ ላይ ምን ወሳኝ እውነት ይገኛል? Save Notes ጌታ መሐሪና ቸር፣ ለቁጣ የዘገየና ምሕረቱ የበዛ መሆኑ ኢየሱስ በመስቀል ላይ የሞተበት ዋነኛው ምክንያት ነው። ከእግዚአብሔር ጋር ያለን ግንኙነትም እንደገና እንዲስተካከል ነው። ይህም ተግባራዊ የሚሆነው ኃጢአታችንን ለመቀበልና ለመናዘዝ ፈቃደኛ ስንሆን ነው፤ ጌታ ሆይ፣ እንደገና እዚህ ነኝ ስንል . . እና “እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ!” (ሉቃስ 18:13) ስንል ነው፣ ከመፀለያችን በፊት እንኳን በእኛና በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ለእኛ ሲሠራ የነበረው ኢየሱስ -- ክብደቱን አይቶ ከእኛ ይወስደዋል። ሸክማችን የተነሳልን በቀራንዮ ላይ ነው፤ እናም ኢየሱስ ወደ እርሱ ስንመጣ በእርግጥ በጣም ቅርብ ነው፣ እና ከዚያ በፊትም ቢሆን እንደ መልካም እረኛ ሊፈልገን በበሩ ቆሞ ያንኳኳል (ራዕይ 3:20)። እግዚአብሔርን ከሩቅ እያየን ከመስቀሉ አንራቅ። ወደ ኢየሱስ እንሩጥ እና ኃጢአታችንንና ሸክማችንን በጽድቅ እንለውጥ (ዘካ. 3:4)። ቀጣዮቹን ጥቅሶች ቀስ ብለው ያንብቡ። ስለ እግዚአብሔር ጸጋ የሚነግሩዎትን በራስዎ ቃል መልሰው ይፃፉ፡- “የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነውና፤ የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ ግን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን የዘላለም ሕይወት ነው።” (ሮሜ. 6:23)። “ “በደልም እንዲበዛ ሕግ ጭምር ገባ፤ ዳሩ ግን ኃጢአት በበዛበት፥ ኃጢአት በሞት እንደ ነገሠ፥ እንዲሁ ደግሞ ጸጋ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተነሣ በጽድቅ ምክንያት ለዘላለም ሕይወት ይነግሥ ዘንድ፥ ጸጋ ከመጠን ይልቅ በለጠ።”(ሮሜ 5:20-21)። “ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል።” (ሮሜ 5:8) @SabbathSchool @TekalignSorato

record.ogg24.17 MB

አሁን በኢትዮጵያ ሰዓት 2:30 የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት Live ፕሮግራም ይጀመራል ። ሁላችንም በሰዓቱ እንገናኝ ። @SabbathSchool @TekalignSorato

