University of Gondar (UoG)
University of Gondar is one of a pioneer public higher education institution with commendable achievements in teaching, research and community services.
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام University of Gondar (UoG)
تُعد قناة University of Gondar (UoG) (@uofgondar) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 242 مشتركاً، محتلاً المرتبة 13 965 في فئة التعليم والمرتبة 2 401 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 242 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 13 سبتمبر, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 554، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 18، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 27.35%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.60% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 895 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 221 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 11.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“University of Gondar is one of a pioneer public higher education institution with commendable achievements in teaching, research and community services.”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 14 سبتمبر, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 14 سبتمبر | +2 | |||
| 13 سبتمبر | +18 | |||
| 12 سبتمبر | +15 | |||
| 11 سبتمبر | +16 | |||
| 10 سبتمبر | +10 | |||
| 09 سبتمبر | +13 | |||
| 08 سبتمبر | +24 | |||
| 07 سبتمبر | +23 | |||
| 06 سبتمبر | +12 | |||
| 05 سبتمبر | +19 | |||
| 04 سبتمبر | +26 | |||
| 03 سبتمبر | +16 | |||
| 02 سبتمبر | +19 | |||
| 01 سبتمبر | +6 |
| 2 | 📢 ማስታወቂያ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቅድመ-ምረቃ የ18ቱም ዲፓርትመንት ነባር ተማሪዎች በሙሉ የ2019 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን መስከረም 6/2019 ዓ.ም. የሚጀምር ሲሆን ከዚህ ጋር ተያይዞ የተማሪዎች ምዝገባ መስከረም 4 እና 5/2019 ዓ.ም ይካሄዳል።
ስለሆነም የ18ቱም ዲፓርትመንት ነባር ተማሪዎች በተጠቀሱት ቀናት በአካል በመገኘት ምዝገባችሁን እንድታጠናቅቁ ኮሌጁ በአክብሮት ያሳስባል።
📅 የምዝገባ ቀን
መስከረም 4 እና 5/2019 ዓ.ም
🎓 የትምህርት መጀመሪያ ቀን
መስከረም 6/2019 ዓ.ም
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ
ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና አጠ/ስፔ/ሆስ | 2 898 |
| 3 | لا يوجد نص... | 3 081 |
| 4 | 🌼🌼🌼🌼🌼🌼 | 2 894 |
| 5 | لا يوجد نص... | 3 044 |
| 6 | لا يوجد نص... | 2 758 |
| 7 | የጎንደር ዩኒቨርሲቲና የጎንደር ግብርና ምርምር ማዕከል በትብብር ለመስራት የሚያስችላቸውና የምርምር ስራዎችን ለአርሶ አደሩ ህይወት ለማሻሻል የሚያሰችል አውደ ጥናት አካሄዱ ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና በጎንደር ግብርና ምርምር ማዕከል የጋራ ትብብር የተዘጋጀና የምርምር ውጤቶችን ወደ ህብረተሰቡ ማድረስ እንዲሁም የግብርና ምርምሮችን ወደ ገበያ ለመቀየር (Agricultural Research to Commercialization) ሂደቶች ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት ጳጉሜ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ህንፃ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሄደ።
በዚህ መርሃ ግብር ላይ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ዳንኤል ታደሰ፣ የጎንደር ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ ተስፋዬ እና የጎንደር ግብርና ምርምር ማዕከል ተመራማሪዎች ተገኝተዋል።
