ch
Feedback
FM መረጃ

FM መረጃ

前往频道在 Telegram

እንኳን ወደ FM መረጃ በደህና መጡ በቻናላችን 🌐 ፈጣን ሀገራዊ መረጃዎች 📺 🌐 ዓለም ዓቀፍ መረጃዎች 📢 🌐 ወቅታዊ ጉዳዮች ሁሉንም በአንድ ታገኛላችሁ 📣

显示更多
8 438
订阅者
-1124 小时
-477 天
-18530 天
吸引订阅者
九月 '26
九月 '26
+4
在0个频道中
八月 '26
+357
在4个频道中
Get PRO
七月 '26
+525
在0个频道中
Get PRO
六月 '26
+274
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+234
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+344
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+544
在1个频道中
Get PRO
二月 '26
+595
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+288
在1个频道中
Get PRO
十二月 '25
+10
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+13
在1个频道中
Get PRO
十月 '25
+31
在1个频道中
Get PRO
九月 '25
+501
在7个频道中
Get PRO
八月 '25
+917
在4个频道中
Get PRO
七月 '25
+1 583
在2个频道中
Get PRO
六月 '25
+1 709
在1个频道中
Get PRO
五月 '25
+356
在5个频道中
Get PRO
四月 '25
+308
在3个频道中
Get PRO
三月 '25
+266
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+295
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+106
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+24
在1个频道中
Get PRO
十一月 '24
+21
在2个频道中
Get PRO
十月 '24
+16
在2个频道中
Get PRO
九月 '24
+1 773
在138个频道中
Get PRO
八月 '24
+1 249
在216个频道中
Get PRO
七月 '24
+1 963
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+1 293
在66个频道中
Get PRO
五月 '24
+1 615
在49个频道中
Get PRO
四月 '24
+1 041
在7个频道中
Get PRO
三月 '24
+710
在21个频道中
Get PRO
二月 '24
+743
在32个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
17 九月0
16 九月+1
15 九月0
14 九月0
13 九月0
12 九月0
11 九月+1
10 九月+1
09 九月0
08 九月0
07 九月0
06 九月0
05 九月0
04 九月0
03 九月+1
02 九月0
01 九月0
频道帖子
የአክሱም ዩኒቨርሲቲ የጦር ጉዳተኞችን ከግቢው በማስወጣት ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ከትምህርት ሚኒስቴር በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት በዲዲአር (ትጥቅ ማስፈታት፣ መ
የአክሱም ዩኒቨርሲቲ የጦር ጉዳተኞችን ከግቢው በማስወጣት ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ከትምህርት ሚኒስቴር በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት በዲዲአር (ትጥቅ ማስፈታት፣ መበተንና መልሶ ማቋቋም) ሂደት ከትጥቅ እንቅስቃሴ የተሰናበቱ የጦር ጉዳተኞችን ከዋናው ግቢ የማስወጣት ሥራ እያከናወነ እንደሚገኝና ሂደቱ ተማሪዎች ከመድረሳቸው በፊት ሙሉ በሙሉ እንደሚጠናቀቅ ለትምህርት ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ አመለከተ። ዩኒቨርሲቲው የመማር ማስተማር፣ የምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎት ሥራውን ሰላማዊና ደህንነቱ በተጠበቀ ሁኔታ ማከናወን እንዲችል የዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ ከማንኛውም የጦር ጉዳተኞች ነፃ እንዲሆን ሚኒስቴሩ ቀደም ሲል አቅጣጫ መስጠቱ ይታወቃል። ይህንን ተከትሎ ዩኒቨርሲቲው ከአካባቢው፣ ከዞንና ከከተማ አመራሮች ጋር በመተባበር ጉዳዩን የሚያስፈጽም ኮሚቴ አቋቁሞ እየሰራ መሆኑን ጠቅሶ፣ ወደ ግቢው ገብተው የነበሩ የጦር ጉዳተኞችም ጥያቄውን በመቀበል ለመውጣት ፈቃደኛ መሆናቸው ተገልጿል። በተጨማሪም ከዋናው ግቢ ውጭ ያሉ ሌሎች ሦስት የዩኒቨርሲቲው ግቢዎች ከዚህ ጉዳይ ጋር የተያያዘ ምንም ዓይነት ችግር የሌለባቸው መሆኑ ተጠቅሷል።

2
የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የዩኒቨርሲቲ ምደባን ይመለከታል በትምህርት ሚኒስቴር በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን ወደ መንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የመመደብ ሂደትን አጠናቋል። ምደባው ፍትሐዊነትን፣ ግልጽነትን፣ እኩል ዕድልን እና ሚዛናዊ ስርጭትን በሚያረጋግጥ መልኩ፣ የተማሪዎችን ውጤትና ምርጫ፣ የዩኒቨርሲቲዎችን የቅበላ አቅም እንዲሁም ሌሎች የምደባ መስፈርቶችን ታሳቢ በማድረግ ተከናውኗል። 1. የምደባው ዋና መስፈርቶች 1.1. የተማሪዎች አጠቃላይ ውጤት እና የዩኒቨርሲቲ ምርጫ የተማሪዎች አጠቃላይ የብሔራዊ ፈተና ውጤት የምደባው ዋና የቅደም ተከተል መስፈርት ሆኖ ተወስዷል። በዚህም መሠረት ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች በምርጫቸው መሠረት የመመደብ ቅድሚያ እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን በተቻለ መጠን ከመረጧቸው የመጀመሪያ ሦስት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲመደቡ ተደርጓል። 1.2. የዩኒቨርስቲዎች የተማሪ ቅበላ አቅም የእያንዳንዱ ዩኒቨርስቲ የተማሪ ቅበላ አቅም በምደባው ሂደት ታሳቢ ተደርጓል። በመሆኑም የተማሪው ውጤትና ምርጫ ከዩኒቨርስቲዎች የቅበላ አቅም ጋር በማጣጣም ምደባው ተከናውኗል። 1.3. የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ እና የትምህርት ቤት ስርጭት በዩኒቨርሲቲዎቻችን ብዝሃነትን ለማጠናከር እና የተማሪዎችን ሚዛናዊ ስርጭት ለማረጋገጥ፦ • 70 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች ከተማሩበት ክልል ወይም ዞን ውጭ ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲመደቡ፤ • 30 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች ደግሞ በተማሩበት ክልል ወይም ዞን ውስጥ ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲመደቡ  ተደርጓል። በተጨማሪም የዞን፣ የወረዳ እና የትምህርት ቤት ስርጭት በምደባው ሂደት ታሳቢ ተደርጓል። 1.4. የፆታ ሚዛን በዩኒቨርሲቲዎች የሴትና የወንድ ተማሪዎች ስብጥር ሚዛናዊ እንዲሆን በምደባው ሂደት ታሳቢ ተደርጓል። 2. ልዩ ምደባ 2.1. የዓይነ ስውራን እና የመስማት ችግር ያለባቸው ተማሪዎች የዓይነ ስውራን እና የመስማት ችግር ያለባቸው ተማሪዎች አስፈላጊውን የትምህርትና የድጋፍ አገልግሎት ሊያገኙ በሚችሉባቸው ዩኒቨርሲቲዎች እንዲመደቡ ተደርጓል። 2.2. 500 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ600 ነጥብ 500 እና ከዚያ በላይ አጠቃላይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች፣ ላስመዘገቡት የላቀ የአካዳሚክ ውጤት ልዩ ታሳቢነት በመስጠት፣ በመጀመሪያ ምርጫቸው ተመድበዋል። ይህ ልዩ የምደባ አሠራር ተማሪዎቹ በብሔራዊ ፈተናው ላስመዘገቡት የላቀ ውጤት ዕውቅና ለመስጠት እና ከፍተኛ አፈጻጸምን ለማበረታታት የተደረገ ነው። 3. የምደባ ውጤትን ስለመመልከት ተማሪዎች የተመደቡበትን ዩኒቨርስቲ ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው የኦንላይን ሥርዓት በመጠቀም ማየት ይችላሉ። የተመደቡበትን ዩኒቨርስቲ  ለማየት ማስፈንጠሪያ፦ https://student.ethernet.edu.et/view-placement 4. ቅሬታ ስለማቅረብ በምደባው ቅሬታ ያላቸው ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለዚሁ ሲባል በተዘጋጀው የኦንላይን ሥርዓት ብቻ ይህ ምደባ ይፋ ከሆነበት ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ አስፈላጊውን መረጃና ማስረጃ በማያያዝ እንዲያቀርቡ እናሳስባለን። የቅሬታ ማቅረቢያ ማስፈንጠሪያ፦ https://student.ethernet.edu.et/complaints • በአካል ወደ ትምህርት ሚኒስቴር በመምጣት የሚቀርብ የምደባ ቅሬታ የማይስተናገድ መሆኑን ተማሪዎችና ወላጆች እንዲገነዘቡ እናሳውቃለን። 5. ማሳሰቢያ ቅሬታ በሚቀርብበት ወቅት የሐሰት መረጃ፣ የተሳሳተ ማስረጃ ወይም የተጭበረበረ ሰነድ ማቅረብ በፍጹም የተከለከለ ነው። በቅሬታ ሂደት የሚቀርቡ መረጃዎችና ሰነዶች ትክክለኛነት የሚረጋገጥ ሲሆን፣ የሐሰት መረጃ ወይም ሰነድ አቅርበው የተገኙ ተማሪዎች ምደባቸው ሊሰረዝ ይችላል። በመሆኑም ሁሉም ተማሪዎች ቅሬታቸውን በእውነተኛና በተረጋገጠ መረጃ ላይ ብቻ በመመሥረት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ እንዲያቀርቡ እናሳስባለን። የትምህርት ሚኒስቴር በ2018 ዓ.ም ወደ መንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ለተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ እያለ፣ በቀጣዩ የከፍተኛ ትምህርት ጉዟችሁ ስኬታማ እንድትሆኑ መልካም ምኞቱን ይገልጻል። የትምህርት ሚኒስቴር @FM_mereja @FM_mereja
176
3
没有文字...