ማክሰኞ ግንቦት 25 Jun 2 እውነተኛ ንስሐ እግዚአብሔር ለአገልጋይነት እና ለየዋህነት(ማቴ. 5:5) ካቀረበው ጥሪ በተቃራኒ ዓለም የነፃነት፣ የተመኘነውን የማድረግ እና ራስን የማስተዋወቅ መልዕክቶች ሰጥታናለች። የሚገርመው፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በመጥምቁ ዮሐንስ፣ እና በኢየሱስ የተነገሩት የመጀመሪያ ቃላት ተመሳሳይ ነበሩ። ዮሐንስ “ ‘መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ!’” ብሏል (ማቴ. 3:1, 2)። ኢየሱስ “ጊዜው ተፈጸመ የእግዚአብሔርም መንግሥት ቀርባለች። ንስሐ ግቡ፥ በወንጌልም እመኑ” ብሏል። (ማርቆስ 1:14-15፣ ሉቃስ 24:46-47ን ይመልከቱ)። ኢየሱስም ሆነ ዮሐንስ የንስሐን ጥሪ የሚሰሙትን የጠሩት መንግሥተ ሰማያት ስለቀረበ ነው። ይህ መልእክት ዛሬም ለእኛም የሚጠቅም መልእክት ሊሆን ይችላል? የሐዋርያት ሥራ 3:18-19ን ያንብቡ። በመንፈሳዊ እድገት ሂደት ውስጥ ንስሐ አስፈላጊ የሆነው ለምንድነው? “የመታደስ ወራት” ምንድን ነው? Save Notes የእግዚአብሔር ቸርነት እና መልካምነት ወደ ንስሐ ይመራናል (ሮሜ. 2:4)። ንስሐ መግባት ሁለት ደረጃዎችን ያካትታል፤ (1) ለኃጢአታችን እውነተኛ ህመም፤ እና (2) ኃጢአትን ለመተው እውነተኛ ውሳኔ። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ንስሐ መግባት ሁልጊዜ ማለት ይቻላል ከይቅርታ ጋር የተያያዘ ነው። በእውነት ስንጸጸት፤ እግዚአብሔር ይቅር ይለናል። ይህን ያህል ቀላል ነው (1ኛ ዮሐንስ 1:9፣ ራዕይ 3:19)። “ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል።” 2ኛ ጴጥሮስ 3፥9)። ነፍሳችንን በግላችን ለዳግም ምጽአቱ ስናዘጋጅ፣ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነገሮችን እንድናስተካክል ጊዜ እየሰጠን ነው። ኢየሱስ መከራ ተቀብሎ ሞተ፣ እናም ተነሣ፣ ስለዚህ ንስሐ ስንገባ፣ ጸጋው በሕይወታችን ውስጥ ተአምር ሊሠራ ይችላል። አሁን ባለንበት ደህና መሆናችንን ከሚነግረን ዓለም በተቃራኒ፣ እግዚአብሔር በንስሐ እና በእምነት ወደ እርሱ እንድንመለስ ይጠይቀናል (የሐዋርያት ሥራ 20:21)፣ ራሳችንን ሙሉ በሙሉ በእጁ ውስጥ በማስቀመጥ፣ ገፀ ባህሪያችንን ወደ እርሱ መልክ ሊቀርጽና ስለ እርሱ መመስከር እንድንችል ይጠይቀናል (ዮሐንስ 15:2፣ 8)። ከዚያም ከንስሐ ጋር በሚስማማ መንገድ እናድጋለን፣ ፍሬም እናፈራለን (ማቴ. 3:8)። “መታደስን የማያስከትል ንስሐ እውነተኛ ንስሐ አይደለም። የክርስቶስ ጽድቅ ባሕሪን የሚለውጥና ፀባይን የሚቆጣጠር የሕይወት መርህ እንጂ የድብቅ ኃጢአት መሸፈኛ ካባ አይደለም።”—ኤለን ጂ. ኋይት፣ የዘመናት ምኞት፣ ገጽ 571። ንስሐ ወደ ሕይወት ይመራል (የሐዋርያት ሥራ 11:18) እና ከእግዚአብሔር ጋር ባለን ግንኙነት ለማደግ ወሳኝ ነው። በመገዛት፣ በንስሐ፣ በመጸጸት እና እግዚአብሔር እንዲገርዘን በመፍቀድ ሂደት ውስጥ፣ ለእርስዎ በጣም ፈታኝ የሆነው እርምጃ የትኛው ነው? @SabbathSchool @TekalignSorato