በዕለቱ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብዕ ኮሌጅ ዶ/ር ቴዎድሮስ ዘውዱ "Hunger is a Constitutional Injury" በሚል ርዕስ የምግብ ዋስትናን ከሰብአዊ መብትና ህጋዊ ማዕቀፍ አንፃር የዳሰሰ ጥናት አቅርበዋል ።
ከቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ አቶ ብርሃኑ ፀሐይ "Agricultural Entrepreneurial Mindset" በሚል ርዕስ ባቀረቡት ገለጻ አርሶ አደሮችም ሆኑ ተመራማሪዎች Entrepreneurial Mindset) ኖሯቸው የግብርና ስራዎችን አዋጭነትና ትርፋማነት እየገመገሙ በመስራት የማኅበረሰቡን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል እንደሚቻል በስልጠናው አስገንዝበዋል።
ከግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ የኮሌጁ ምክትል ዲን ዶ/ር ዳንኤል ንጉሴ "Agricutural Research to Commercialization" በሚል ርዕስ የግብርና ምርምር ውጤቶችን እንዴት ወደ ገበያና ንግድ ማሸጋገር እንደሚቻል ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎች በንድፈ-ሀሳብ የቀረቡትን ገለጻዎች ከተከታተሉ በኋላ ሰፊ ውይይት አድርገዋል።
የግብርና ምርምር ማዕከሉ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅን ልክ እንደ አይኑ ብሌን እያየው መሆኑን የገለፁት የማዕከሉ ዲይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ ተስፋዬ የምርምር ማዕከሉ ብቻውን ቢሰራ የሚያመጣው ለውጥ ጉልህ ባለመሆኑ ከዩኒቨርስቲው ጋር በጋራ በማቀድና በመተግበር ለአካባቢው ማህበረሰብ ተጨባጭ የሆነ ስራ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
ይህ የጋራ የምርምርና ስልጠና መርሃ ግብር በዩኒቨርሲቲው እና በምርምር ማዕከሉ መካከል ያለውን ቅንጅት ለማጠናከር እንዲሁም የምርምር ውጤቶች ከወረቀት ወጥተው የአርሶ አደሩን ህይወት እንዲቀይሩ ለማስቻል ትልቅ እቅስቃሴ መሆኑ ተገልጾ በምርምር ማዕከሉ ዳይሬክተር በዶ/ር ቴዎድሮስ ተሰፋዬ የመዝጊያ ንግግር መርሃ ግብሩ ተጠናቋል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለልህቀት እንተጋለን !
የህዝብና ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ
ጳጉሜ 5/2018 ዓ.ም | 2 576 |
| 8 | لا يوجد نص... | 3 166 |
| 9 | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ «ኅብር በተግባር» በሚል መሪ ቃል የሀገር አቀፍ የተማሪዎች ድጋፍ መርሃ ግብር አካሄደ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ጳጉሜ 4 ቀን 2018 ዓ.ም የጎንደር ዩኒቨርሲቲ «ኅብር በተግባር» እና «አንድ ተማሪ፣ አንድ ተስፋ» በሚሉ መሪ ቃሎች የ2018 ዓ.ም የጳጉሜ 4 «የኅብር ቀን» ሀገር አቀፍ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እና የተማሪዎች ድጋፍ መርሐ ግብር በደመቀ ሁኔታ አከናውኗል።
በዝግጅቱ ላይ የዩኒቨርሲቲው የፕሬዝዳንት ተወካይና የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ካሳሁን ተገኝ፣ የምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር አይንሸት አዳነ፣ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ጌታው ብርሃን፣ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ልዩ አማካሪ ዶ/ር መንግሥቱ ሙሉ፣ የጎንደር ከተማ ትምህርት መምሪያ ተወካይ አቶ ይርጋለም ተስፋዬ፣ ርእሳነ መምህራን ጥሪ የተደረገላቸው ወላጆችና ተማሪዎች ተገኝተዋል፡፡
በዕለቱም የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ማጠናከር፣ የማበረሰብ አቀፍ ድጋፎችን ማሳደግ እንዲሁም የአንድነትና የኅብረት እሴቶችን በተግባር ማሳየት የሚያስችሉ ልዩ ልዩ የተማሪዎች ድጋፍና የማኅበረሰብ አገልግሎት ስራዎች ተከናውነዋል።
ለተማሪዎችም የፖርሳ፣ የደብተር፣ የእስክርቢቶ የእርሳስ፣ የላፒስ፣ የሳሙና እና የሴቶች የንጽሕና መጠበቂያ ድጋፎች ተካሂደዋል፡፡
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ካሳሁን ተገኝ «አንድ ተማሪ፣ አንድ ተስፋ» የሚለው መሪ ቃል ተማሪዎችን በመደገፍ ነገን የተስፋና የነገ ሀገር ተረካቢ ዜጋ አድርጎ ለማነጽ ትልቅ ድርሻ እንዳለው ገልጸው፤ ዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ አቀፍ አገልግሎቱንና የበጎ ፈቃድ ስራዎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለአካዳሚው የሚያደርገው ብርቱ ጥረት በአንድ ቀን ጀምበር የተገኘ ሳይሆን ከምሥረታው ጀምሮ ያደገበት ባህል ነው፡፡ በትምህርት ቤቶች ግንባታ፣ በመማር ማስተማር ድጋፍ፣ በምርምርና በማኅረሰብ አገልግሎት የወገን አለኝታነቱ “ሀገር ያወቀው ጸሐይ የሞቀው” ሀቅ ነው፡፡
