3 330
مشترکین
+324 ساعت
+277 روز
+9830 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئیه '26
ژوئیه '26
+144
در 0 کانالها
ژوئن '26
+142
در 0 کانالها
Get PRO
مه '26
+204
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '26
+124
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '26
+104
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '26
+113
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '26
+117
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '25
+121
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '25
+130
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '25
+106
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '25
+102
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '25
+172
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '25
+226
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '25
+163
در 0 کانالها
Get PRO
مه '25
+236
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '25
+238
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '25
+158
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '25
+165
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '25
+216
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '24
+229
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '24
+286
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '24
+252
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '24
+119
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '24
+171
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '24
+76
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '24
+54
در 0 کانالها
Get PRO
مه '24
+147
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '24
+228
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '24
+120
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '24
+1 068
در 0 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 24 ژوئیه | +3 | |||
| 23 ژوئیه | +7 | |||
| 22 ژوئیه | +5 | |||
| 21 ژوئیه | +9 | |||
| 20 ژوئیه | +10 | |||
| 19 ژوئیه | +5 | |||
| 18 ژوئیه | +5 | |||
| 17 ژوئیه | +3 | |||
| 16 ژوئیه | +2 | |||
| 15 ژوئیه | +5 | |||
| 14 ژوئیه | +4 | |||
| 13 ژوئیه | +8 | |||
| 12 ژوئیه | +8 | |||
| 11 ژوئیه | +6 | |||
| 10 ژوئیه | +4 | |||
| 09 ژوئیه | +11 | |||
| 08 ژوئیه | +7 | |||
| 07 ژوئیه | +6 | |||
| 06 ژوئیه | +6 | |||
| 05 ژوئیه | +9 | |||
| 04 ژوئیه | +6 | |||
| 03 ژوئیه | +2 | |||
| 02 ژوئیه | +13 | |||
| 01 ژوئیه | 0 |
پستهای کانال
ንጉሱ ወደ ጦርነት ከመሄዱ በፊት ቆንጅዬዋ ሚስቱን በአንድ ክፍል ውስጥ ቆልፎባት ቁልፉን ለቅርብ ጓደኛው ሙሳ ሰጠው እና "በአራት ቀን ውስጥ ካልተመለስኩ ክፍሉን ክፈት እና ሚስቴን አግባት…" ብሎት ፈረሱ ላይ ወጥቶ ወደ ጦር ሜዳ ሄደ። ከግማሽ ሰዓት በኋላ ንጉሱ ከኋላው አቧራማ ንፋስ እንዳለ አየ። ቆም ብሎ ጓደኛው ወደ እሱ በፍጥነት እየሮጠ ሲመጣ አየ።
...
"ምነዉ ምን ሆንክ ?" ብሎ ንጉሱ ጠየቀ። በጣም ከመሮጡ የተነሳ ትንፋሹ እየተቆራረጠ ጓደኛው ሙሳ "የተሳሳተ ቁልፍ ነው የሰጠኸኝ" ሲል መለሰ።
....
"ምን?" ብሎ ንጉሱ አይቶት በድንጋጤ እና በመገረም አየዉ ቁልፎቹን ከመሞከሩ በፊት ለአራት ቀናት ይቅርና ለ አንድ ሰአት እንኳን አልጠበቀም።
...
እንደ “ጓደኞችህ” ከምትቆጥራቸው ሰዎች ጋር ተጠንቀቅ እና በትጋት ለምታገኘው ሃብት አደራ ልትሰጣቸው ትችላለህ፤ እነሱ በቅርቡ እንድትሞት እየተመኙልህ ሊሆን ይችላል እና እራስህን መጠበቅህን መዘንጋት የለብንም።
| 2 | እባቡ በጢሻ ውስጥ ሲሽሎከሎክ እና ሲታጠፍ ከበስተጀርባው የሚንቀሳቀሰውን የገዛ ጅራቱን የሌላ ጠላት ይመስለውና በደመነፍስ ተመርቶ ጅራቱን መዋጥ ይጀምራል! ወደ ውስጥ በዋጠው ቁጥር ግን የሚሰማው ህመም እየጨመረ ይሄዳል። እባቡ ግን ህመሙን እራሱ የፈጠረው ሳይሆን "ጠላት" እያጠቃው መስሎት በንዴት ይበልጥ በኃይል መዋጡን ይቀጥላል። በመጨረሻም ራሱን ጨርሶ በመዋጥ ሕይወቱ ያልፋል።
...