ሰኞ ግንቦት 24 Jun 1 የመንፈስ ቅዱስ ወቀሳ በእርሱና በሚስቱ መካከል ስላለው ርቀት ሲያስብ፣ ስህተት እንደሠራ ገብቶታል። ደግነት የጎደለው እና ጨካኝ ሆኖ ነበር፣ የሚጸጸትባቸውን አንዳንድ ነገሮች ተናግሯል። ሆኖም ቀጣዩ ሀሳቡ ትንሽም ቢሆን ይህ የሚገባት አይደለችም ወይ? የሚለው ነበር። ይህ የአስተሳሰብ ሂደት ለእርስዎ የተለመደ ይሆን? ከጸጸት ስሜት ወደ ሀሳባችን እና ድርጊታችን ትክክል ለመሆኑ ምክንያትን ማግኘት ቀላል ነው። ስህተት ስንሠራ “ይቅርታ…” ማለት ሁልጊዜ ቀላል አይደለም፣ ነገር ግን ይህ ማንኛውንም ግንኙነት እንደገና ለመገንባት ወይም ለማጠናከር በጣም አስፈላጊ ነው። በእኛ እና በእግዚአብሔር መካከል ባለው ግንኙነትም ተመሳሳይ ነው። መንፈስ ቅዱስ ብዙውን ጊዜ የፈፀምናቸውን ኃጢአቶች ያስታውሰናል። ልባችን በእነዚህ ወቀሳዎች ምክንያት ይንቀሳቀሳል፣ ነገር ግን በተወሰነ መንገድ ለምን እንደሠራን ምክንያት ለመስጠት በመሞከር ያንን ጸጥ ያለ፣ ትንሽ ድምጽ መግፋት ሊቀለን ይችላል። የመንፈስ ቅዱስ ሚናዎች አንዱ “ስለ ኃጢአት ዓለምን መውቀስ” (ዮሐንስ 16፡7-8) ነው። ይህ ከእግዚአብሔር የተቀበልነው አስደናቂ ስጦታ (ሉቃስ 11:13) ነው፣ ከእርሱ ጋር ስንጓዝ የሚፈጠረውን ክፍተት ለመሙላት እንዲህ ያሉ ወቀሳዎች እንዴት እንደሚያስፈልጉን! ሆሴዕ 6ን ያንብቡ። እግዚአብሔር ለንስሐ በሚያቀርበው ልመና ውስጥ ራሱን እንዴት እንደገለጸ እዚህ ላይ ምን ያስተውላሉ? Save Notes መንፈስ ቅዱስ እኛን ወደ ወይኑ ግንድ መልሶ በማያያዝ ሂደት ውስጥ ያለውን ሚና አስቡበት (ዮሐንስ 15:4)። “አብዛኛውን ጊዜ የምናዝነው ክፉ ሥራችን መልሶ እኛኑ የሚጎዳ ነገር ስለሚያመጣብን ነው፤ ነገር ግን ይህ ንስሐ መግባት አይደለም። ስለ ኃጢአት የሚደረግ እውነተኛ ሀዘን የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ውጤት ነው። መንፈስ ቅዱስ ልባችን ክርስቶስን በማሳዘንና ችላ በማለት የሚያሳየውን ምስጋናቢስነት በመግለፅ በትህትና ወደ መስቀሉ እንድንቀርብ ያደርገናል። እያንዳንዱ ኃጢአት ክርስቶስን ያቆስለዋል፤ . . . በእርሱ ላይ ጉዳት ስላደረሰው ኃጢአት እናዝናለን። የዚህ ዓይነቱ ሀዘን ኃጢአትን እንድንተው ያደርገናል።”— ኤለን ጂ. ኋይት፣ የዘመናት ምኞት፣ ገጽ 299. እውነቱ ግን፣ በምርጫ የሚደረግና የተወደደ ኃጢአት በእኛና በእርሱ መካከል ቆሞ እያለ ከእግዚአብሔር ጋር ባለን ግንኙነት ማደግ አንችልም። ፍጹም መሆን አንችልም፣ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ ወደ አእምሯችን ሲያመጣው ከኃጢአታችን ንስሐ መግባት እንችላለን፣ ይገባናልም (ኤፌ. 4:30)። ለመጨረሻ ጊዜ የንስሐ ተግሣጽ ወይም የንስሐ ጥሪ የሰሙት መቼ ነበር? ምን አይነት ምላሽ ሰጡ? በዚህ ሳምንት እግዚአብሔር ልብዎን እንዲያለሰልስና በቃሉ ውስጥ ያለውን ድምፅ እንዲሰሙ ጆሮዎን እንዲከፍትልዎ አሁን በጸሎት ጊዜ ያሳልፉ። @SabbathSchool @TekalignSorato