178
4
የእንቁጣጣሽ ወረቀት ይዞ ሆቴል ገብቶ ባለ 240 ሺህ ብር አይፎን የሰረቀው ታዳጊ እጅ ከፈንጂ ተያዘ ! በታዲያስ አዲስ ፕሮግራም ላይ ከአዲስ አበባ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ባልደረባ ከኮማንደር ቶማስ ጋር የተደረገው ቆይታ በእውነትም ብዙ የሚያስደምሙ፣ የሚያስቁ እንዲሁም ትልቅ ማህበራዊ መልእክት ያዘሉ ክስተቶችን ይፋ አድርጓል። የመጀመሪያውና በርካቶችን እያነጋገረ ያለው ክስተት የተፈጸመው በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 በሚገኝ አንድ ዓለም አቀፍ ሆቴል ውስጥ ነው። አንዲት ትውልደ ኢትዮጵያዊት እንግዳ ባረፈችበት ሆቴል ክፍል በር ይንኳኳል። አንኳኪው ደግሞ የባህል ልብስ ለብሶ "የአበባዮሽ/እንቁጣጣሽ" ወረቀት የያዘ ታዳጊ ልጅ ነው። ባህሉን የምታውቀው እንግዳም በደስታ ወረቀቱን ተቀብላ ለልጁ ስጦታ የሚሆን ገንዘብ ልታመጣ ወደ ውስጠኛው ክፍል ታመራለች። ይሁን እንጂ ልጁ የዋጋ ግምቱ ከ240 ሺህ ብር በላይ የሚያወጣውን አይፎን ፕሮ ማክስ ስልክ ጠረጴዛው ላይ ተመልክቶ በቅጽበት ይዞ ይሰወራል። ይባስ ብሎም ይሄን ውድ ስልክ መገናኛ አካባቢ በ6 ሺህ ብር ብቻ ሊሸጠው ሲደራደር በቁጥጥር ስር ውሎ ስልኩ ለባለቤቱ ተመልሷል። ሁለተኛው አስገራሚ ክስተት ደግሞ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የተፈጸመው ነው። አንድ ሌባ 8 በጎች እና 13 ፍየሎችን (በድምሩ 21 እንስሳትን) ሰርቆ ጭኖ ሳይሆን በእግሩ እየነዳ ሲሄድ እጅ ከፍንጅ ተይዟል! የሚገርመው ነገር ልክ የራሱ ከብቶች ይመስል ምንም አይነት ፍርሃትና ጥርጣሬ በማይፈጥር መልኩ በሙሉ Confidence ሆኖ መንገደኛውን ሁሉ "እረኛ" መስሎ እያታለለ ሲነዳቸው ነበር። ነገር ግን በፖሊስ እና በህብረተሰቡ ንቃት ወንጀሉ ሳይሳካ እጁን ሊሰጥ ችሏል። ከእነዚህ አጋጣሚዎች እና በዋዜማው ከተከሰተ አንድ የሰው ህይወት ያለፈበት የትራፊክ አደጋ ውጪ፣ አጠቃላይ የበዓሉ ድባብ ካለፉት ዓመታት ይልቅ እጅግ ሰላማዊ ሆኖ ማለፉ ተገልጿል። በአጠቃላይ ግን ከዚህ የበዓል ሰሞን ወሬ የምንማረው ትልቁ ቁምነገር፣ የልጆች አስተዳደግ የትምህርት ቤት ወይም የህግ አካላት ብቻ ሳይሆን የሁላችንም የወላጆች እና የማህበረሰብ የጋራ ኃላፊነት መሆኑን ነው። ልጆቻችንን በስነ-ምግባር ካላነጽናቸው ነገ ለማህበረሰቡም ራስ ምታት መሆናቸው አይቀርም።  እናንተስ በታዳጊው ድርጊት እና በወላጆች የክትትል ኃላፊነት ዙሪያ ምን ትላላችሁ? ሀሳብ አስተያየታችሁን አካፍሉን እስኪ ?  
299
5
Happy Ethiopian New Year! እንኳን ለ2019 ዓ.ም አደረሰዎ! መልካም አዲስ ዓመት!
Happy Ethiopian New Year! እንኳን ለ2019 ዓ.ም አደረሰዎ! መልካም አዲስ ዓመት!