ይኸ ክስተት (ራስን መብላት) የሚባል ሲሆን፣ በአብዛኛው እባቦች በጣም ሲጨነቁ፣ አካባቢያቸው ሲሞቅ ወይም የእይታ መጋረድ ሲገጥማቸው የሚያደርጉት ስህተት ነው።
...
የማስተዋል ማነስ ጥፋትን ይጋብዛል። አንዳንድ ጊዜ የምናደርገው ነገር ማንነታችንንና የራሳችንን ወገን የሚጎዳ መሆኑን ሳናስተውል፣ ሌላውን የምንጎዳ መስሎን የጥፋት ጉድጓድ እንቆፍራለን።
.. | 1 514 |
| 3 | አንድ አሳማ ጭቃ ውስጥ ሲንከባለል ቆይቶ ወጣ። መንገድ ላይ ሲጓዝም በአጋጣሚ ከአንድ ግዙፍ ዝሆን ጋር ተገናኙ። ዝሆኑም አሳማውን ሲያየው ወዲያው መንገድ ለቆለት አለፈ።
...
አሳማው በነገሩ ተደስቶ "ጉድ እዩ! ያ ግዙፍ ዝሆን ሳይቀር የሚፈራኝ እኔ ምንኛ ጀግና ነኝ!" እያለ በትዕቢት ይፎክር ጀመር።
...
ይህን የታዘቡ ሌሎች እንስሳት ዝሆኑን ጠጋ ብለው ጠየቁት። "ለመሆኑ አንተን የሚያህል ግዙፍ የተከበረ ፍጡር አሳማ መሰል አነስተኛ እንስሳ መንገድ እንዴት መንገድ ለቀቀለት?"
..
ዝሆኑም "እኔ እኮ አሳማውን ፈርቼው አይደለም፤ ቆሻሻው እንዳይነካኝ ብዬ ነው!" አላቸው።
..
ሰዎች ርቀው የሚሄዱት ስለፈሩ ሳይሆን 'ቆሻሻ' አስተሳሰብና ንግግር እንዳይበክላቸው ብለው ነው።
...
ዝምታንና መራቅን ሁልጊዜም ፍርሃት አድርገህ አትተርጉመው፤ ብልህነት ነው! | 1 615 |
| 4 | ጅቡ አህያውን ሊበላው አሯሯጠው፤ ሊደርስበት ግን ፈጽሞ አልቻለም። ቢል ቢል ቢጫንቀው... ዞር አለና "ይኸ አህያ በጤናው ነው? አብዷል እንዴ?!" አለ ይባላል።
...
በሕይወትህ ውስጥ ብዙ ሰው ሊጥልህ፣ ሊያቆምህና ሊያሸንፍህ ይሮጣል። በጥንካሬህና በጥረትህ እጅ አልሰጥ ስትለው ግን፣ በራስህ ብቃት ያመለጥከው አይመስለውም።
...
የገዛ ድክመቱንና ያንተን ጥንካሬ አምኖ ከመቀበል ይልቅ ስም ሊሰጥህ ይሞክራል፤ "ቡዳ ነው"፣ "አሰርቶ ነው"፣ "ዕድለኛ ነው" እያለ ያማሃል።
..
ዋናው ነገር አንተ ከሚያሯርጥህ "ጅብ" አምልጠህ ግብህ ላይ መድረስህ ብቻ ነው። ጅቡ ማውራቱን አይተውም፤ አንተ ግን መሮጥህን አታቁም! | 1 490 |
| 5 | አንድ አባት ወፍ ልጁን እንዲህ እያለ ሲመክረው "ልጄ ፤ ሰው የሚባለው ፍጡር እጅግ ክፉና ተንኮለኛ ነው። ጥሬህን እየለቀምክ በአጠገብህ ሲያልፍ ድንገት 'ዝቅ' ካለ ፈጥነህ ብረር። ምክንያቱም ዝቅ ያለው ድንጋይ አንስቶ ሊወረውርብህ ሊሆን ይችላልና!"
...
የወፉ ጫጩትም በረዥሙ አሰበና እንዲህ ሲል ጠየቀ። "እሺ አባባ፣ ይሁን! ግን ዝቅ ሳይል ድንጋዩን አስቀድሞ ከኪሱ ይዞ ቢመጣስ?" አባትየውም ልጁን እያየ "ልጄ እኔ የነገርኩህ የኔን ዘመን ችግርና መፍትሔ ነው። አንተ ደግሞ ለዚህ ለተራቀቀው ለዘመንህ አዲስ አስተሳሰብና ጥንቃቄ ጨምርበት" አለው።
...
