FM መረጃ
رفتن به کانال در Telegram
እንኳን ወደ FM መረጃ በደህና መጡ በቻናላችን 🌐 ፈጣን ሀገራዊ መረጃዎች 📺 🌐 ዓለም ዓቀፍ መረጃዎች 📢 🌐 ወቅታዊ ጉዳዮች ሁሉንም በአንድ ታገኛላችሁ 📣
نمایش بیشتر8 442
مشترکین
-1124 ساعت
-477 روز
-18530 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
سپتامبر '26
سپتامبر '26
+3
در 0 کانالها
اوت '26
+357
در 4 کانالها
Get PRO
ژوئیه '26
+525
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '26
+274
در 0 کانالها
Get PRO
مه '26
+234
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '26
+344
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '26
+544
در 1 کانالها
Get PRO
فوریه '26
+595
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '26
+288
در 1 کانالها
Get PRO
دسامبر '25
+10
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '25
+13
در 1 کانالها
Get PRO
اکتبر '25
+31
در 1 کانالها
Get PRO
سپتامبر '25
+501
در 7 کانالها
Get PRO
اوت '25
+917
در 4 کانالها
Get PRO
ژوئیه '25
+1 583
در 2 کانالها
Get PRO
ژوئن '25
+1 709
در 1 کانالها
Get PRO
مه '25
+356
در 5 کانالها
Get PRO
آوریل '25
+308
در 3 کانالها
Get PRO
مارس '25
+266
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '25
+295
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '25
+106
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '24
+24
در 1 کانالها
Get PRO
نوامبر '24
+21
در 2 کانالها
Get PRO
اکتبر '24
+16
در 2 کانالها
Get PRO
سپتامبر '24
+1 773
در 138 کانالها
Get PRO
اوت '24
+1 249
در 216 کانالها
Get PRO
ژوئیه '24
+1 963
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '24
+1 293
در 66 کانالها
Get PRO
مه '24
+1 615
در 49 کانالها
Get PRO
آوریل '24
+1 041
در 7 کانالها
Get PRO
مارس '24
+710
در 21 کانالها
Get PRO
فوریه '24
+743
در 32 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 16 سپتامبر | 0 | |||
| 15 سپتامبر | 0 | |||
| 14 سپتامبر | 0 | |||
| 13 سپتامبر | 0 | |||
| 12 سپتامبر | 0 | |||
| 11 سپتامبر | +1 | |||
| 10 سپتامبر | +1 | |||
| 09 سپتامبر | 0 | |||
| 08 سپتامبر | 0 | |||
| 07 سپتامبر | 0 | |||
| 06 سپتامبر | 0 | |||
| 05 سپتامبر | 0 | |||
| 04 سپتامبر | 0 | |||
| 03 سپتامبر | +1 | |||
| 02 سپتامبر | 0 | |||
| 01 سپتامبر | 0 |
پستهای کانال
የእንቁጣጣሽ ወረቀት ይዞ ሆቴል ገብቶ ባለ 240 ሺህ ብር አይፎን የሰረቀው ታዳጊ እጅ ከፈንጂ ተያዘ !