እሑድ ግንቦት 23 May 31 የሕይወት ሩጫ በጣም የተጨናነቀ ሳምንት ነበር። ከሰንበት በፊት ብዙ የሚሠራ ነገር እንዳለ ብታውቅም፣ አጣዳፊው ነገር አስፈላጊ የሆነውን ነገር የሚውጥ ይመስል ነበር፣ እና ሳታውቀው ፀሐይ ጠልቃ ነበር። ቤተሰቡ አንድ ላይ ልዩ የአርብ ምሽት ምግብና አምልኮ ተካፈሉ። ነገር ግን የሰንበት ጠዋት ሲመጣና በማለዳ ስትነቃ፣ መታጠቢያ ቤቱ ቆሽሾ ስላገኘችው ጠራረገችው። ከዚያም ትንሹ ልጇ አልጋውን በሽንቱ እንዳራሰ አየች፣ ስለዚህ አንሶላዎቹን ከሌሎች ልብሶች ጋር ወደ ማጠቢያ ማሽን ጣለችው። ለቤተሰቧ ቁርስ ስታዘጋጅ፣ ለምሳ የሚሆን ጣፋጭ ምግብ እንደሌለ ተገነዘበች እና በፍጥነት የሙዝ ዳቦ ጋገረች። ባለቤቷ ለቤተ ክርስቲያን የሚተኮስ ሸሚዝ እንደሚያስፈልገው አየች፣ ስለዚህ ተኮሰችለት፣ ከዚያም ልብሶችን አጣጠፈችና ቆሻሻዎቹን አወጣች። ከዚያም ነገሩ ነካት። ሰንበት ነው - ከሌሎቹ ሁሉ በላይ የምወደው ቀን ነው! ሆኖም ግን፣ እነዚህን ሁሉ የቤት ውስጥ ሥራዎች እየሠራሁ እነዚህ ነገሮች ከሰንበት ጣዕም(በረከት) ማለትም ወደ እግዚአብሔር ከመቅረብ እንዲያዘናጉኝ ፈቅጃለሁ። ለአፍታ፣ አእምሮዋ ድርጊቶቿ ትክክለኛ እንደነበሩ ራሷን ለማሳመን ጀመረ - እነዚህ ሁሉ መደረግ ያለባቸው ነገሮች ነበሩ። በእርግጥ ግን ነበሩ? Save Notes እንደ ማርታ “በብዙ አገልግሎት በመጨነቅ” (ሉቃስ 10:40) እንደምትሠራ ተገነዘበች፣ ነገር ግን የኢየሱስ ቃላት በአእምሮዋ ውስጥ “በብዙ ነገር ትጨነቂአለሽ ትታወኪማለሽ፥ የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው፤ ማርያምም መልካም ዕድልን መርጣለች ከእርስዋም አይወሰድባትም።” (ሉቃስ 10፥41-42) ሲል አስተጋባ። ለኢየሱስ ካላት ጥልቅ ፍቅር የተነሳ በሰንበት ብቻ ሳይሆን በየቀኑ በኢየሱስ እግር ስር ትቀመጥ ነበር። ዛሬ ጠዋት ግን ያንን አልመረጠችም። እግዚአብሔርን ትወድ ነበር፣ ሆኖም ግን ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ሰንበትን በጊዜ ውስጥ እንደ ስጦታ እንደሰጣት መርሳት ቀላል ነበር። በጸጥታ በወጥ ቤት ውስጥ ቆማ ሳለች ከዓይኖቿ እንባ ፈሰሰ። የዚህ ምሳሌ ዓላማ በሰንበት ቀን ምን ማድረግ እንዳለብን ወይም ምን ማድረግ እንደሌለብን ላይ ማተኮር አይደለም፤ ይልቁንም ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ግንኙነት