የትናንት መፍትሔ የዛሬን አዳዲስ ፈተናዎች ሙሉ በሙሉ አይፈታም። ዘመን ሲቀየር የክፋትም ሆነ የችግሮች ስልት አብሮ ስለሚራቀቅ፣ እኛም ዘመኑን የሚመጥን ንቃት፣ ጥንቃቄና አዲስ አስተሳሰብ ሊኖረን ይገባል! | 1 411 |
| 6 | በአዕምሮ ህሙማን ሆስፒታል ውስጥ አንድ መጽሐፍ የሚያነብ ወጣት አየሁ። ከሌሎቹ ታማሚዎች የተለየ ሆኖ ስላገኘሁት ቀረብ ብዬ "እንዴት እዚህ ልትገባ ቻልክ?" ስል ጠየቅኩት።
...
ልጁም መጽሐፉን ዘጋና እንዲህ ሲል መለሰልኝ። "አባቴ እንደሱ ሀኪም እንድሆን ፈለገ፤ እናቴ እንደ ወንድሟ ነጋዴ እንድሆን ተመኘች። እህቴ ታዋቂ አርቲስት እንድሆን ስትገፋፋኝ፣ አያቴ ደግሞ የሃይማኖት አባት እንድሆን ይጸልይ ነበር። እኔ ግን የራሴ ህልም ነበረኝ። የሁሉንም ፍላጎት ለማርካት ስታገል ግን በመጨረሻ ራሴን አጣሁት። አዕምሮዬ ሲታወክ ግን ሁሉም ተስማምተው እዚህ አስገቡኝ። አሁን ግን በጣም ደስተኛ ነኝ! ምክንያቱም እዚህ ቦታ ማንም 'ይሄንን ሁን' የሚለኝ የለም። እዚህ የመጣሁት በመጨረሻ ራሴን ለመሆን ነው!" አለኝደ
....
የልጆቻችሁን ህይወት በእናንተ ፍላጎት አትቅረጹ። የሌሎችን ህልም ለመኖር ሲታገሉ የራሳቸውን ማንነት ያጣሉ። በዚህም እድሜያቸውን በሙሉ ሲኳትኑ ደስተኛ ያልሆነ ህይወት ይኖራሉ። | 1 455 |
| 7 | ወጣቱ መምህሩን "ስለ ፍቅር እና ጋብቻ ንገረኝ ።" አለው። መምህሩም "ወደ ስንዴ ማሳው ሂድና ረዥሙን ስንዴ ቁረጥ፤ ህጉ ግን ወደ ኋላ መመለስ አትችልም።" አሉት።
....
ወጣቱ ሄዶ ባዶ እጁን ተመለሰ። "ምነው?" አሉት። "በጣም የሚያምር ስንዴ አግኝቼ ነበር፤ ነገር ግን ‘ከዚህ የተሻለ አገኝ ይሆናል’ ብዬ አልፌው ሄድኩ። ወደፊት ስሄድ ግን የተሻለ አላገኘሁም፤ ወደ ኋላ መመለስ ደግሞ አይቻልም።"አላቸው። መምህሩም እንዲህ አሉት። "እንግዲህ ፍቅር ማለት ይህ ነው! ምርጡን ዕድል (ሰው) እያየህ፣ ‘ከዚህ የተሻለ አገኝ ይሆናል’ በሚል ስግብግብነት አልፈኸው ትሄዳለህ። ነገር ግን ጊዜው ካለፈ በኋላ ያጣኸው ነገር ምን ያህል ውድ እንደነበር ይገባሃል።"
...
"እሺ ጋብቻስ?” አላቸው። መምህሩም “አሁን ደግሞ ወደ በቆሎ ማሳው ሂድና ትልቁን ቁረጥ" አሉት።
...
ወጣቱ በዚህ ጊዜ ብዙ ሳይቆይ አንድ መካከለኛ በቆሎ ይዞ ተመለሰ። 'ቅድም የሰራሁትን ስህተት መስራት አልፈለግኩም። ፍፁም ባይሆንም፣ ‘ከዚህ የተሻለ እፈልጋለሁ’ ብዬ ብጓዝ ባዶ እጄን እንደምቀር አውቄያለሁ። ስለዚህ ይሄኛውን ወድጄና አምኜበት ይዤው መጣሁ።" አላቸው።
...