በታዲያስ አዲስ ፕሮግራም ላይ ከአዲስ አበባ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ባልደረባ ከኮማንደር ቶማስ ጋር የተደረገው ቆይታ በእውነትም ብዙ የሚያስደምሙ፣ የሚያስቁ እንዲሁም ትልቅ ማህበራዊ መልእክት ያዘሉ ክስተቶችን ይፋ አድርጓል።
የመጀመሪያውና በርካቶችን እያነጋገረ ያለው ክስተት የተፈጸመው በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 በሚገኝ አንድ ዓለም አቀፍ ሆቴል ውስጥ ነው። አንዲት ትውልደ ኢትዮጵያዊት እንግዳ ባረፈችበት ሆቴል ክፍል በር ይንኳኳል።
አንኳኪው ደግሞ የባህል ልብስ ለብሶ "የአበባዮሽ/እንቁጣጣሽ" ወረቀት የያዘ ታዳጊ ልጅ ነው። ባህሉን የምታውቀው እንግዳም በደስታ ወረቀቱን ተቀብላ ለልጁ ስጦታ የሚሆን ገንዘብ ልታመጣ ወደ ውስጠኛው ክፍል ታመራለች።
ይሁን እንጂ ልጁ የዋጋ ግምቱ ከ240 ሺህ ብር በላይ የሚያወጣውን አይፎን ፕሮ ማክስ ስልክ ጠረጴዛው ላይ ተመልክቶ በቅጽበት ይዞ ይሰወራል። ይባስ ብሎም ይሄን ውድ ስልክ መገናኛ አካባቢ በ6 ሺህ ብር ብቻ ሊሸጠው ሲደራደር በቁጥጥር ስር ውሎ ስልኩ ለባለቤቱ ተመልሷል።
ሁለተኛው አስገራሚ ክስተት ደግሞ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የተፈጸመው ነው። አንድ ሌባ 8 በጎች እና 13 ፍየሎችን (በድምሩ 21 እንስሳትን) ሰርቆ ጭኖ ሳይሆን በእግሩ እየነዳ ሲሄድ እጅ ከፍንጅ ተይዟል!
የሚገርመው ነገር ልክ የራሱ ከብቶች ይመስል ምንም አይነት ፍርሃትና ጥርጣሬ በማይፈጥር መልኩ በሙሉ Confidence ሆኖ መንገደኛውን ሁሉ "እረኛ" መስሎ እያታለለ ሲነዳቸው ነበር። ነገር ግን በፖሊስ እና በህብረተሰቡ ንቃት ወንጀሉ ሳይሳካ እጁን ሊሰጥ ችሏል።
ከእነዚህ አጋጣሚዎች እና በዋዜማው ከተከሰተ አንድ የሰው ህይወት ያለፈበት የትራፊክ አደጋ ውጪ፣ አጠቃላይ የበዓሉ ድባብ ካለፉት ዓመታት ይልቅ እጅግ ሰላማዊ ሆኖ ማለፉ ተገልጿል።
በአጠቃላይ ግን ከዚህ የበዓል ሰሞን ወሬ የምንማረው ትልቁ ቁምነገር፣ የልጆች አስተዳደግ የትምህርት ቤት ወይም የህግ አካላት ብቻ ሳይሆን የሁላችንም የወላጆች እና የማህበረሰብ የጋራ ኃላፊነት መሆኑን ነው። ልጆቻችንን በስነ-ምግባር ካላነጽናቸው ነገ ለማህበረሰቡም ራስ ምታት መሆናቸው አይቀርም።
እናንተስ በታዳጊው ድርጊት እና በወላጆች የክትትል ኃላፊነት ዙሪያ ምን ትላላችሁ? ሀሳብ አስተያየታችሁን አካፍሉን እስኪ ?
| 2 | Happy Ethiopian New Year!
እንኳን ለ2019 ዓ.ም አደረሰዎ!
መልካም አዲስ ዓመት! | 323 |
| 3 | የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከሐምሌ ወር ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ በርሜል ከ100 ዶላር በላይ አሻቅቧል። | 410 |
| 4 | የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተጣራ ትርፍ በ75.8% ማደጉን አስታወቀ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከታክስ በኋላ የሚያገኘውን የተጣራ ትርፍ በ75.8% በማሳደግ 38.71 ቢሊዮን ብር ማድረሱን ይፋ በተደረገው የኦዲት ሪፖርት ላይ ገለጸ።
በባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ አህመድ ሽዴ እና በፕሬዚዳንቱ አብይ ሳኖ የጸደቀው የኦዲት አገልግሎት ኮርፖሬሽን ሪፖርት እንደሚያሳየው፣ የተቋሙ የወለድ ገቢ በ30.7% አድጎ 132.06 ቢሊዮን ብር ደርሷል። በሌላ በኩል የባንኩ የወለድ ወጪዎች በ1.8% ብቻ አድገው 45.31 ቢሊዮን ብር መሆናቸው ተገልጿል።
በተመሳሳይ ከወለድ ውጭ ያለው ገቢ በ77.5% እድገት በማሳየት 60.52 ቢሊዮን ብር መድረሱ በሪፖርቱ ተመላክቷል። ሆኖም የሰራተኞች እና ሌሎች የሥራ ማስኬጃ ወጪዎች በእጥፍ በመጨመር 113.71 ቢሊዮን ብር መድረሳቸው ተጠቁሟል። | 461 |
| 5 | የወርቅ ማዕድን ፕሮጀክቱ ታገደ!