409
6
የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከሐምሌ ወር ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ በርሜል ከ100 ዶላር በላይ አሻቅቧል።
የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከሐምሌ ወር ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ በርሜል ከ100 ዶላር በላይ አሻቅቧል።
466
7
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተጣራ ትርፍ በ75.8% ማደጉን አስታወቀ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከታክስ በኋላ የሚያገኘውን የተጣራ ትርፍ በ75.8% በማሳደግ 38.71 ቢሊዮን ብ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተጣራ ትርፍ በ75.8% ማደጉን አስታወቀ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከታክስ በኋላ የሚያገኘውን የተጣራ ትርፍ በ75.8% በማሳደግ 38.71 ቢሊዮን ብር ማድረሱን ይፋ በተደረገው የኦዲት ሪፖርት ላይ ገለጸ። በባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ አህመድ ሽዴ እና በፕሬዚዳንቱ አብይ ሳኖ የጸደቀው የኦዲት አገልግሎት ኮርፖሬሽን ሪፖርት እንደሚያሳየው፣ የተቋሙ የወለድ ገቢ በ30.7% አድጎ 132.06 ቢሊዮን ብር ደርሷል። በሌላ በኩል የባንኩ የወለድ ወጪዎች በ1.8% ብቻ አድገው 45.31 ቢሊዮን ብር መሆናቸው ተገልጿል። በተመሳሳይ ከወለድ ውጭ ያለው ገቢ በ77.5% እድገት በማሳየት 60.52 ቢሊዮን ብር መድረሱ በሪፖርቱ ተመላክቷል። ሆኖም የሰራተኞች እና ሌሎች የሥራ ማስኬጃ ወጪዎች በእጥፍ በመጨመር 113.71 ቢሊዮን ብር መድረሳቸው ተጠቁሟል።
514
8
የወርቅ ማዕድን ፕሮጀክቱ ታገደ! በለንደን የአክሲዮን ገበያ የተመዘገበው "ከፊ ጎልድ ኤንድ ኮፐር" (Kefi Gold & Copper) ኩባንያ በኦሮሚያ ክልል በሚገኘው ዋናው የቱሉ ካፒ የወርቅ ማዕድን
የወርቅ ማዕድን ፕሮጀክቱ ታገደ! በለንደን የአክሲዮን ገበያ የተመዘገበው "ከፊ ጎልድ ኤንድ ኮፐር" (Kefi Gold & Copper) ኩባንያ በኦሮሚያ ክልል በሚገኘው ዋናው የቱሉ ካፒ የወርቅ ማዕድን ፕሮጀክት ላይ እየተከናወኑ የነበሩትን ሁሉንም የልማት ስራዎች ማገዱን አስታወቀ። 📌ከሦስት ቀናት በፊት በፀጥታ አካላትና በአካባቢው ማህበረሰብ መካከል በተፈጠረ የጸጥታ ችግር ምክንያት የኩባንያው ሠራተኛ ህይወት ማለፉን ተከትሎ ነው። 📌 ኩባንያው ከህብረተሰብ ተወካዮች፣ ከክልል የስራ ኃላፊዎችና ከጸጥታ አካላት ጋር በመነጋገር የደህንነት ሁኔታውን ለመገምገም ጥረት እያደረገ ይገኛል። 📌 የመስክ ስራዎችን በሰላም ለመጀመር የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እና አስተማማኝ ደህንነት እስኪፈጠር ድረስ የፕሮጀክቱ ስራዎች ሙሉ በሙሉ ተቋርጠው ይቆያሉ።
428
9
አባ ተስፋስላሴ የአዲስ አበባ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ በመሆን መንበራቸውን በይፋ ተረከቡ በሮማ ካቶሊክ የቤተክርስቲያን ሕግ መሠረት በተከናወነ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓት፣ ብፁዕ አቡነ አባ