መምህሩም ፈገግ ብለው "እንግዲህ ጋብቻ ማለት ደግሞ ይህ ነው! ፍፁም የሆነ ሰው ፍለጋ ህይወትህን አታባክንም። ካገኘኸውና አብሮህ ሊሆን ከሚችለው ሰው ጋር ፍቅርንና እምነትን መስርተህ፣ ባገኘኸው ነገር ረክተህ በደስታ መኖር ማለት ነው!"
...
ስለፍቅር ስናስብ ፍፁም ነገር በመፈለግ እንባዝናለን፤ ጋብቻ ግን ካገኘኸው መልካም ሰው ጋር ፍፁም የሆነ ህይወት መፍጠር ነው። | 1 343 |
| 8 | አንድ ጊዜ የአንድ መንደር ሰዎች ዝናብ እንዲዘንብ ለመጸለይ ወሰኑ። በጸሎቱ ቀን ሁሉም ተሰበሰቡ፤ ነገር ግን ጃንጥላ ይዞ የመጣው አንድ አነስተኛ ልጅ ብቻ ነበር። ይህ እውነተኛ እምነት ነው።
...
አንድ ዓመት ሕፃንን ወደ ላይ ወርወር ስታደረገው በፍርሃት ፈንታ ይስቃል፤ ምክንያቱም አባቱ (ወላጁ) መልሶ እንደሚያቅፈውና እንደማይጥለው ሙሉ በሙሉ ያውቃል። ይህ መተማመን ነው።
...
በየሌሊቱ ለመተኛት ወደ አልጋችን ስናመራ፣ በማግስቱ ጠዋት በሕይወት ለመንቃታችን ምንም አይነት የፅሁፍ ዋስትና የለንም፤ ነገር ግን የማለዳውን ፀሀይ ለማየት በማሰብ ነገን በብዙ እቅዶች እናስባለን። ይህ ተስፋ ነው።
...
ዛሬም፣ ነገም በህይወታችን እምነት፣ መተማመን እና ተስፋ አይለየን። | 1 275 |
| 9 | አንድ ፈላስፋ ከሙላ ናስሩዲን ጋር ሊከራከር ቀጠሮ ይይዛል። በቀጠሮው ቀን ናስሩዲንን ቢጠብቅ ናስሩዲን ሳይመጣ ይቀራል።ፈላስፋውም በንዴት ወደ ናስሩዲን ቤት ሄዶ በሩ ላይ የማይረባ ደደብ ብሎ ጽፎ ይሄዳል።
ናስሩዲን ሲመለስ ጽሑፉን አይቶ ወደ ፈላስፋው ቤት ሄዶ፣ 'ቀጠሯችንን ረስቼ ነበር፤ ስምህን በሬ ላይ አይቼ ነው ያስታወስኩት' አለው።
...
ከእውነት ፍለጋ ይልቅ በክርክር ማሸነፍ የሚጠመድ ሰው ከንቱ ድካም ውስጥ ይወድቃል። ጥበበኛ ሰው ሌሎችን ከማሸነፍ በፊት ራሱን ለማወቅ ይጥራል። | 1 464 |
| 10 | አንድ አባት ልጁን ሁልጊዜ ሲመክረው ጠንካራ እና ጀግና እንዲሆንለት በማሰብ ፣ መስመርህን የሚያልፍ ሰው ሁሉ አትታገስ፣ በሀይልም ቢሆን ክብርህን አስጠብቅ፤ ምታው!" እያለ አሳደገው።
...
ልጁ ችግርን በሃይል ብቻ መፍታት እንደሚቻል አምኖ አደገ። አንድ ቀን ግን አባት በሆነ ነገር ተናዶ ልጁን ክፉኛ ተቆጣው። በዚህ ጊዜ ልጁ አባቱን እንደ ወላጅ ሳይሆን "እንዳስቸገረው ሰው" ድንጋይ አነሳና አባቱን መትቶ ገደለው።
...
ልጁ ለፍርድ ቀረበ። ዳኛው በቁጣ "እንዴት የገዛ አባትህን ትገድላለህ?" ሲሉ ጠየቁት።
ልጁ "ክቡር ዳኛ፣ አባቴ ‘የሚያስቸግርህን ሁሉ በለው’ እያለ ነው ያሳደገኝ። በዚያች ሰዓት አባቴ በጣም አስቸግሮኝ ነበር፤ ታዲያ ከመምታት በቀር ምን ማድረግ እችል ነበር?" ብሎ ግራ በመጋባት መልሶ ጠየቀው።
...