በለንደን የአክሲዮን ገበያ የተመዘገበው "ከፊ ጎልድ ኤንድ ኮፐር" (Kefi Gold & Copper) ኩባንያ በኦሮሚያ ክልል በሚገኘው ዋናው የቱሉ ካፒ የወርቅ ማዕድን ፕሮጀክት ላይ እየተከናወኑ የነበሩትን ሁሉንም የልማት ስራዎች ማገዱን አስታወቀ።
📌ከሦስት ቀናት በፊት በፀጥታ አካላትና በአካባቢው ማህበረሰብ መካከል በተፈጠረ የጸጥታ ችግር ምክንያት የኩባንያው ሠራተኛ ህይወት ማለፉን ተከትሎ ነው።
📌 ኩባንያው ከህብረተሰብ ተወካዮች፣ ከክልል የስራ ኃላፊዎችና ከጸጥታ አካላት ጋር በመነጋገር የደህንነት ሁኔታውን ለመገምገም ጥረት እያደረገ ይገኛል።
📌 የመስክ ስራዎችን በሰላም ለመጀመር የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እና አስተማማኝ ደህንነት እስኪፈጠር ድረስ የፕሮጀክቱ ስራዎች ሙሉ በሙሉ ተቋርጠው ይቆያሉ። | 385 |
| 6 | አባ ተስፋስላሴ የአዲስ አበባ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ በመሆን መንበራቸውን በይፋ ተረከቡ
በሮማ ካቶሊክ የቤተክርስቲያን ሕግ መሠረት በተከናወነ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓት፣ ብፁዕ አቡነ አባ ተስፋስላሴ የአዲስ አበባ ሊቀ ጳጳስ በመሆን መንበራቸውን በይፋ መረከባቸው ተገልጿል።
በስነ-ስርዓቱ ላይ አባ ተስፋስላሴ ወደ ካቴድራሉ ከመግባታቸው በፊት የካቴድራሉን በር ሶስት ጊዜ በማንኳኳት ሀገረ ስብከቱን ለመምራት ያላቸውን ይፋዊ ፍላጎት ያሳዩ ሲሆን፣ የቀድሞው ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነየሱስ የሃይማኖታዊ አገልግሎት ዘንግ እና አልባሳትን በይፋ አስረክበዋቸዋል። ከ1999 እስከ 2026 እ.ኤ.አ. ለ27 ዓመታት ያህል የአዲስ አበባ ሊቀ ጳጳስ በመሆን ያገለገሉት ካርዲናል አቡነ ብርሃነየሱስ በበላይነት የመሩት ይህ የቅዳሴ ሥነ-ሥርዓት የርክክብ ሽግግሩ በይፋ መጠናቀቁን ያበሰረ ሆኖ ተመዝግቧል። | 279 |
| 7 | የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ በኢንዶኔዥያ
የኢንዶኔዥያ ባለስልጣናት በእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ምክኒያት በስምንት አውሮፕላን ማረፊያዎች የሚሰጠውን አገልግሎት በጊዜያዊነት ለማቋረጥ መገደዳቸውን ተከትሎ፣ የ270ሺ መንገደኞች ጉዞ ተስተጓጉሏል።
የአናክ ክራካታው እሳተ ገሞራ አመድ በአውሮፕላን ማረፊያው አቅራቢያ በሚገኝ የአየር ክልል ውስጥ መታየቱን ተከትሎ፣ እሁድ ጠዋት መጀመሪያ የተዘጋው በጃካርታ የሚገኘው የሶካርኖ-ሀታ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ነው።የትራንስፖርት ሚኒስቴሩ አውሮፕላን ማረፊያዎቹ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ዝግ ሆነው እንደሚቆዩና ከ 2ሺ በላይ በረራዎች መዘግየታቸውን አስታውቋል።
