University of Gondar (UoG)
University of Gondar is one of a pioneer public higher education institution with commendable achievements in teaching, research and community services.
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام University of Gondar (UoG)
کانال University of Gondar (UoG) (@uofgondar) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 13 530 مشترک است و جایگاه 14 860 را در دسته آموزش و رتبه 2 510 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 13 530 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 01 اوت, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 280 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 13 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 29.16% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 11.94% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 3 946 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 616 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 6 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“University of Gondar is one of a pioneer public higher education institution with commendable achievements in teaching, research and community services.”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 02 اوت, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 02 اوت | +12 | |||
| 01 اوت | +13 |
| 2 | بدون متن... | 3 333 |
| 3 | بدون متن... | 2 818 |
| 4 | ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ አዲስ ፕሬዚዳንት ተሾመ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በአመራር ደረጃ የተደረገውን ለውጥ ተከትሎ ከሰባት ዓመታት በላይ ዩኒቨርሲቲውን በፕሬዚዳንትነት ሲመሩ የቆዩት ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ሆነው በመዛወራቸው፣ በምትካቸው አዲስ ፕሬዚዳንት መመደባቸው ታውቋል።
አዲሱ ፕሬዚዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደ ዩኒቨርሲቲው በትምህርት፣ በምርምር፣ በማኅበረሰብ አገልግሎትና በተቋማዊ አስተዳደር ያስመዘገበውን ውጤት በማስቀጠል የተሻለ አፈጻጸም ለማረጋገጥ ከዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብና ከሁሉም አጋር አካላት ጋር በትብብር መስራት እንደሚገባቸው ተገልጿል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማ/ሰብ ፣ የጎንደር ከተማ አስተዳደርየመንግስት ከፋተኛ ኃላዎችና የሀይማኖት አባቶች ፣ ለቀድሞው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን በተቋሙ እድገት ላይ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበው፣ ለአዲሱ ፕሬዚዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደ ቀጣዩ ጊዜ የተሳካ የሥራ ዘመን እዲሆን ተመኝተዋል።
ትምህርት ሚኒስተር እያደረገ ባለው አዲስ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የፕሬዚዳንቶች ድልድል መሰረት የትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሰረተ-ልማት ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ በተገኙበት በዛሬው ዕለት በሁለቱም ፕሬዚዳንቶች መካከል የስራ ርክክብ ተካሂዷል።
ለዶ/ር አስራት እና ለዶ/ር የቻለ መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለልህቀት እንተጋለን!
የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ
ሀምሌ 21/218 ዓ.ም | 3 539 |
| 5 | بدون متن... | 3 362 |
| 6 | بدون متن... | 2 900 |
| 7 | بدون متن... | 2 831 |
| 8 | بدون متن... | 2 583 |
| 9 | بدون متن... | 2 243 |
| 10 | የጎንደር ዩኒቨርሲቲን የጽናትና የለውጥ ጉዞ የሚያስቃኘው «ጽናት» መጽሐፍ በደማቅ ሁኔታ ተመረቀ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ያለፈባቸውን የታሪክ ውጣ ውረዶችና ያስመዘገባቸውን ተቋማዊ የለውጥ ጉዞዎች በሰፊው የሚዳስሰው «ጽናት፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ» የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ ዛሬ ሐምሌ 18/2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ ለምረቃ በቅቷል።
በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን የተዘጋጀው ይህ ልዩ ታሪካዊ ሰነድ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት የተካሄደው በማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር የመሰብሰቢያ አዳራሽ ነው።
በዚህ ታሪካዊ መርሀ- ግብር ላይ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው፣ የጎንደር ከተማ ም/ ከንቲባ ወ/ሮ ደብሬ የኋላ፣ የዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ፕሬዚዳንቶች፣ ከፍተኛ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው ልዩ እንግዶች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የከተማዋ ነዋሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት ተገኝተዋል።
መጽሐፉ መታሰቢያነቱ ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ርስታቸውን ለሰጡ 59 አርሶ አደሮች፣ እንዲሁም በተለያዩ ዘመናት በአመራርነት፣ በባለሙያነት፣ በሰራተኝነትና በአጋርነት ተቋሙን አሁን ላለበት ታላቅ ደረጃ ላደረሱ ምስጉን ባለውለታዎች በሙሉ እንደሆነ ተገልጿል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ም/ፕሬዚዳንትና አቶ ልጃለምን የመጽሀፉ የምረቃ ሥነ- ስርዓት ኮሚቴ አባል አቶ ልጃለም ጋሻው በመርሀ- ግብሩ መክፈቻ ባደረጉት ንግግር፣ «ተቋማት በሂደታቸው ውስጥ የሚያልፉባቸውን ፈተናዎችና የሚያስመዘግቧቸውን ስኬቶች በጽሁፍ ሰነድ አድርገው ካልያዙ የታሪክ ሂደቶች ይቋረጣሉ» ብለዋል።
አክለውም፣ ይህ «ጽናት» የተሰኘ መጽሐፍ ተቋሙ ከ1947 ዓ.ም. ጀምሮ ያለፈባቸውን ዘረፈ-ብዙ ጉዞዎች፣ ፈተናዎችና የደረሰበትን የዕድገት ደረጃ በትክክለኛ መረጃና ታሪካዊ ሰነዶች አስደግፎ ያቀረበ ድንቅ ስራ መሆኑን አስረድተዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ካሳሁን ተገኘ በበኩላቸው የፕሬዝዳንቱን የህይወት ጉዞ፣ ስብዕና፣ የመሪነት ባህሪና የአካዳሚክ ስኬቶች እንዲሁም መጽሐፉ ለትውልድ የሚያስተላልፈውን ትልቅ ትምህርት በተመለከተ የዩኒቨርሲቲውን ማህበረሰብ በመወከል ሀሳባቸውን አካፍለዋል።
በሥነ-ስርዓቱ ላይ በዩኒቨርሲቲው ሞዴል ትምህርት ቤት ተማሪ ኢዮስያስ ፋሲል የተገጠመው ግጥም በፋሲለደስ የባህል ቡድን በኩል በመዝሙር እና በተማሪው የቀረበ ሲሆን፣ ይህም ለዝግጅቱ ልዩ ድምቀትን ሰጥቶታል።
የመጽሐፉን ዳሰሳ ያቀረቡት የቀድሞው የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕ/ር መንገሻ አድማሱ እና የቀድሞው የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር በላይ ካሣ መጽሐፉ የጎንደር ዩኒቨርሲቲን የተቋምነት ጉዞ፣ ዓላማ እና የጽናት መንገድ በግልጽ የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም በፕ/ር ተከተል ዮሐንስ፣ በጎንደር ከተማ ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው፣ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ም/አስተዳዳሪ አቶ አላምረው አበራ፣ በቀድሞው የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕ/ር ይግዛው ከበደ እና የአካዳሚክ ስታፍ ተወካዩ ፕ/ር አምሳሉ ፈለቀ አስተያየቶች ቀርበዋል።
የመጽሐፉ ደራሲና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን ባደረጉት ንግግር መጽሐፉ የግል ታሪክ (ባዮ ግራፊ) አለመሆኑን ጠቁመው፤ ይልቁንም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ላይ ቢያጠነጥንም በአጠቃላይ የሀገራችን ከፍተኛ ትምህርት ታሪክ አካል፣ የስኬቶች አቅም እና የቀጣይ ግስጋሴ ጠቋሚ ካርታ እንደሆነ ገልጸዋል።
ዶ/ር አሥራት አያይዘውም መጽሐፉ የተቋሙን ታሪክ ለቀጣይ ትውልዶች አጋዥና መነሻ ለማድረግ፣ በተቋሙ ውስጥ የመጽሐፍ ዝግጅትና የንባብ ባህል እንዲጎለብት ለማነሳሳት፣ለወደፊት ተመራማሪዎች ጠንካራ ሳይንሳዊና ታሪካዊ መነሻ ለማስቀመጥ ዓላማ ያደረገ መሆኑን አብራርተዋል።
በተጨማሪም የከተማዋ መሪዎችና የዩኒቨርሲቲው ምሁራን የየራሳቸውን ተሞክሮ እንዲጽፉ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ አዲስ የተቋቋመው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬስም እንዲህ ያሉ ረቂቅ ሥራዎችን በጥራት የማሳተም ኃላፊነቱን እንዲወጣ አስገንዝበዋል።
11 ምዕራፎችና 390 ገጾች ያሉት ይህ መጽሐፍ፣ ከ1947 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ 2017 ዓ.ም. ድረስ ያለውን የ70 ዓመታት ታሪካዊ ጉዞና ተቋማዊ ማስታወሻዎችን በአንድነት የያዘ ነው።
ፕሬዛዳንቱ የ«ጽናት» መጽሐፍ የመጀመሪያ እትም ሽያጭ 50 በመቶ (50%) ለ2019 ዓ.ም ለተቸገሩ ሕፃናት የትምህርት ቁሳቁስ መግዣ የሚውል መሆኑን አብስረዋል።
በመጨረሻም የተቋሙን ታሪክ፣ ተሞክሮ እና የለውጥ ጉዞ በአንድ ላይ የሚያስተሳስረው «ጽናት» መጽሐፍ በደማቅ ሁኔታ ተመርቆ ፕሮግራሙ ተጠናቋል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለልህቀት እንተጋለን!
የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ
ሐምሌ 18/2018 ዓ.ም | 2 432 |
| 11 | بدون متن... | 3 240 |
| 12 | የዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ሽግግር በኢትዮጵያ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
"የዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ሽግግር በኢትዮጵያ እንዲሁም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተሞክሮ" በሚል ርዕስ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝ ሽግግር ቴክኒካል ኮሚቴ የተዘጋጀ የተሞክሮ ልውውጥና የውይይት መርሀ-ግብር ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም በማራኪ ግቢ ዘርዓያዕቆብ አዳራሽ ተካሂዷል።
መርሀ-ግብሩን የከፈቱት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አስራት አፀደወይን፣ ዩኒቨርሲቲው ራስ ገዝ ለመሆን የሚያስፈልጉ 57 የፖሊሲና ማስፈፀሚያ ሰነዶችን በማዘጋጀት ወደ መጨረሻው የዝግጅት ምዕራፍ መድረሱን ገልጸዋል።
በሂደቱም ከ300 በላይ ምሁራን የነበራቸውን ንቁ ተሳትፎ በማድነቅ፣ እንዲህ ያሉ የተሞክሮ መድረኮች የራስ ገዝ ሽግግሩን ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳላቸው አስገንዝበዋል።
በውይይቱ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጡት ፕሮፌሰር አበባው ይርጋ በራስ ገዝ ሽግግር ዙሪያ የዓለም አቀፍ እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ተሞክሮ በማቅረብ፣ ሂደቱ ያስገኘውን ውጤት፣ የገጠሙትን ተግዳሮቶች እና የተወሰዱ መፍትሄዎችን አጋርተዋል።
ራስ ገዝ የተቋማትን አስተዳደራዊ ብቃት፣ የሀብት አስተዳደር ቅልጥፍና እና የአካዳሚክ ጥራት እንደሚያጎለብትም አብራርተዋል።
ከተሳታፊዎች የቀረቡ ጥያቄዎችና ሐሳቦች ላይም ሰፊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን፣ በመጨረሻ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ካሳሁን ተገኘ የመዝጊያ ንግግር በማድረግ፣ የተገኘው ተሞክሮ ዩኒቨርሲቲው ወደ ራስ ገዝነት በሚያደርገው ጉዞ ጠቃሚ ግብዓት መሆኑን ገልጸው ፕሮፌሰር አበባው ይርጋንና ሁሉንም ተሳታፊዎች አመስግነዋል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለልህቀት እንተጋለን!
የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም | 2 966 |
| 13 | بدون متن... | 5 519 |
| 14 | بدون متن... | 1 |
| 15 | የመጽሐፍ ምረቃ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈባቸውን የታሪክ ውጣ ውረዶች እና ተቋማዊ የለውጥ ጉዞ በሰፊው የሚዳስስ ልዩ ታሪካዊ መጽሐፍ በዩኒቨርሲቲያችን ፕሬዚዳንት በዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን «ጽናት፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ» በሚል ርእስ ተጽፎ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የከተማችን ነዋሪዎች እና የዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብ አባላት በተገኙበት ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 በማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር የመሰብሰቢያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ ይመረቃል፡፡
በመሆኑም የዚህን ታሪካዊ መጽሐፍ ደራሲ እና የዩኒቨርሲቲያችን ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይንን በዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብ ስም እንኳን ደስ አለዎት ለማለት እንወዳለን!