ለልጆቻችን የምንሰጠው ምክርና የምናሳያቸው ባህሪ የነገ ማንነታቸውን ይወስናል። ዛሬ በልጆቻችን አእምሮ ውስጥ የምንዘራው መርዝ፣ ነገ መድረሻችንን ያጠፋል። | 1 345 |
| 11 | ሰውዬው በብርድ ሌሊት ግቢውን እየጠበቀ ያለውን ዘበኛ ያየዋል። ብርዱ በጣም ኃይለኛ ስለነበር "ይሄን ከባድ ብርድ እንዴት ትችለዋለህ?" ብሎ ጥበቃውን ጠየቀው።
ጥበቃውም "ጌታዬ! ምንም የለኝም፤ ለብዙ ዓመታት ይሄንን ብርድ ለምጄዋለሁ" አለው።
...
ሰውዬውም እጅጉን አዝኖ "እሺ አሁን ወደ ቤት ልግባና ሙቅ የሆነ ብርድ ልብስ እልክልሃለሁ።" አለው። ጥበቃውም በጣም ተደሰተ።
...
ነገር ግን ሀብታሙ ሰው ቤት እንደገባ ቃሉን ዘነጋው። ጠዋት ላይ ትዝ ብሎት በፍጥነት ብርድ ልብሱን ይዞ ቢሄድም፣ ጥበቃው ግን በብርድ ተመትቶ ህይወቱ አልፎ አገኘው።
...
ከአጠገቡም እንዲህ የምትል ማስታወሻ ተጽፋ ነበር። "ጌታዬ! በየቀኑ ያለ ብርድ ልብስ ብርዱን የመቋቋም አቅም ነበረኝ። ነገር ግን ብርድ ልብስ እልክልሃለሁ ብለህ ቃል ስትገባልኝ፣ በተስፋህ ላይ ተደገፍኩ፤ የነበረኝን የውስጥ መቋቋም አቅሜን ግን አጣሁት።"
...
ለሰዎች የምትሰጠው ተስፋ ካልተጠበቀ ትልቅ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል። ለአንተ ቀላል የሆነው ቃል፣ ለሌላው ሰው ህይወት ነው። ቃል ከገባህ አትዘንጋ።
...
ከተቻለህ-በሰዎች ተስፋ ላይ ብቻ አትደገፍ። የራስህን ውስጣዊ ጥንካሬ በሰዎች ቃል አትቀይረው። መደገፉስ ቃሉን በማያጥፈው ፈጣሪ ነው። | 1 288 |
| 12 | ሰውዬው የሚወዳት ባለቤቱን በሞት ያጣል። ከሚስቱ የተረፈው አንድ ትልቅ ፎቶግራፍ ብቻ ስለነበር፣ ፎቶውን ሳሎን ላይ ሰቅሎ ሁልጊዜ ያየውና ይሳለመው ነበር።
..
እንደ ሁልጊዜው አገልጋዮቹ ፎቶዋን ሲያጸዱ በስህተት ጥለውት ማዕቀፉ (Frame) ይሰበራል። አባትየው በንዴት ተሞልቶ፣ ወደ ከተማው ምርጥ ባለሙያ ዘንድ በመሄድ እጅግ ውድና በወርቅ የተለበጠ አዲስ ማዕቀፍ አሰራ።
...
ፎቶውን በአዲሱ ማዕቀፍ አድርጎ ሳሎን ሲሰቅለው ግን ወደ ቤት የሚመጡ እንግዶች በሙሉ በማዕቀፉ ውበት ተደምመው የሚያዩት ውዱን ማዕቀፍ እንጂ ውስጥ ያለውን የባለቤቱን ፎቶ አልነበረም።
...
ይህን አንድ ጎሮቤቱ ለአባትየው "ወዳጄ ያሰናዳኸው ማዕቀፍ እጅግ ጎልቶ ከመውጣቱ የተነሳ፣ ሰዎች የባለቤትህን ፊት ማየት አቁመዋል። ዋና መታየት የሚገባውን በውጫዊ ውበት ሸፈንከው።"
...
ብዙዎቻችን ዋናውን ነገር ትተን ውጫዊው “ማዕቀፍ” ላይ እንጠመዳለን።
...
ልጆቻችንን በፍቅርና በባህሪ ማሳደግ ሲገባን፣ ውድ ትምህርት ቤትና ውድ ልብስ ላይ ብቻ እናተኩራለን። ትዳርን ለመገንባት ማሰብ ሲገባን፣ ሰርጉን ፍጹም ለማድረግ እንባዝናለን።
...