እሳተ ገሞራው አርብ ምሽት ላይ መፈንዳት የጀመረ ሲሆን፣ ተከታታይነት ያለው የመሬት ንዝረት እና ከፍተኛ የፍንዳታ ድምፆችን አስከትሏል። እሁድ ማለዳ ላይ ተጨማሪ ሁለት ፍንዳታዎች መከሰታቸውን ባለስልጣናት ገልጸዋል።የበረራ አገልግሎቶች መቋረጥ በዋናነት ከሲንጋፖር እና ወደ ሲንጋፖር የሚደረጉ በረራዎችን ያስተጓጎለ ሲሆን፣ ዶሃን፣ ሲድኒን እና ኩዋላልምፑርን ጨምሮ ሌሎች ዓለም አቀፍ የበረራ መስመሮችም ተጎድተዋል ሲል የትራንስፖርት ሚኒስቴሩ አስገንዝቧል።
የትራንስፖርት ሚኒስትሩ ዱዲ ፑርዋጋንዲ ተጨማሪ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በጊዜያዊነት ለመዝጋት ውሳኔ ላይ የተደረሰው፣ የእሳተ ገሞራው አመድ ወደ ምዕራብ ጃቫ አቅጣጫ መሰራጨቱን ምርመራዎች ማረጋገጣቸውን ተከትሎ ነው ብለዋል።በረራ በመሰረዙ ምክኒያት ለተስተጓጎሉ መንገደኞች የቲኬት ገንዘብ ተመላሽ የማድረግ ሂደትን አየር መንገዶች እንዲያፋጥኑ ያሳሰቡት ሚኒስትሩ፣ በአውሮፕላን ማረፊያዎች የሰዎች መጨናነቅን ለማስቀረት አየር መንገዶች ቀጣይ በረራ ላላቸው መንገደኞች ወቅታዊ መረጃ እንዲያቀርቡም ጠይቀዋል።
የኢንዶኔዥያ የሚቲዎሮሎጂ ኤጀንሲ መረጃ እንደሚያመለክተው፣ የእሳተ ገሞራው አመድ ከእሳተ ገሞራው በስተምስራቅ በኩል በጃቫ እስከ 20ሺ ጫማ ከፍታ ላይ የደረሰ ሲሆን፣ ከእሳተ ገሞራው በስተምዕራብ በሱማትራ በኩል ደግሞ 50ሺ ጫማ ከፍታ ላይ ደርሷል።
@FM_mereja
@FM_mereja | 251 |
| 8 | بدون متن... | 299 |
| 9 | የድሮን ጥቃት‼
📌አዳሩን በሕንጣሎ ወረዳ የድሮን ጥቃት ተፈፅሟል።
በትግራይ ክልል ሕንጣሎ ወረዳ ጣብያ ፍረወይኒ «ማይ ሽመት» ልዩ ቦታ ላይ ሌሊት 8:30 ሰዓት ተደጋጋሚ የድሮን ደብደባ መፈፀሙ ታውቋል።
የድሮን ጥቃቱ ኢላማ የህውሃት የጦር መሳሪያ ክምችት ላይ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ህውሃት በበኩሉ በጥቃቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ሦስት ሰዎች (የአራት ዓመት ሕፃንን ጨምሮ) ሲሞቱ፣ የሟቾች እናት ደግሞ በጽኑ መቁሰላቸውንና በንብረት ላይም ከባድ ውድመት መድረሱ አሳውቋል።
ህውሃት መኖሪያ መንደሮችን አስታኮ የጦር መሳሪያ ስለሚያከማች በንፅሃን ላይ ጉዳት እየደረሰ ያለው ክምችቱ በድሮን ሲመታ የሚወድመው ጦር መሳሪያ ፍንዳታ ነው ሲሉ ገለልተኛ ወገኖች እየገለፁ ነው። | 369 |
| 10 | ህወሓት የቀድሞውን የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሉሴጉን ኦባሳንጆን ለአሸማጋይነት ብቁ አይደሉም ሲል ውድቅ አደረገ