አባ ተስፋስላሴ የአዲስ አበባ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ በመሆን መንበራቸውን በይፋ ተረከቡ በሮማ ካቶሊክ የቤተክርስቲያን ሕግ መሠረት በተከናወነ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓት፣ ብፁዕ አቡነ አባ ተስፋስላሴ የአዲስ አበባ ሊቀ ጳጳስ በመሆን መንበራቸውን በይፋ መረከባቸው ተገልጿል። በስነ-ስርዓቱ ላይ አባ ተስፋስላሴ ወደ ካቴድራሉ ከመግባታቸው በፊት የካቴድራሉን በር ሶስት ጊዜ በማንኳኳት ሀገረ ስብከቱን ለመምራት ያላቸውን ይፋዊ ፍላጎት ያሳዩ ሲሆን፣ የቀድሞው ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነየሱስ የሃይማኖታዊ አገልግሎት ዘንግ እና አልባሳትን በይፋ አስረክበዋቸዋል። ከ1999 እስከ 2026 እ.ኤ.አ. ለ27 ዓመታት ያህል የአዲስ አበባ ሊቀ ጳጳስ በመሆን ያገለገሉት ካርዲናል አቡነ ብርሃነየሱስ በበላይነት የመሩት ይህ የቅዳሴ ሥነ-ሥርዓት የርክክብ ሽግግሩ በይፋ መጠናቀቁን ያበሰረ  ሆኖ ተመዝግቧል።
320
10
የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ  በኢንዶኔዥያ የኢንዶኔዥያ ባለስልጣናት በእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ምክኒያት በስምንት አውሮፕላን ማረፊያዎች የሚሰጠውን አገልግሎት በጊዜያዊነት ለማቋረጥ መገደዳቸውን ተከትሎ፣ የ270ሺ መንገደኞች ጉዞ ተስተጓጉሏል። የአናክ ክራካታው እሳተ ገሞራ አመድ በአውሮፕላን ማረፊያው አቅራቢያ በሚገኝ የአየር ክልል ውስጥ መታየቱን ተከትሎ፣ እሁድ ጠዋት መጀመሪያ የተዘጋው በጃካርታ የሚገኘው የሶካርኖ-ሀታ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ነው።የትራንስፖርት ሚኒስቴሩ አውሮፕላን ማረፊያዎቹ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ዝግ ሆነው እንደሚቆዩና ከ 2ሺ በላይ በረራዎች መዘግየታቸውን አስታውቋል። እሳተ ገሞራው አርብ ምሽት ላይ መፈንዳት የጀመረ ሲሆን፣ ተከታታይነት ያለው የመሬት ንዝረት እና ከፍተኛ የፍንዳታ ድምፆችን አስከትሏል። እሁድ ማለዳ ላይ ተጨማሪ ሁለት ፍንዳታዎች መከሰታቸውን ባለስልጣናት ገልጸዋል።የበረራ አገልግሎቶች መቋረጥ በዋናነት ከሲንጋፖር እና ወደ ሲንጋፖር የሚደረጉ በረራዎችን ያስተጓጎለ ሲሆን፣ ዶሃን፣ ሲድኒን እና ኩዋላልምፑርን ጨምሮ ሌሎች ዓለም አቀፍ የበረራ መስመሮችም ተጎድተዋል ሲል የትራንስፖርት ሚኒስቴሩ አስገንዝቧል። የትራንስፖርት ሚኒስትሩ ዱዲ ፑርዋጋንዲ ተጨማሪ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በጊዜያዊነት ለመዝጋት ውሳኔ ላይ የተደረሰው፣ የእሳተ ገሞራው አመድ ወደ ምዕራብ ጃቫ አቅጣጫ መሰራጨቱን ምርመራዎች ማረጋገጣቸውን ተከትሎ ነው ብለዋል።በረራ በመሰረዙ ምክኒያት ለተስተጓጎሉ መንገደኞች የቲኬት ገንዘብ ተመላሽ የማድረግ ሂደትን አየር መንገዶች እንዲያፋጥኑ ያሳሰቡት ሚኒስትሩ፣ በአውሮፕላን ማረፊያዎች የሰዎች መጨናነቅን ለማስቀረት አየር መንገዶች ቀጣይ በረራ ላላቸው መንገደኞች ወቅታዊ መረጃ እንዲያቀርቡም ጠይቀዋል። የኢንዶኔዥያ የሚቲዎሮሎጂ ኤጀንሲ መረጃ እንደሚያመለክተው፣ የእሳተ ገሞራው አመድ ከእሳተ ገሞራው በስተምስራቅ በኩል በጃቫ እስከ 20ሺ ጫማ ከፍታ ላይ የደረሰ ሲሆን፣ ከእሳተ ገሞራው በስተምዕራብ በሱማትራ በኩል ደግሞ 50ሺ ጫማ ከፍታ ላይ ደርሷል። @FM_mereja @FM_mereja
305
11
没有文字...