ውጫዊው ማዕቀፍ የቱንም ያህል ቢያምር፣ ውስጥ ያለው ዋናው ነገር (ፎቶው) ከጠፋ ትርጉም የለውም። | 1 366 |
| 13 | بدون متن... | 1 211 |
| 14 | እናቱ በናፍቆትና በተስፋ ልጇ ወደ ቤት የሚመለስበትን ሰዓት ትጠባበቃለች። እሱ ግን ለጎጆአቸው ማስደገፊያ የሚሆን ምሰሶ (ባላ) ለመቁረጥ ከጓደኞቹ ጋር ወደ ጫካ አምርቷል። እዚያም እንደደረሱ በጨዋታና በልጅነት ፉክክር ተጠምደው ጊዜው እንዴት እንደነጎደ አላስተዋሉም ነበር።
...
ከጫካው አቅራቢያ በሚያልፈው ወንዝ ላይ አስፈሪና አደገኛ ድልድይ ተሰርቷል። ባላ ለመቁረጥ የመጡት ወጣቶችም በዚሁ በድልድዩ ስጋቶች ላይ እየተረማመዱ፣ “አንተ አትችልም፤ እኔ እችላለሁ!” በሚል የፉክክር ስሜት መሻገራቸውን ተያያዙት።
...
#ሽመልስ መጀመሪያ ላይ በዚህ አደገኛ ጨዋታ ውስጥ የመሳተፍ ፍላጎት አልነበረውም። ነገር ግን የጓደኞቹ “አትችልም!” የሚል ስላቅና ጩኸት፣ በውስጡ ተኝታ የነበረችውን የጀብደኝነት ስሜት ቀሰቀሳት፤ እንዲደፍርም ገፋፋው።
...
#ሽመልስ የፍርሃት ስሜቱን ዋጥ አድርጎ ወደ ድልድዩ ጫፍ ላይ ወጣ... መጓዝ ጀመረ... አንድ ስምንት ሜትር ያህል እንደተጓዘ ግን እግሩ አዳልጦት ወደ ታች ተከሰከሰ። ያቺ ሰከንድ የመጨረሻው ሆነች።
..
የልጇን #ሽመልስ ፍልቅልቅ ሳቅና ጨዋታ በናፍቆት ስትጠብቅ የነበረችው እናት፣ በመጨረሻ ያገኘችው ልጇን ሳይሆን በቃሬዛ የተሸከሙትን አስከሬን ነበር። ሰፈሩም በጭንቅና በኡኡታ ተሞላ።
...
አንዳንዴ ለእኛ የማይሆኑና አደጋ ያላቸውን ነገሮች መተው ፍጹም ብልህነት ነው። አደጋ እንዳለው እያወቁ በድፍረት መጋፈጥ፣ ወይም “ሰው ስላደረገው ብቻ አደርጋለሁ” ብሎ ያላስፈላጊ ፉክክር ውስጥ መግባት ዋጋው የህይወት ማጣት ነው።
....
አንዳ'ዴ “አልችልም” ወይም “አልፈልግም” ማለት መሸነፍ ሳይሆን ህይወትን መታደግ ነው። | 1 435 |
| 15 | የዓሳ ሥጋ መሸጫ ውስጥ ውለህ ስትወጣ ዓሳ ዓሳ ትሸታለህ
ሽቶ መሸጫ ውስጥ ውለህ ስተወጣ ሽቶውን ሳትቀባ ሽቶ ሽቶ ትሸታለህ
ከሀሜተኛ ጋር ስትውል ሀሜተኛ ትሆናለህ
ከብሶተኛ ጋር ስትውል ብሶተኛ ትሆናለህ
ከአመስጋኝ ጋር ስትውል አመስጋኝ ትሆናለህ
ራዕይ ካለው ሰው ጋር ስትውል አንተም ባለራዕይ ትሆናለህ
በአጠቃላይ ውሎህን መምሰልህ ወይም የውሎህ ውጤት መሆንህ አይቀሬ ነው። | 1 226 |
| 16 | ባል እና ሚስት ወደ አዲሱ ቤታቸው ገና መዛወራቸው ነው። አንድ ቀን ጠዋት፣ ሚስትየው በመስታወት መስኮት በኩል ወደ ውጭ ስትመለከት አዲስ ጎረቤታቸው ያጠበቻቸውን ልብሶች በገመድ ላይ ስታሰጣ አየቻት።
...