በምርጫ ቦርድ ህጋዊ እውቅና የተነፈገው ህወሓት፣ የአፍሪካ ኅብረት ልዩ መልዕክተኛ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ ከፌደራል መንግስት ቀጥተኛ ትዕዛዝ የሚቀበሉ በመሆናቸው ለአሸማጋይነት ብቁ እንዳልሆኑ በትናንትናው ዕለት ማምሻውን ባወጣው ይፋዊ መግለጫ አስታውቋል።
ድርጅቱ ኦባሳንጆ ግልፅ የሆነ የሰላም አጀንዳ እንደሌላቸው እና የዓለም አቀፍ አሸማጋይነት ዋና መመሪያ የሆኑትን ነጻነት፣ ገለልተኝነት እንዲሁም ተከታታይነት ያለው ጥረት የማድረግ መስፈርቶችን እንደማያሟሉ ገልጾ፣ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት በፌደራል መንግስት ስር መውደቃቸውን በመጠቆም ለሌላ ገለልተኛ አሸማጋይ በሩ ክፍት መሆኑን አጽዕኖት ሰጥቷል። | 327 |
| 11 | ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው የሙዚቃ አልበም ሊለቁ ነው
ላለፉት ሶስት አስርት አመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ እንቅስቃሴ በማድረግ የሚታወቁት አቶ ልደቱ፤ ሀሳብን በዜማ በሚል ለአዲስ አመት የሙዚቃ አልበም ሊያሰራጩ መሆኑን ገልጸዋል።
ፖለቲከኛው አዲስ የከፈቱትን የዩቲዩብ ገጽ ይፋ ባደረጉበት ወቅት እንዳሳወቁት የሙዚቃ አልበሙን ያዘጋጁት አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን በመጠቀም ነው።
እንደሚታወሰው ቴዲ አፍሮ ኢቶሪካ አልበሙን ካሰራጨ በኋላ የፈጠረውን ተጽእኖ ተከትሎ አቶ ልደቱ በወቅቱ፣ "የመንፈስ ቅናት አደረብኝ" ሲሉ ገልጸው ነበር።
@FM_mereja
@FM_mereja | 308 |
| 12 | የኬሚካል ጦር መሳሪያ
ከሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ጋር እየተዋጋ የሚገኘውና በአርቡርሃን የሚመራው የሱዳን ጦር ኃይሎች ጥቅም ላይ የሚውሉ የኬሚካል ጦር መሳሪያዎችን እያመረቱ መሆኑ ታውቋል። | 334 |
| 13 | ቴዲ :- ፋኖ ከነ አካቴው ወለጋ ውስጥ መደራጀት የለበትም ብለህ ታምናለህ?
ጀዋር :- [ መደራጀቱ ] ይጠቅማቸዋል?
ቴዲ :- አዎ። ከፍተኛ ጥቃት ሲደርስባቸው የነበሩ የአማራ ተወላጆች አሉ። መንግስት ምላሽ ሊሰጣቸው አልቻለም። Infact በልዩ ልዩ መልክ እየጨፈጨፋቸው ነው። ስለዚህ የህልውና አደጋ ላይ ወድቀዋል። ራሳችንን መከላከል አለብን ብለው ተደራጁ። ስህተት ነው ይሄ?
ጀዋር :- እኔ አማጺ የዜጎችንን ደህንነት ያድናል ብዬ አላስብም። አይችልም ያባብሰዋል እንጂ። የፋኖዎች በወለጋ ውስጥ መንቀሳቀስ በወለጋ ውስጥ ያሉትን የአማራና የኦሮሞን ዜጎች ለመንግስት ሸርና ግድያ ያባብሳል/ያጋልጣል እንጂ ፈጽሞ ሊረዳቸው አይችልም
ቴዲ :- እዚያ አካባቢ (ወለጋ) የሚገደሉት የአማራ ተወላጆች ታዲያ ምን ምርጫ አላቸው? ዝም ብለው መሞት?
ጀዋር :- እዚያ አካባቢ የሚገደሉት የኦሮሞ ተወላጆች ታዲያ ምን ምርጫ አላቸው?