የዛሬው የተማሪዎች የትምህርት ግብዓት ድጋፍም የዚሁ አንድ አካል ነው በማለት የጎንደር ከተማ ትምህርት መምሪያ ተወካይ አቶ ይርጋለም ተስፋዬ ተናግረዋል፡፡
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለትምህርት የሚሰጠው ትኩረት ከትምህርት ቤት ግንባታ ጀምሮ፣ የትምህርት ማበልጸጊያ ስልጠና፣ የርእሳነ መምህራን እና መምህራን ሥልጠና በአጠቃላይ ከቁሳዊ ሃብት እስከ አካዳሚያዊ ዕውቀት በመቸር ለወገን አለኝታ በመሆኑ በእኔና በትምህርት መምሪያው ስም ከፍ ያለ ምስጋና ሳቀርብ ዛሬም ዘወትርም የዚህ ዓይነቱ ድጋፍ እንደማይለየን በማመን ነው በማለት አቶ ይርጋለም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ድጋፍ የተደረገላቸው የጻድቁ ዮሐንስ እና የአቢዮት ፍሬ ርእሳነ መምህራን በበኩላቸው ለተደረገው የትምህርት ግብዓትና የሴቶች ንጽሕና መጠበቂያ በችግር ምክንያት ትምህርታቸውን ሊያቋርጡ ለነበሩ ችግረኛ ተማሪዎች አለኋችሁ የሚያስብል በመሆኑ በተማሪዎችና በትምህርት ቤቱ ስም ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በዛሬው ዕለትም በቁጥር 407 ለሆኑ፣ ለጻድቁ ዮሐንስ፣ ለአቢዮት ፍሬ፣ ለሎዛ ማርም እና ለአዘዞ መለስተኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል፡፡
ተማሪዎቹ የአካል ጉዳት ያለባቸው፣ እናት አባት ያጡና የሚረዳ የሌላቸው ሲሆኑ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ያደረገላቸውን የወላጅነት ስሜት አውስተው፣ ከድጋፉ በተጨማሪ ለትምህርታቸው የሥነ ልቦና ስንቅ እንደሚሆናቸው ጭምር በመግለጽ ዩኒቨርሲቲውን በታላቅ አክብሮት አመስግነዋል፡፡
በአጠቃላይ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ባሻገር በክረምት የበጎ አድራጎት ተግባራትን አጠናክሮ እየሠራ ሲሆን በያዝነው ክረምትም የዩኒቨርሲቲው ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የጤና ምርመራ፣ የአልባሳት ድጋፍ፣ የማዕድ ማጋራት እና ከዚሁ ጋር የተያያዙ የበጎ አድራጎት ተግባራትን አከናውኗል፡፡
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለልህቀት እንተጋለን !
የህዝብና ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም | 3 169 |
| 10 | لا يوجد نص... | 3 444 |
| 11 | لا يوجد نص... | 1 |
| 12 | University of Gondar Holds Strategic Discussions with VCU
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
The University of Gondar (UoG), Ethiopia, and Virginia Commonwealth University (VCU), USA, held a virtual strategic discussion on September 8, 2026, following the signing of a Memorandum of Understanding (MoU).
The discussion, attended by UoG President Dr. Yechale Kebede and his team alongside VCU counterparts, focused on collaboration in mental health education, research, and capacity building.
Both institutions reaffirmed their commitment to strengthening and sustaining the partnership, while also exploring additional areas of collaboration in public health and rehabilitation.
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
Devoted to Excellence!
Public Relations and Communucation Executive
September 9, 2026 | 3 480 |
| 13 | لا يوجد نص... | 7 831 |
| 14 | University of Gondar Delegation Participates in Sustainable Watershed and Resource Management Workshop in Austria
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
A delegation from the Institute of Technology at the University of Gondar has concluded a two-week scientific workshop at BOKU University in Vienna, Austria.