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለልህቀት እንተጋለን!
የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም. | 5 467 |
| 16 | بدون متن... | 5 020 |
| 17 | بدون متن... | 3 569 |
| 18 | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ማዕከል ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በ"ማቲማቲክስና ኮዲንግ " ስልጠና መስጠት ጀመረ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ማዕከል በክረምት መርሐ ግብር ከጎንደር ከተማ አስተዳደር ለተመረጡ 17 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የ10ኛ እና 11ኛ ክፍል ተማሪዎች በማቲማቲክስ እና በኮዲንግ (Coding) ላይ ያተኮረ ተግባራዊ ስልጠና ከዛሬ ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም ጀምሮ መስጠት ጀምሯል።
ለአንድ ወር በሚቆየው በዚህ ስልጠና ላይ የሚሳተፉ ተማሪዎች፣ የንድፈ-ሀሳብና ተግባራዊ ትምህርቱን ከተከታተሉ በኋላ በቡድንም ሆነ በተናጠል ልዩ ልዩ የፈጠራ ፕሮጀክቶችን ሰርተው የሚያቀርቡ ሲሆን፣ በስኬት ለሚያጠናቅቁም የምስክር ወረቀት (ሰርተፊኬት) የሚሰጣቸው ይሆናል።
የመርሀ-ግብሩ መክፈቻ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አሳታፊነትና ኢንዱስትሪ ትስስር ዳይሬክተር ዶ/ር ክብሮም አዳነ እንደገለጹት፣ የስልጠናው ዋና ዓላማ ተማሪዎች የክረምት ዕረፍት ጊዜያቸውን አልባሌ ቦታዎች ላይ ከማሳለፍ ይልቅ በቴክኖሎጂና በፈጠራ እውቀት እንዲበቁ ማድረግ ነው ብለዋል።
ለአሰልጣኝነትም ተማሪዎችን በኮዲንግ እውቀት ብቁ ማድረግ የሚችሉ መምህራን ተመርጠው ወደ ሥራ መግባታቸውን አብራርተዋል።
በዕለቱ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዚዳንት ተወካይ ዶ/ር ውለታው መኩሪያው በበኩላቸው፣ ስልጠናው ተማሪዎች ቴክኖሎጂን በአግባቡና ለበጎ ዓላማ እንዲጠቀሙ የሚያስችላቸው መሆኑን ገልጸዋል።
አክለውም ተማሪዎች የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ በመጠቀም የታለመውን ዓላማ ማሳካት እንዳለባቸውና ይህም ወደፊት በሚዘጋጁ አህጉራዊና ሀገራዊ የቴክኖሎጂ ውድድሮች እንዲሁም ወርክሾፖች ላይ ለመሳተፍ ትልቅ እድል እንደሚፈጥርላቸው ተናግረዋል።
የሳይንስ ማዕከሉ አስተባባሪ አቶ ግርማ ወርቄ የማዕከሉን እንቅስቃሴ አስመልከተው በሰጡት ማብራሪያ፤ ማዕከሉ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ በደንብ ያልተደራጁ የትምህርት ቤት ቤተ-ሙከራዎችን በተንቀሳቃሽ ቤተ-ሙከራ (Mobile Lab) በመደገፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ሲያበረክት መቆየቱን ገልጸዋል።
በተጨማሪም ከመደበኛው የትምህርት ገበታ ጎን ለጎን ተማሪዎች ወደ ማዕከሉ በአካል እየመጡ ተግባራዊ ትምህርት እንዲወስዱና የፈጠራ ክህሎታቸውን እንዲያጎለብቱ ሁኔታዎች መመቻቸታቸውን ጠቁመው፣ በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ብቻ በስልጠናና በጉብኝት መርሃ-ግብሮች ከ900 በላይ ተማሪዎችና መምህራን የማዕከሉ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን አብራርተዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ማዕከል እንደነዚህ ያሉ ማህበረሰብ አቀፍ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ስራዎችን በማጠናከር የነገ ሀገር ተረካቢዎችን በሳይንስና ቴክኖሎጂ ለማብቃት የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተገልጿል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለልህቀት እንተጋለን!
የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ
ሀምሌ 12/2018 ዓ.ም | 3 667 |
| 19 | بدون متن... | 3 892 |
| 20 | ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስኮላርስ ፕሮግራም ጋር በትብብር የሚሰራው የአጋዥ ቴክኖሎጅ ማዕከል "Grand Assistive Technology Center" /GATC/ የጉብኝትና የስራ አፈፃፀም ሪፖርት መርሀ-ግብር ተካሄደ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በጎንደር ዩኒቨርሲቲና ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስኮላርስ ፕሮግራም ጋር በትብብር የሚሰራው የአጋዥ ቴክኖሎጅ ማዕከል "Grand Assistive Technology Center" /GATC/ የጉብኝትና የስራ አፈፃፀም ሪፖርት መርሀ-ግብር ሀምሌ 10/2018 ዓ.ም ፋሲለደስ ት/ቤት ጀርባ በሚገኘው የድርጅቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሂዷል።
መርሀ- ግብሩን በንግግር የከፈቱት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስኮላርስ ፕሮግራም ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ሞላልኝ በላይ ሲሆኑ ፣ “የማስተር ካርድ ስኮለርስ ፕሮግራም ከአጋዥ ቴክኖሎጂ ማዕከል "GATC" ጋር በትብብር እየሰሩ እንደሚገኙ ገልፀዋል።
በመሆኑም "Grand Assistive Technology Center" /GATC/ ማዕከል ባለፉት ሁለት አመታት የአካል ጉዳተኛ ህፃናት የህክምና ድጋፍና የህፃናት ማቆያ አገልግሎት ሲሰጡ ቆይተዋል ሲሉ ተናግረዋል ፤ ዳይሬክተሩ አክለውም የአካል ጉዳተኞች ድጋፍ ማምረቻ ወርክሾፕ ተገንብቶ በተግባር ለማዬትም ተችሏል ብለዋል።
ሌላው ደግሞ የአካል ጉዳተኛ ልጅ ያሏቸው ወላጆች የሚሰለጥኑበት የልብስ ስፌትና ማምረቻ ክፍል በጥሩ ሁኔታ ተዘጋጅቶ እጅግ በጣም ጠቃሚ ተግባራትን እየሰጠ የሚገኝ መሆኑን ለተሳታፊዎች አስረድተዋል፡፡
አቶ ዘላለም ደሳለኝ በጎንደር ከተማ "Grand Assistive Technology Center" /GATC/ ስራ አስኪያጅና የኦኮፔሽናል ቴራፒ መምህር “በጎንደር ከተማ በርካታ ህፃናት የአካል ጉዳተኛ መሆናቸውን የተረዳን በመሆኑ ይህን ማዕከል/ድርጅት መስርተን የተለያዩ ክፍሎችን አደራጅተን ወደ ስራ የገባን ሲሆን፣ መልካም የሚባል ውጤትንም እየተመለከትን ነው፡፡
ለምሳሌ የአካል ድጋፍ ማምረቻ ወርክሾፓችን በከፍተኛ ሁኔታ ስራ ሊሰራበት የሚችልና እንደ ሀገርም በዚህ ዘርፍ ብዙ ማምረቻ የሌለ በመሆኑ ስራውን አጠናክረን ስንቀጥል ለአካል ጉዳተኞች በቂ የአካል ድጋፍ መስጫዎችን ማምረት ያስችለናል በማለት አብራርተዋል ፡፡
በሌላ በኩል የልብስ ስፌት ማሰልጠኛና ማምረቻ ክፍላችን ለበርካታ የአካል ጉዳት ያለባቸው ወላጆች ስልጠና በመስጠትና የተወሰኑትን በማምረት ተግባሩ በመቅጠር እየተጠቀምንበት እንገኛለን” ብለዋል።
በዚህ መርሀ-ግብር ከጎንደር ከተማ የተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶችና የከንቲባ ጽ/ቤት በአጋር አካልነት በመገኘት የተለያዩ ገንቢ አስተያዬቶችን ሰጥተዋል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለልህቀት እንተጋለን!
የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ
ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም | 3 091 |