318
12
የድሮን ጥቃት‼ 📌አዳሩን በሕንጣሎ ወረዳ የድሮን ጥቃት ተፈፅሟል። በትግራይ ክልል ሕንጣሎ ወረዳ ጣብያ ፍረወይኒ «ማይ ሽመት» ልዩ ቦታ ላይ ሌሊት 8:30 ሰዓት ተደጋጋሚ የድሮን ደብደባ መፈፀሙ ታ
የድሮን ጥቃት‼ 📌አዳሩን በሕንጣሎ ወረዳ የድሮን ጥቃት ተፈፅሟል። በትግራይ ክልል ሕንጣሎ ወረዳ ጣብያ ፍረወይኒ «ማይ ሽመት» ልዩ ቦታ ላይ  ሌሊት 8:30 ሰዓት ተደጋጋሚ የድሮን ደብደባ መፈፀሙ ታውቋል። የድሮን ጥቃቱ ኢላማ የህውሃት የጦር መሳሪያ ክምችት ላይ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ህውሃት በበኩሉ በጥቃቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ሦስት ሰዎች (የአራት ዓመት ሕፃንን ጨምሮ) ሲሞቱ፣ የሟቾች እናት ደግሞ በጽኑ መቁሰላቸውንና በንብረት ላይም ከባድ ውድመት መድረሱ አሳውቋል። ህውሃት መኖሪያ መንደሮችን አስታኮ የጦር መሳሪያ ስለሚያከማች በንፅሃን ላይ ጉዳት እየደረሰ ያለው ክምችቱ በድሮን ሲመታ የሚወድመው ጦር መሳሪያ ፍንዳታ ነው ሲሉ ገለልተኛ ወገኖች እየገለፁ ነው።
392
13
ህወሓት የቀድሞውን የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሉሴጉን ኦባሳንጆን ለአሸማጋይነት ብቁ አይደሉም ሲል ውድቅ አደረገ በምርጫ ቦርድ ህጋዊ እውቅና የተነፈገው ህወሓት፣ የአፍሪካ ኅብረት ልዩ መልዕክተኛ ኦሉሴጉ
ህወሓት የቀድሞውን የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሉሴጉን ኦባሳንጆን ለአሸማጋይነት ብቁ አይደሉም ሲል ውድቅ አደረገ በምርጫ ቦርድ ህጋዊ እውቅና የተነፈገው ህወሓት፣ የአፍሪካ ኅብረት ልዩ መልዕክተኛ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ ከፌደራል መንግስት ቀጥተኛ ትዕዛዝ የሚቀበሉ በመሆናቸው ለአሸማጋይነት ብቁ እንዳልሆኑ በትናንትናው ዕለት ማምሻውን ባወጣው ይፋዊ መግለጫ አስታውቋል። ድርጅቱ ኦባሳንጆ ግልፅ የሆነ የሰላም አጀንዳ እንደሌላቸው እና የዓለም አቀፍ አሸማጋይነት ዋና መመሪያ የሆኑትን ነጻነት፣ ገለልተኝነት እንዲሁም ተከታታይነት ያለው ጥረት የማድረግ መስፈርቶችን እንደማያሟሉ ገልጾ፣ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት በፌደራል መንግስት ስር መውደቃቸውን በመጠቆም ለሌላ ገለልተኛ አሸማጋይ በሩ ክፍት መሆኑን አጽዕኖት ሰጥቷል።
344
14
ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው የሙዚቃ አልበም ሊለቁ ነው ላለፉት ሶስት አስርት አመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ እንቅስቃሴ በማድረግ የሚታወቁት አቶ ልደቱ፤ ሀሳብን በዜማ በሚል ለአዲስ አመት የሙዚቃ
ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው የሙዚቃ አልበም ሊለቁ ነው ላለፉት ሶስት አስርት አመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ እንቅስቃሴ በማድረግ የሚታወቁት አቶ ልደቱ፤ ሀሳብን በዜማ በሚል ለአዲስ አመት የሙዚቃ አልበም ሊያሰራጩ መሆኑን ገልጸዋል። ፖለቲከኛው አዲስ የከፈቱትን የዩቲዩብ ገጽ ይፋ ባደረጉበት ወቅት እንዳሳወቁት የሙዚቃ አልበሙን ያዘጋጁት አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን በመጠቀም ነው። እንደሚታወሰው ቴዲ አፍሮ ኢቶሪካ አልበሙን ካሰራጨ በኋላ የፈጠረውን ተጽእኖ ተከትሎ አቶ ልደቱ በወቅቱ፣ "የመንፈስ ቅናት አደረብኝ" ሲሉ ገልጸው ነበር። @FM_mereja @FM_mereja
325
15
የኬሚካል ጦር መሳሪያ ከሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ጋር እየተዋጋ የሚገኘውና በአርቡርሃን የሚመራው የሱዳን ጦር ኃይሎች ጥቅም ላይ የሚውሉ የኬሚካል ጦር መሳሪያዎችን እያመረቱ መሆኑ ታውቋል።