The workshop, which ran from August 3 to August 14, 2026, marks a significant milestone in international academic collaboration for sustainable resource management.
The session is a core component of the SWARM2 project (Sustainable Watershed and Resources Management through shared local wisdom, Advanced Research and Mobility).
Financed by the Austrian OeAD, SWARM2 operates as a joint initiative between BOKU University and the University of Gondar to address critical environmental and water challenges.
This follow-up meeting builds on the momentum of the project's initial kickoff workshop held in April 2026 at the ILRI campus and Capital Hotel in Addis Ababa, Ethiopia.
During the April sessions, the joint team laid the groundwork for their collaboration by designing research blueprints, planning joint fieldwork campaigns, meeting with Austrian Development Agency (ADA) representatives, and establishing concrete protocols for soil and water sampling in the Ribb watershed.
While the first workshop focused on logistical planning, the recent two-week event in Vienna centered on deep scientific integration.
The Ethiopian delegation engaged directly with BOKU University research partners, evaluated advanced scientific facilities, and accelerated joint research frameworks.
The team toured BOKU’s international relations office, the Cluster for Development Research, the hydraulic lab infrastructure, the forest research station, and the specialized erosion research station.
In a practical boost to the partnership's research capabilities, BOKU University has temporarily transferred a specialized scientific instrument to the University of Gondar.
The device is designated for exclusive, time-limited use within the technology institute's experimental framework to monitor chlorine concentration in potable water.
The international initiative is organized under the joint leadership of Ass. Prof. Dipl.-Ing. Dr. Stefan Strohmeier from BOKU’s Institute of Soil Physics and Rural Water Management (SoPhy), and Dr. Abebe Worku Mekonnen, Assistant Professor of Civil Engineering and Scientific Director of the Technology Institute at the University of Gondar.
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
Devoted to Excellence!
Public Relations and Communications Executive
August 31, 2026 | 6 340 |
| 15 | لا يوجد نص... | 6 092 |
| 16 | لا يوجد نص... | 5 958 |
| 17 | The workshop also featured presentations and extensive discussions on key achievements and lessons learned in the area of e-learning; the reasons why instructors and students may be reluctant to engage in online and blended learning and possible solutions; strengthening digital assessment and academic management capacity through Moodle; and the challenges encountered and solutions identified in the process of delivering blended courses at the University of Gondar.
Research findings and experience-sharing papers were presented on these topics, followed by in-depth discussions.
Dr. Yechale Kebede, President of the University of Gondar, highlighted the significant importance of digital technology to the University in two major ways.
First, it provides an opportunity to support the country’s ongoing efforts to ensure that its overall development is increasingly driven by technology. Second, it offers the University an opportunity to strengthen its position in e-learning and create a more accessible and inclusive teaching and learning environment.
The workshop underscored the need to build a strong digitalization ecosystem encompassing leadership, policy, infrastructure, and academic departments; establish systems that safeguard the quality of education; achieve the University’s vision; and make a significant contribution to the successful implementation of Digital Ethiopia 2030.
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
Devoted to Excellence!