የሚያዳክሙ ወይም የሚያበላሹ ነገሮችን ማስተዋል ለምን አስፈላጊ እንደሆነ ማስታወስ ነው። በልባችን ውስጥ የኃጢአትና የመለያየት ሥቃይ ሲሰማን ወደ እርሱ ስንጣራ ኢየሱስ በጣም ቅርብ ነው (መዝ. 53:2)። በደም በተሸፈኑ እጆቹ ነጭ ልብስ ይይዛል። የንስሐ እንባችንን አይቶ የቆሸሹ ልብሶቻችንን ያስወግዳል። ከዚያም ንፁህ የጽድቅ ልብሱን በዙሪያችን ሁሉ ላይ ያደርጋል። ንጽሕናው ኃጢአታችንን - ሙሉ በሙሉ እና ፍጹም በሆነ መልኩ ይሸፍናል። ልብሳችንን በደሙ ማጠብ እንችላለን (ራዕይ 7:14)። ኢሳይያስ 64:6፣ ዘካርያስ 3:4 እና ኢሳይያስ 61:10 ስለ ክርስቶስ ጽድቅ ይህን አስፈላጊ እውነት ለእኛ የሚገልጹት እንዴት ነው? እዚህ ላይ የተሰጠንን የተስፋ ቃል ሁልጊዜ አጥብቀን መያዝ ያለብን ለምንድን ነው? @SabbathSchool @TekalignSorato

ግንቦት 22 - 28 10ኛ ትምህርት May 30 - Jun 5 ንስሐ እና ይቅርታ ሰንበት ከሰዓት በኋላ ለዚህ ሳምንት ጥናት የሚከተሉትን ጥቅሶች ያንብቡ፡ ኢሳ. 61:10፤ ሆሴዕ 6፤ የሐዋርያት ሥራ 3:18-19፤ ዘጸ. 34:1-10፤ ሮሜ. 6:23፤ ማቴ. 22:1-14። የመታሰቢያ ጥቅስ፡ “ኃጢአታችንን ብንናዘዝ፣ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው” (1ኛ ዮሐንስ 1:9)። የተስፋዪቱ ምድር በሜዳው ላይ ባለው የደመና አምድ ስር ለሰፈሩት እስራኤላውያን በጣም የራቀች ትመስል ነበር። ሙሴ ከብዙ ቀናት በፊት የተራራውን ጫፍ ሸፍኖ ወደነበረው ጨለማ ወጥቶ ነበር። ወይ በረሃብ ካልሆነም በጫፉ ላይ ካለው የሚቃጠል እሳት የተነሳ መሪያችን አሁን ሞቷል ብለው አሰቡ። በመካከላቸው የተደባለቀው ሕዝብ እረፍትና ትዕግስት አጥቶ፣ ወተትና ማር ወደምታፈሰው ምድር ለመሄድ ተዘጋጅቶ ነበር። ምንም እንኳን እነዚህ ሰዎች ከጥቂት ቀናት በፊት እርሱን ለመታዘዝ ከእግዚአብሔር ጋር ቃል ኪዳን ቢገቡም፣ ሊያዩት የሚችሉትን ምስል ፈልገው ነበር። ስለዚህ፣ በአሮን ድንኳን ዙሪያ ተሰብስበው ጣዖት እንዲሰራላቸው ጠየቁት። አሮን ለራሱ ደህንነት በመፍራት በሀሳባቸው ተስማማ። በዘጸአት 32-34፣ ይህ አሳዛኝ ታሪክ እንዴት እንደቀጠለ እናነባለን። ይህ ዘገባ የዚህ ሳምንት የትምህርት ዋና ጭብጥ ስለሆነው ስለ ንስሐና ይቅር ባይነት የሚያስተምር ከቅዱሳት መጻሕፍት የተወሰደ አንድ ታሪክ ብቻ ነው። የእያንዳንዱን ቀን ትምህርት ሲያጠኑ የዚህን ሳምንት መሪ ጥቅስ ጭብጥ በአእምሮዎ ይያዙ። አዎ፣ ኃጢአት እንሠራለን፣ ነገር ግን ለመስቀሉ እና ለመዳን እቅድ ምስጋና ይግባውና ለሚናዘዝና ለሚጸጸት ኃጢአተኛ ይቅርታ አለ።  @SabbathSchool @TekalignSorato

record.ogg44.01 MB

አሁን ግብ !!