የኬሚካል ጦር መሳሪያ ከሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ጋር እየተዋጋ የሚገኘውና በአርቡርሃን የሚመራው የሱዳን ጦር ኃይሎች ጥቅም ላይ የሚውሉ የኬሚካል ጦር መሳሪያዎችን እያመረቱ መሆኑ ታውቋል።
358
16
ቴዲ :- ፋኖ ከነ አካቴው ወለጋ ውስጥ መደራጀት የለበትም ብለህ ታምናለህ? ጀዋር :- [ መደራጀቱ ] ይጠቅማቸዋል? ቴዲ :- አዎ። ከፍተኛ ጥቃት ሲደርስባቸው የነበሩ የአማራ ተወላጆች አሉ። መንግስ
ቴዲ :- ፋኖ ከነ አካቴው ወለጋ ውስጥ መደራጀት የለበትም ብለህ ታምናለህ? ጀዋር :- [ መደራጀቱ ] ይጠቅማቸዋል? ቴዲ :- አዎ። ከፍተኛ ጥቃት ሲደርስባቸው የነበሩ የአማራ ተወላጆች አሉ። መንግስት ምላሽ ሊሰጣቸው አልቻለም። Infact በልዩ ልዩ መልክ እየጨፈጨፋቸው ነው። ስለዚህ የህልውና አደጋ ላይ ወድቀዋል። ራሳችንን መከላከል አለብን ብለው ተደራጁ። ስህተት ነው ይሄ? ጀዋር :- እኔ አማጺ የዜጎችንን ደህንነት ያድናል ብዬ አላስብም። አይችልም ያባብሰዋል እንጂ። የፋኖዎች በወለጋ ውስጥ መንቀሳቀስ በወለጋ ውስጥ ያሉትን የአማራና የኦሮሞን ዜጎች ለመንግስት ሸርና ግድያ ያባብሳል/ያጋልጣል እንጂ ፈጽሞ ሊረዳቸው አይችልም ቴዲ :- እዚያ አካባቢ (ወለጋ) የሚገደሉት የአማራ ተወላጆች ታዲያ ምን ምርጫ አላቸው? ዝም ብለው መሞት? ጀዋር :- እዚያ አካባቢ የሚገደሉት የኦሮሞ ተወላጆች ታዲያ ምን ምርጫ አላቸው? ቴዲ :- ኦላ (OLA) እንዳደረገው ራሳቸውን መከላከል ይችላሉ። OLA አለ። የቆምኩት ለኦሮሞ ህዝብ ጥያቄዎች ነው ብሏል። በአካባቢው እየተንቀሳቀሰ ነው። በፖለቲካ አመለካከታቸው ምክንያት የኦሮሞ ተወላጆች እየተገደሉ ነው። ያ የOLAን መደራጀት አላስቆመውም? የፋኖን ለምን ያስቆመዋል ልልህ ነው? ጀዋር :- OLA እዛ ውስጥ መንቀሳቀሱ የኦሮሞን መገደል አላስቆመውም። እንደውም excuse ነው የሚሰጠው። የፋኖን እዚያ አካባቢ መንቀሳቀስ አገዛዙ ለሚወስደው ግድያ excuse ነው እንጂ የሚሰጠው በምንም መልኩ ሊያሻሽለው አይችልም። ቴዲ :-ታዲያ OLA መኖር አልነበረበትም? ሰባህል ኸይር ምዕመናን
353
17
የአሜሪካ እና ኢራን መካረር NBC Ethiopia ። ። ። ። ። ። ። ። ። ። የአሜሪካና ኢራን ወታደራዊ ኃይሎች በኢራን ዙሪያ ሲንቀሳቀሱ በነበሩ መርከቦች ተኩስ መክፈታቸው ተገልጿል። ዋሽንግተን
የአሜሪካ እና ኢራን መካረር NBC Ethiopia ። ። ። ። ። ። ። ። ። ። የአሜሪካና ኢራን ወታደራዊ ኃይሎች በኢራን ዙሪያ ሲንቀሳቀሱ በነበሩ መርከቦች ተኩስ መክፈታቸው ተገልጿል። ዋሽንግተን ሥስት የኢራን የነዳጅ ተሸካሚ መርከቦች ላይ ጥቃት ስትፈጽም ኢራን  ደግሞ በሆርሙዝ ሰርጥ  ሶስት ታንከሮችን ኢላማ ማድረጓ ተዘግቧል። የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ከኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኃይል(IRGC) በሁለት የአሜሪካ የባህር ኃይል መርከቦች ላይ የሚሳኤል ጥቃት ከተከፈተ በኋላ ሦስቱን የኢራን መርከቦች መምታቱን ነው ያሳወቀው።  ሁለት መርከቦቻችን ላይ ጥቃት ብትሰነዝሩ የበለጠ ኢኮኖሚያዊ ወጪ በማስወጣት ሦስቱ ላይ ምላሽ እንወስዳለን ነው ያለው የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ። የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኃይል በበኩሉ በቀጠናው  በሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ መርከቦች ላይ የተጠናከረ ጥቃት መወሰዱ ተዘግቧል። ዘቡ በቀጠናው ተገቢ ያልሆነ አካሄድ በዋሽንግተን እየተተገበር መሆኑን አስታውቋል። በሀገራቱ መካከል ያለው ውጥረት ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ ተባብሶ ቀጥሏል። ጃፓን ታይምስ
351
18
🧠 ቻይና አእምሮን ከኮምፒውተር ጋር የሚያገናኝ አዲስ ቴክኖሎጂ ለገበያ እንዲቀርብ ፈቀደች ​የቻይና ብሔራዊ የመድኃኒትና የሕክምና ምርቶች አስተዳደር NEO የተሰኘውን የሳንቲም ያህል መጠን ያለው አ