Public Relations and Communications Executive Office
August 28, 2026 | 4 145 |
| 18 | በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የኢ-ለርኒንግ አውደ ጥናት ተካሄደ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስኮላርስ ፕሮግራም አዘጋጅነት «Transforming Teaching and Learning through Digital Technology at the University of Gondar: Experiences, Innovation, Challenges and Opportunities» በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የኢ-ለርኒንግ አውደ ጥናት ነሀሴ 21/2018 ዓ.ም በዘርዓያቆብ አዳራሽ ተካሂዷል።
በዚህ አውደ ጥናት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደን ጨምሮ፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ ዲኖች፣ ዳይሬክተሮች፣ በአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ በኦንላይን ትምህርታችውን እየተከታትሉ የሚገኙ 36 የጎንደር ዩኒቨርሲቲ መምህራን፣ ተማሪዎችና የቀደሞው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕ/ር መንገሻ አድማሱ ተገኝተዋል፡፡
አውደ ጥናቱ ቀደም ሲል በዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ በአካቶ ትምህርት እና በሰውሰራሽ አስተውሎት ዙሪያ የተሰጡ ስልጠናዎችን እንዲሁም የተዘረጉ መሰረተ ልማቶችን በመጠቀም የመማር ማስተማር ሂደቱን ትራንስፎርም ለማድረግ ያለመ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም በተናጠል ይከናወኑ የነበሩ አሰራሮችን ወደ አንድ በማምጣትና የተቀናጀ ተቋማዊ መልክ በመስጠት፣ በተለያዩ ምክንያቶች በአካል ተገኝተው መማር ለማይችሉ የማህበረሰብ ክፍሎች ትምህርትን አካታች በሆነ መልኩ በኦንላይን ተደራሽ ማድረግ የአውደ ጥናቱ ዋና አላማው መሆኑን በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስኮላርስ ፕሮግራም ዳይሬክተር ዶ/ር ሞላልኝ በላይ ተናግረዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የዩኒቨርሲቲው አይሲቲ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ተስፋሁን መለሰ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ያሉ የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶችን በተመለከተ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን፤ የኢ-ለርኒንግ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አበበ አለሙ በበኩላቸው በዩኒቨርሲቲው ከኢለርኒግ ጋር በተያያዘ እየተሰሩ ያሉ ሰራዎቸን በተለይ ደግሞ በትምህርት ሚኒስቴር የተዘረጋውን የ eSHE (eLearning to Strengthen Higher Education) ፕሮጀክት አፈጻጸምን በተመለከተ ገለጻ አድርገዋል።
በአውደ ጥናቱ ላይበኢ-ለርኒንግ ዘርፍ የተመዘገቡ አበይት ውጤቶችና የተቀሰሙ ልምዶች፣ መምህራንና ተማሪዎች ከበይነ-መረብና ቅይጥ (Blended) ትምህርት ለመሸሽ የሚያቀርቧቸው ምክንያቶችና የመፍትሔ አቅጣጫዎች፣ የዲጂታል ምዘናንና የአካዳሚክ አስተዳደርን አቅም በሙድል ማጠናከር፣በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ኮርሶችን ቀላቅሎ በመስጠት ሂደት ያጋጠሙ እንቅፋቶችና መፍትሔዎቻቸው ላይ የጥናትና የልምድ ልውውጥ ጽሁፎች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደ ዲጂታል ቴክኖሎጂ ለዩኒቨርሲቲው በሁለት ዋና ዋና መንገዶች ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል። የሀገራችን ሁለንተናዊ እድገት በቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆን እየተደረገ ያለውን ጥረት ለመደገፍ እና ዩኒቨርሲቲውን በ የኢ-ለርኒንግ የተሻለ ቦታ ላይ በማድረስ ተደራሽ እና አካታች የመማር ማስተማር ከባቢን ለመፍጠር ዕድል ይሰጣል ብለዋል።
በመጨረሻም አመራርን፣ ፖሊሲን፣ መሰረተ ልማትንና ዲፓርትመንቶችን ያካተተ ጠንካራ ዲጂታላይዜሽን ኢኮ-ሲስተም በመገንባት፣ የትምህርት ጥራቱን የጠበቀ አሰራር በመዘርጋት የዩኒቨርሲቲውን ራእይ ማሳካትና ለሀገሪቱ የዲጂታል 2030 ስኬት የጎላ አስተዋጽኦ ማበርከት እንደሚገባ ተመላክቷል።
ለልህቀት እንተጋለን!
የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ
ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
eLearning Workshop Held at the University of Gondar
The Mastercard Foundation Scholars Program at the University of Gondar hosted an e-learning workshop under the theme “Transforming Teaching and Learning through Digital Technology at the University of Gondar: Experiences, Innovation, Challenges and Opportunities” on August 27, 2026 at the Zerayakob Hall.
The workshop was attended by the President of the University of Gondar, Dr. Yechale Kebede, vice presidents, deans, directors, academic staff members currently pursuing online studies at Arizona State University, students, and former University of Gondar President Professor Mengesha Admasu.
The workshop aimed to transform the teaching and learning process by building on previous trainings provided in digital technology, inclusive education, and artificial intelligence, as well as the digital infrastructure that has been established. It also sought to bring together initiatives that had previously been implemented separately and provide them with an integrated institutional framework. The main objective was to make education more inclusive and accessible for members of the community who are unable to attend in-person classes for various reasons.