ቴዲ :- ኦላ (OLA) እንዳደረገው ራሳቸውን መከላከል ይችላሉ። OLA አለ። የቆምኩት ለኦሮሞ ህዝብ ጥያቄዎች ነው ብሏል። በአካባቢው እየተንቀሳቀሰ ነው። በፖለቲካ አመለካከታቸው ምክንያት የኦሮሞ ተወላጆች እየተገደሉ ነው። ያ የOLAን መደራጀት አላስቆመውም? የፋኖን ለምን ያስቆመዋል ልልህ ነው?
ጀዋር :- OLA እዛ ውስጥ መንቀሳቀሱ የኦሮሞን መገደል አላስቆመውም። እንደውም excuse ነው የሚሰጠው። የፋኖን እዚያ አካባቢ መንቀሳቀስ አገዛዙ ለሚወስደው ግድያ excuse ነው እንጂ የሚሰጠው በምንም መልኩ ሊያሻሽለው አይችልም።
ቴዲ :-ታዲያ OLA መኖር አልነበረበትም?
ሰባህል ኸይር ምዕመናን | 342 |
| 14 | የአሜሪካ እና ኢራን መካረር
NBC Ethiopia
። ። ። ። ። ። ። ። ። ።
የአሜሪካና ኢራን ወታደራዊ ኃይሎች በኢራን ዙሪያ ሲንቀሳቀሱ በነበሩ መርከቦች ተኩስ መክፈታቸው ተገልጿል።
ዋሽንግተን ሥስት የኢራን የነዳጅ ተሸካሚ መርከቦች ላይ ጥቃት ስትፈጽም ኢራን ደግሞ በሆርሙዝ ሰርጥ ሶስት ታንከሮችን ኢላማ ማድረጓ ተዘግቧል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ከኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኃይል(IRGC) በሁለት የአሜሪካ የባህር ኃይል መርከቦች ላይ የሚሳኤል ጥቃት ከተከፈተ በኋላ ሦስቱን የኢራን መርከቦች መምታቱን ነው ያሳወቀው። ሁለት መርከቦቻችን ላይ ጥቃት ብትሰነዝሩ የበለጠ ኢኮኖሚያዊ ወጪ በማስወጣት ሦስቱ ላይ ምላሽ እንወስዳለን ነው ያለው የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኃይል በበኩሉ በቀጠናው በሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ መርከቦች ላይ የተጠናከረ ጥቃት መወሰዱ ተዘግቧል። ዘቡ በቀጠናው ተገቢ ያልሆነ አካሄድ በዋሽንግተን እየተተገበር መሆኑን አስታውቋል።
በሀገራቱ መካከል ያለው ውጥረት ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ ተባብሶ ቀጥሏል።
ጃፓን ታይምስ | 340 |
| 15 | 🧠 ቻይና አእምሮን ከኮምፒውተር ጋር የሚያገናኝ አዲስ ቴክኖሎጂ ለገበያ እንዲቀርብ ፈቀደች
የቻይና ብሔራዊ የመድኃኒትና የሕክምና ምርቶች አስተዳደር NEO የተሰኘውን የሳንቲም ያህል መጠን ያለው አእምሮን ከኮምፒውተር ጋር የሚያገናኝ (BCI) ቴክኖሎጂ ለገበያ እንዲቀርብ ፈቃድ ሰጠ።
🔹 ዋና ዋና ነጥቦች፦
የዓለማችን የመጀመሪያው፦ በጽንግሁዋ ዩኒቨርሲቲ እና በኒውራክል ቴክኖሎጂ የተገነባው ይህ መሳሪያ፣ ከምርምር ማዕከላት ውጭ የሰዎችን የእንቅስቃሴ አቅም ለመመለስ ለገበያ እንዲቀርብ ፈቃድ ያገኘ በዓለማችን የመጀመሪያው በአእምሮ ውስጥ የሚተከል ቴክኖሎጂ ሆኗል።
ከኢሎን መስክ Neuralink ያለው ልዩነት፦ የኢሎን መስክ ኒውራሊንክ (Neuralink) አሁንም በሰው ልጅ ላይ በሚደረግ የሙከራ ደረጃ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ NEO ግን ደህንነቱን ባስቀደመ ዲዛይኑ የንግድ ፈቃድ ማግኘት ችሏል።
ደህንነቱና አሠራሩ፦ መሳሪያው የአእምሮ ክፍሎችን ጥሶ ከመግባት ይልቅ 8 ሴንሰሮቹ ከአእምሮ ውጫዊ ሽፋን (dura mater) ላይ የሚያርፉ በመሆናቸው የሕብረ-ሕዋሳት ጉዳትንና የደም መፈሰስን በእጅጉ ይቀንሳል።