🧠 ቻይና አእምሮን ከኮምፒውተር ጋር የሚያገናኝ አዲስ ቴክኖሎጂ ለገበያ እንዲቀርብ ፈቀደች ​የቻይና ብሔራዊ የመድኃኒትና የሕክምና ምርቶች አስተዳደር NEO የተሰኘውን የሳንቲም ያህል መጠን ያለው አእምሮን ከኮምፒውተር ጋር የሚያገናኝ (BCI) ቴክኖሎጂ ለገበያ እንዲቀርብ ፈቃድ ሰጠ። ​🔹 ዋና ዋና ነጥቦች፦ ​የዓለማችን የመጀመሪያው፦ በጽንግሁዋ ዩኒቨርሲቲ እና በኒውራክል ቴክኖሎጂ የተገነባው ይህ መሳሪያ፣ ከምርምር ማዕከላት ውጭ የሰዎችን የእንቅስቃሴ አቅም ለመመለስ ለገበያ እንዲቀርብ ፈቃድ ያገኘ በዓለማችን የመጀመሪያው በአእምሮ ውስጥ የሚተከል ቴክኖሎጂ ሆኗል። ​ከኢሎን መስክ Neuralink ያለው ልዩነት፦ የኢሎን መስክ ኒውራሊንክ (Neuralink) አሁንም በሰው ልጅ ላይ በሚደረግ የሙከራ ደረጃ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ NEO ግን ደህንነቱን ባስቀደመ ዲዛይኑ የንግድ ፈቃድ ማግኘት ችሏል። ​ደህንነቱና አሠራሩ፦ መሳሪያው የአእምሮ ክፍሎችን ጥሶ ከመግባት ይልቅ 8 ሴንሰሮቹ ከአእምሮ ውጫዊ ሽፋን (dura mater) ላይ የሚያርፉ በመሆናቸው የሕብረ-ሕዋሳት ጉዳትንና የደም መፈሰስን በእጅጉ ይቀንሳል። ​ለማን ይውላል፦ በጽኑ የአንገት አጥንትና የሕብረ-ሰstandard አደጋ ምክንያት የእጅና የእግር ሽባነት ለገጠማቸው ከ18 እስከ 60 ዕድሜ ክልል ውስጥ ላሉ አዋቂዎች የተፈቀደ ሲሆን፣ በሙከራዎችም 100% ስኬት በማስመዝገብ ታካሚዎች እንደ መብላትና መጠጣት ያሉ ተግባራትን በራሳቸው እንዲያከናውኑ አስችሏቸዋል። ​
365
19
አዲስ ተሿሚዎች‼ ብልጽግና ፓርቲ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት መሠረት በሚመሰርተው አዲስ መንግሥት ውስጥ ከ70 እስከ 80 በመቶ የሚሆነውን የከፍተኛ ኃላፊነት ቦታ ለአዲስ ተሿሚዎች ለመስጠት መወሰ
አዲስ ተሿሚዎች‼ ብልጽግና ፓርቲ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት መሠረት በሚመሰርተው አዲስ መንግሥት ውስጥ ከ70 እስከ 80 በመቶ የሚሆነውን የከፍተኛ ኃላፊነት ቦታ ለአዲስ ተሿሚዎች ለመስጠት መወሰኑ ተሰማ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ውሳኔውን ለሚኒስትሮችና ሚኒስትር ዲኤታዎች ያሳወቁ ሲሆን፣ ነባር አመራሮች ራሳቸውን ለሌላ ተልዕኮ—በተለይም ለአምባሳደርነት ሹመት—እንዲያዘጋጁ መነገሩ ተጠቁሟል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ካቢኔያቸውን ለማዋቀር ለሳምንታት ስብሰባ ላይ ሲሆኑ፣ አሁንም የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በካቢኔው ውስጥ የሚካተቱበት እድል ሰፊ እንደሆነ ዋዜማ ሬዲዬ ዘግቧል።
387
20
እንዲፈቱ ተወሰነ‼ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት በሽብር ወንጀል ተጠረጥረው በእስር ላይ በሚገኙት የኢሕአፓ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ይስሓቅ ወልዳይ፣ አባል አበበ አካ
እንዲፈቱ ተወሰነ‼ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት በሽብር ወንጀል ተጠረጥረው በእስር ላይ በሚገኙት የኢሕአፓ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ይስሓቅ ወልዳይ፣ አባል አበበ አካሉ እና ጠበቃ አበራ ንጉሥ ላይ እያንዳንዳቸው በ50 ሺህ ብር ዋስ እንዲፈቱ ብይን ሰጠ። ​ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ «ሕጋዊ ፓርቲን ሽፋን በማድረግ ሥልጣንን በኃይል ለመያዝ እና አገር ለማፍረስ አደራጅተዋል» በሚል ተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ ጠይቆ የነበረ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብታቸውን ፈቅዷል። ተጠርጣሪዎቹ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በቁጥጥር ሥር ውለው ለአንድ ወር ያህል በእስር ላይ ነበሩ።
431