In his remarks, Dr. Molalign Belay, Co-Director of the Mastercard Foundation Scholars Program at the University of Gondar, emphasized the importance of creating an integrated approach to e-learning and expanding access to education through digital platforms.
During the program, Dr. Tesfahun Melese, Director of the University’s ICT Directorate, provided an overview of the technological infrastructure available at the University of Gondar. Mr. Abebe Alemu, Director of the E-Learning Directorate, also presented an update on the University’s ongoing e-learning activities, with particular emphasis on the implementation of the eSHE (eLearning to Strengthen Higher Education) project launched by the Ministry of Education. | 3 860 |
| 19 | لا يوجد نص... | 4 592 |
| 20 | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሳሳካዋ አፍሪካ አሶሴሽን (Sasakawa Africa Association) ከተባለ ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ፡፡
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የመግባቢያ ሰነዱን የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደ እና ዶ/ር ኤርምያስ አባተ የሳሳካዋ አፍሪካ አሶሴሽን (Sasakawa Africa Association) ምክትል ዋና ዳይሬክተር ጋራ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ህንፃ ዛሬ ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም. ተፈራርመዋል፡፡
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደ በጋራ መግባቢያ ሰነድ ፊርማ ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለፁት የሳሳካዋ አፍሪካ አሶሴሽን ከዚህ ቀደም በርካታ ተግባራትን ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ ሲያከናውን የቆዬ ቢሆንም ዛሬ ግን የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ወደ ራስ ገዝነት በምናደርገው ጉዞ በአቅም ግንባታ እና በተለያዩ የልማት መስኮች በአጋርነት ትውልድን የሚጠቅምና በግብርናው ዘርፍ ውጤታማ የሚያደርግ ተግባራትን በጋራ እናከናውናለን ብለን ተስፋ እናደርጋለን ብለዋል፡፡
የሳሳካዋ አፍሪካ አሶሴሽን (Sasakawa Africa Association) ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኤርምያስ አባተ በበኩላቸው ሳሳካዋ አፍሪካ በኢትዮጵያ የግብርና ኤክስቴንሽን፣ የምግብ ዋስትና እና ዘላቂ የግብርና ስልጠናዎችን ሲሰጥ የቆየ ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የግብርናው ዘርፍ የማይተካ ሚና ያለው ዘርፍ መሆኑን እና ዛሬ የምንሰራው ስራ ሁሉ ከተፈጥሮ ሀብት ጋር የሚጋጭና አጥፊ እንዳይሆን መጠንቀቅ ይገባናል ብለዋል፡፡
ሳሳካዋ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ በመስራት የአርሶ አደራችን ህይወት ለመለወጥ የአቅማችን እገዛ እናደርጋለን ሲሉ ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡
በግብርና ሚኒስቴር የእርሻና ሆርቲካልቸር ኤክስቴንሽን መሪ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ የኔነሽ ኢጉ እንደገለጹት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ እጅግ ትልቅ ተቋም መሆኑን ጠቅሰው የዛሬው የመግባቢያ ሰነድም ከዚህ በፊት ሲሰሩ ከነበሩት ተግባራት በተሻለና በላቀ ደረጃ ውጤታማ ለማድረግ እንደ ግብርና ሚኒስቴር የሚጠበቅብንን ድጋፍ እንደምናደርግ ቃል እንገባለን ብለዋል፡፡
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ካሳሁን ተገኘ በበኩላቸው ሰነዱ ዩኒቨርሲቲያችንና የሳሳካዋ አፍሪካ አሶሴሽን ሀገራችን ለምትጠብቀው የግብርና እድገት ወሳኝ ሚና እንዲጫወቱና የኤክስቴንሽን ሰራተኞችን ትምህርት ከፍ በማድረግ ግብርናውን እንዲደግፉ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡
የግብርና እና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ዳንኤል ታደሰ በሁለቱ ተቋማት የሚፈጠረው ትብብር በግብርና ልማት፣በእውቀት ሽግግር እና በአቅም ግንባታ ዘርፍ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚያስገኝ አስረድተዋል፡፡
በጋራ መግባቢያ ሰነዱ ፊርማ ላይ ዲኖች፣ ዳይሬክተሮች፣ ተመራማሪዎች እና መምህራን ተገኝተዋል፡፡
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለልህቀት እንተጋለን!
የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ
ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም | 3 921 |