ሚስትየው ወደ ባሏ ዞራ "ያጠበችው ልብስ ጨርሶ አልነፃም። ልብሶቹ አሁንም ቆሻሻ ናቸው። ትክክለኛ የልብስ ሳሙና አጠቃቀም የምታውቅ አይመስለኝም፤ ወይም ደግሞ እንዴት እንደምትታጠብ ማንም አላስተማራትም።"አለችው።
...
ባልየው ግን ምንም ሳይናገር በዝምታ አለፈ። ከዚያን ቀን ጀምሮ ጎረቤቷ ልብስ ባሰጣች ቁጥር፣ ሚስቱ በመስኮት እየተመለከተች ተመሳሳይ ትችትና ወቀሳ መሰንዘሯን ቀጠለች። "ዛሬም ልብሶቹ አልጠሩም፣ ዛሬም አልተለወጠችም።" እያለች ታወራለች።
...
ከአንድ ወር በኋላ ግን፣ ሚስትየው ጠዋት ተነስታ በመስኮት ስትመለከት በጣም ተገረመች። የጎረቤቷ ልብሶች በገመዱ ላይ እንደ በረዶ ነጭ ሆነው፣ በፀሐይ ብርሃን ፍንትው ብለው ታዩዋት።
...
በመገረም ወደ ባሏ " እስኪ ተመልከት፤ ዛሬ በመጨረሻ እንዴት አድርጋ ማጠብ እንዳለባት አውቃለች። ልብሶቿ እንዴት እንደነጡ ተመልከት። ማን አስተማራት ይሆን?"አለችው።
...
ባልየው ጋዜጣውን ቀስ አድርጎ ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠና ፈገግ ብሎ " ማንም አላስተማራትም። ዛሬ ማለዳ አንቺ ሳትነሺ እኔ ቀድሜ ተነስቼ መስኮቱን አፅድቼ ነው። ቆሻሻው ስለተነሳ ነው።" አላት።
...
ሰዎችንና በዙሪያችን ያለውን ዓለም የምናይበት መንገድ፣ እኛ በውስጣችን ባለን መስተዋት ንጽህና ላይ የተመሠረተ ነው። ሌሎችን ከመተቸታችን እና ጥፋተኛ ከማድረጋችን በፊት፣ መጀመሪያ የራሳችንን አእምሮ እና አመለካከት ማጽዳት ይኖርብናል።
...
ብዙ ጊዜ የምንቀየምበት ነገር ያለው በሌሎች ላይ ሳይሆን፣ እኛ ዓለምን በምናይበት በቆሸሸው መነጽራችን ላይ ነው። | 1 447 |
| 17 | አንድ ታዋቂ ፕሮፌሰር ወደ አንድ የዜን መምህር ሄደ።
..
“ስለ መንፈሳዊነት እና ስለ እውነት ልታስተምረኝ መጥቻለሁ።” አለው።
..
ግን ከተቀመጠ ጀምሮ ራሱ ብቻ ይናገር ነበር።
“ይህን መጽሐፍ አንብቤያለሁ…”
“ይህን ፍልስፍና አውቃለሁ…”
“ይህን አስተሳሰብ ተምሬያለሁ…”
...
የዜን መምህሩ ግን ዝም ብሎ ሻይ ብርጭቆ ውስጥ እመቅዳት ጀመረ።
..
ጽዋው ሞላ።
...
ግን መቅዳቱን አላቆመም። ሻዩ ከጽዋው ውጭ መፍሰስ ጀመረ።
..
ፕሮፌሰሩ ደነገጠ።
“አቁሙ እንጂ መምህር! ጽዋው እኮ ሞልቷል!” አለ።
..
መምህሩ ፈገግ አለና እንዲህ አለ፤
“አንተም እንደዚሁ ነህ። አእምሮህ በራስህ ሀሳብ ተሞልቷል። አዲስ ነገር እንዴት ይገባበታል?”
....
አንዳንዴ ለመማር…መጀመሪያ “አውቃለሁ” የሚለውን መተው ያስፈልጋል። | 1 332 |
| 18 | ለአንገቷ ጌጥ ልታሰራ አንዲት ሴት የወርቅ አንጥረኛ ጋር ሄደች። አንጥረኛው ወርቁን በጣም በሚያቃጥል እሳት ውስጥ አስቀምጦ በከፍተኛ ትኩረት ይመለከተው ነበር።
...
ሴትዮዋም ጠጋ ብላ "ወርቁ በእሳቱ ውስጥ ሲበስል ለምን አንድም ሰከንድ አይንህን ሳትነቅል ትከታተለዋለህ?" ስትል ጠየቀችው።
...