ለማን ይውላል፦ በጽኑ የአንገት አጥንትና የሕብረ-ሰstandard አደጋ ምክንያት የእጅና የእግር ሽባነት ለገጠማቸው ከ18 እስከ 60 ዕድሜ ክልል ውስጥ ላሉ አዋቂዎች የተፈቀደ ሲሆን፣ በሙከራዎችም 100% ስኬት በማስመዝገብ ታካሚዎች እንደ መብላትና መጠጣት ያሉ ተግባራትን በራሳቸው እንዲያከናውኑ አስችሏቸዋል።
| 357 |
| 16 | አዲስ ተሿሚዎች‼
ብልጽግና ፓርቲ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት መሠረት በሚመሰርተው አዲስ መንግሥት ውስጥ ከ70 እስከ 80 በመቶ የሚሆነውን የከፍተኛ ኃላፊነት ቦታ ለአዲስ ተሿሚዎች ለመስጠት መወሰኑ ተሰማ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ውሳኔውን ለሚኒስትሮችና ሚኒስትር ዲኤታዎች ያሳወቁ ሲሆን፣ ነባር አመራሮች ራሳቸውን ለሌላ ተልዕኮ—በተለይም ለአምባሳደርነት ሹመት—እንዲያዘጋጁ መነገሩ ተጠቁሟል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ካቢኔያቸውን ለማዋቀር ለሳምንታት ስብሰባ ላይ ሲሆኑ፣ አሁንም የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በካቢኔው ውስጥ የሚካተቱበት እድል ሰፊ እንደሆነ ዋዜማ ሬዲዬ ዘግቧል። | 379 |
| 17 | እንዲፈቱ ተወሰነ‼
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት በሽብር ወንጀል ተጠረጥረው በእስር ላይ በሚገኙት የኢሕአፓ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ይስሓቅ ወልዳይ፣ አባል አበበ አካሉ እና ጠበቃ አበራ ንጉሥ ላይ እያንዳንዳቸው በ50 ሺህ ብር ዋስ እንዲፈቱ ብይን ሰጠ።
ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ «ሕጋዊ ፓርቲን ሽፋን በማድረግ ሥልጣንን በኃይል ለመያዝ እና አገር ለማፍረስ አደራጅተዋል» በሚል ተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ ጠይቆ የነበረ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብታቸውን ፈቅዷል።
ተጠርጣሪዎቹ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በቁጥጥር ሥር ውለው ለአንድ ወር ያህል በእስር ላይ ነበሩ። | 425 |
| 18 | ህወሃት የፌደራል መንግስትን በድሮን ጥቃት ሲከስ የአላማጣ ባለስልጣናት ደግሞ ህወሃትን ወቀሱ
ህወሃት የፌደራል መንግስት ባለስልጣናት በሲቪል መሠረተ ልማቶች ላይ ተደጋጋሚ የአየር ጥቃቶችን እየፈጸሙ ነው ሲል የከሰሰ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ የህወሃት ታጣቂዎች የህዝብ ትምህርት ቤቶችን ወደ ወታደራዊ ካምፕነት ቀይረዋል የሚሉ የአካባቢው ሪፖርቶች መውጣታቸውን ዶቼ ቬሌ ዘግቧል።