አንጥረኛውም መለሰላት "ወርቁ እሳቱ ውስጥ በሚሆንበት ጊዜ ሙሉ ጊዜዬን እዚያው ላይ ማድረግ አለብኝ። እሳቱ በጣም ከቀነሰ ቆሻሻው አይጠራም፤ እሳቱ በጣም ከበረታ ደግሞ ወርቁ ይበላሻል። ስለዚህ እሳቱን እየተቆጣጠርኩ በንቃት እጠብቀዋለሁ።"
....
ሴትዮዋም "ታዲያ ወርቁ በትክክል መብሰሉንና ዝግጁ መሆኑን በምን ታውቃለህ?" አለችው።
...
አንጥረኛው "በጣም ቀላል ነው፤ የራሴ መልክ በወርቁ ላይ ፍንትው ብሎ ሲታየኝ ስራዬን አበቃለሁ" አላት።
...
እኛም በህይወት እሳት ውስጥ ስናልፍ ፈጣሪ የተወን ይመስለናል፤ እሱ ግን የእሳቱን ሙቀት እየተቆጣጠረ፣ የራሱ ውብ መልክ በእኛ ውስጥ እስኪንጸባረቅ ድረስ ከምንጊዜውም በላይ በቅርበት እየጠበቀን ነው። | 1 288 |
| 19 | ንጉሱ ሰፊ ሀገር ድል አድርጎ፣ ብዙ ወርቅና ብር ሰብስቦ ወደ ሀገሩ እየተመለሰ በመንገድ ላይ አንድ ሰው ያገኘዋል። ሰውዬውም መንገድ ዳር ተቀምጦ በደስታ እየዘፈነ ነበር።
...
ንጉሱም ፈረሱን አቁሞ "አንተ ምስኪን ሰውዬ እኔ እጅግ ሰፊ ግዛቶችን ድል አድርጌ፣ ይህንን ሁሉ ሀብት ይዤ እየተመለስኩ ነው። አንተ ግን ምንም ሳይኖርህ እንዴት እንዲህ ትደሰታለህ?"
..
ሰውዬውም ንጉሱን "ንጉስ ሆይ አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ። አሁን ወደ ሀገርህ እየተመለስክ በበረሃ ውስጥ ከፍተኛ የውሃ ጥም ቢይዝህና ልትሞት ብትደርስ፣ አንድ ሰው አንድ ብርጭቆ ውሃ ይዞ ቢመጣና 'ይህንን ውሃ የምሰጥህ ግማሽ መንግስትህን ከሰጠኸኝ ብቻ ነው' ቢልህ ትሰጠዋለህ?" ንጉሱም ሳያቅማማ "አዎ! በህይወት ለመኖር ስል ግማሽ መንግስቴን እሰጠዋለሁ" አለ።
...
ሰውዬው ቀጠለ "ውሃውን ጠጥተህ ነገር ግን ሽንትህ ቢዘጋና ሊገድልህ ቢቃረብ፣ ሌላ ሰው መጥቶ 'ሽንትህን በቀላሉ እንድትሸና የማደርግህ ቀሪውን ግማሽ መንግስትህን ከሰጠኸኝ ነው' ቢልህስ?"
ንጉሱም "አዎ፤ ካልሸናሁ እሞታለሁ፣ ስለዚህ ቀሪውንም መንግስቴን እሰጠዋለሁ" አለው።
...
ሰውዬውም "ታዲያ ንጉስ ሆይ! በአንድ ብርጭቆ ውሃና በአንድ ጊዜ ሽንት ለሚሸጥ መንግስት መላ ህይወትህን ለምን በጭንቀት ታሳልፋለህ? እኔ ያለምንም መንግስት በነፃ ውሃ እጠጣለሁ፣ በነፃ እሸናለሁ፣ ስለዚህ ካንተ በላይ ደስተኛ ነኝ!"
...
ሰው በህይወቱ የሚያስፈልጉትን መሰረታዊ የሆኑትን የታላቅ ተፈጥሮ ስጦታዎች (ጤና፣ ሰላም፣ ንጹህ አየርና ውሃ) በነጻ አግኝቷል። ነገር ግን የሌለውን ተጨማሪ ነገር ለማግኘት ሲሮጥ ያለውን ትልቅ ሀብት (ጤናውንና ሰላሙን) ያጣል።
...
ያለንን ይባርክ!! ትልቁ ሃብት ጤና ነው፤ በሱም ደስ ይበለን:: | 1 299 |
| 20 | بدون متن... | 1 |