የህወሃት ቃል አቀባይ ሚካኤል አሰግዶም በድሮን እና በሚግ ተዋጊ አውሮፕላኖች የታገዘው የአየር ጥቃት በአምስት ዞኖች በሚገኙ የህዝብ ተቋማት ላይ ማረፉን የገለጹ ሲሆን፣ በሰሜን ምዕራብ ዞን ደጀን ከተማ የሚገኝ አንድ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለሁለተኛ ጊዜ ተመትቶ ሙሉ በሙሉ መውደሙን፣ እንዲሁም በእንደርታ እና በራያ አዘቦ አርሶ አደሮችና የመኖሪያ መንደሮች መመታታቸውን ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ ከአላማጣ ከተማ የተገኙ አንድ የቀድሞ የአካባቢው ባለስልጣን ለዶቼ ቬሌ በሰጡት ተቃራኒ መረጃ፣ የህወሃት ኃይሎች አራት የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ በአላማጣ የሚገኙ ስምንት ትምህርት ቤቶችን፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን እና የማዘጋጃ ቤት ህንፃዎችን በአሁኑ ወቅት ወደ ታጠቁ ወታደራዊ ይዞታነት እና መፈጠሪያነት ቀይረዋቸዋል ሲሉ ከሰዋል። | 448 |
| 19 | አሜሪካ በፈፀመችው የቦምብ ጥቃት በሰርግ ቦታ ላይ የነበሩ ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውንየኢራን ቀይ መስቀል ማህበር ገለፀ ።
የኢራን ቀይ መስቀል ማህበር እንዳስታወቀው፣ በሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል በሚገኝ የሰርግ ስነ-ሰርዓት ላይ በአሜሪካ ጥቃት ምክንያተት አራት ሰዎች (አንድ ህጻን ጨምሮ) ህይወታቸው አልፏል፤ ከ50 በላይ ሰዎችም ቆስለዋል።
ቀይ መስቀል በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባጋራው ጽሁፍ፤ "በአሜሪካ የሚሳኤል ጥቃት የቦምብ ፍንጣሪ በሆርሞዝጋን ግዛት በሲሪክ ወረዳ ኩሄስታክ ከተማ የሰርግ ዝግጅት እየተካሄደበት በነበረ የመኖሪያ ቤት ላይ አርፎ የሰዎችን ህይወት አጥፍቱዋል" ብሏል።
ማህበሩ አክሎም "ከ50 በላይ ሰዎች ቆስለዋል፤ አንድን ህጻን ጨምሮ አራት ሰዎችም ሰማዕትነት ተቀብለዋል" ሲል ገልጿል።
የኢራን የመንግስት ይፋ ያደረገው ቪዲዮ፣ በሲሪክ በሚገኘው የሰርግ ስፍራ ላይ የደረሰውን ሰፊ ፍርስራሽ እና ጉዳት የሚያሳይ ሲሆን፣ በስተጀርባም የሰዎችን ድምጽና ጩኸት ማድመጥም ተችሏል።
የአሜሪካ ባለስልጣናት እስካሁን ድረስ ስለተባለው ድርጊት መረጋገጥ የሰጡት አስተያየት የለም፤ነገር ግን ኢራን ለደረሰው ጥቃት አፀፋዊ ምላሽ እንደምትሰጥ ዝታለች፡፡
በደቡባዊቷ ሲሪክ ወረዳ የምትገኘው ስፍራ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ባለው የሆርሙዝ ወሽመጥ አቅራቢያ ትገኛለች።
| 469 |
| 20 | የኮሊደር ልማት ይቀጥላል‼️
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ በቀጣዩ ዓመት በከተማዋ የኮሪደር ልማት የሚካሄድባቸው አካባቢዎች እንደተለዩ በከተማዋ አስተዳደር የ2019 በጀት ዓመትና የቀጣይ አምስት ዓመታት ዕቅድ የግምገማ መድረክ ላይ ተናገሩ።
አዳነች የኮሪደር ልማት በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል። የወንዞችን ዳርቻ ማደስና "የወደቁ" ሠፈሮችን የማንሳት ሥራ በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውስጥ በቁጥር ተለይቶ መቀመጡን አዳነች ገልጠዋል።
አዳነች አያይዘውም፣ ያረጁ ሠፈሮችን የማደስ ሥራ ነዋሪዎችን በንጽህና እንዲኖሩ ከመደገፉ ባሻገር፤ በተደጋጋሚ የሚከሠቱ ተላላፊ በሽታዎችን ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ በቀጣዩ የኮሊደር ልማት የትኞቹ ሰፈሮች እንደሚነሱ በግልፅ አልታወቀም። | 426 |
