fa
Feedback
🌔የቀልብ ዶክተር🌔 طبيب القلب📿

🌔የቀልብ ዶክተር🌔 طبيب القلب📿

رفتن به کانال در Telegram

(إِنَّا فَتَحْنَا لَكَ فَتْحًا مُّبِينًا) #ጥቅማችን_ጀነት_ጥቅማችን_የአላህ_ውዴታ_ነው #ያስገኘንም_አላህ_እኛም_የርሱ_ባሮች_ሙስሊሞች_ነን👈 ዌብሳይት 👉 https://qalebdoctor.com ለህክምና 👉 @freeeeeeeeeeeere ወይም @UstazulQallb ያናግሩ #እያንዳንዱ_ቤት_እንገባለን_ኢንሻአሏህ! ☄️ #የውሾች_ጩሀት_የአንበሳውን_ጉዞ_አያስተጓጉልም

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام 🌔የቀልብ ዶክተር🌔 طبيب القلب📿

کانال 🌔የቀልብ ዶክተር🌔 طبيب القلب📿 (@qallbdoc) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 40 554 مشترک است و جایگاه 436 را در دسته پزشکی و رتبه 807 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 40 554 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 12 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -1 220 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -26 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 3.99% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 2.16% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 1 620 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 878 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 10 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
(إِنَّا فَتَحْنَا لَكَ فَتْحًا مُّبِينًا) #ጥቅማችን_ጀነት_ጥቅማችን_የአላህ_ውዴታ_ነው #ያስገኘንም_አላህ_እኛም_የርሱ_ባሮች_ሙስሊሞች_ነን👈 ዌብሳይት 👉 https://qalebdoctor.com ለህክምና 👉 @freeeeeeeeeeeere ወይም @UstazulQallb ያናግሩ #እያንዳንዱ_ቤት_እንገባለን_ኢንሻአሏህ! ☄️ #የውሾች_ጩሀት_የአንበሳውን_ጉዞ_አያስ...

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 13 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته پزشکی تبدیل کرده‌اند.

40 554
مشترکین
-2624 ساعت
-2617 روز
-1 22030 روز
آرشیو پست ها
🏴 #ቪድዮውን_ሳያዩ_ለህክምና_እንዳይመጡ 🔸አዎ የዳኑ ሁሉ እየመሰከሩ ነው🔸 💡💡لا غالبَ إلا الله💡💡 💠ቻናላችንን ለኡማው ያስተዋውቁ 👇 ⭐️     https://t.me/Qallbdoc ህክምና ለማግኘት👇 https://t.me/freeeeeeeeeeeere 👆 ህክምና ለማግኘት👇 https://t.me/UstazulQallb 👆 ዌብሳይት (ድህረ ገፅ) 👇 📱 https://qalebdoctor.com

  ✅ብርሀኔ ጠፋችብኝ ፍቅሬን ነጠቁኝ!! ክፍል 10 ‹በቃኝ› አልኩ ‹እሷን ገድዬም ቢሆን እጄን ለመንግስት እሰጣለሁ› ብዬ ዱላ ይዤ እህቷ ቤት ሄድኩ፡፡ በራቸውን ሰበርኩ የግቢያቸውን፡፡ ውስጥ ገብቼ በራቸውን ገነጠልኩኝ፡፡፡ ይህን ሁሉ ሳደርግ ቤቷ ውስጥ ያሉ እቃዎች መስኮቶቿን ስሰባብር አንድም ሰው ዝር አላለም፡፡ አዳሯን ልታስደግም ጠንቋይ ዘንድ አድራ ይሆናል ፡፡ ብጣራ ማንም አቤት የሚል ጠፋ በዛ ለሊት፡፡ እስካሁን ምን ይቆጭሃል ብባል ቤቷን ያኔ በእሳት አለማያያዜ፡፡ በዚያች ምሽት ጠላቶቻችን ምን ያህል ጨካኝና ሰብአዊነት የሌላቸው መሆናቸውን ይበልጥ ተረዳሁ። የገዛ እህት እንዲህ ዓይነቱን አስፈሪ ስቃይ በገዛ ደሟ ላይ ስታደርስ እንዴት ሕሊናዋ እረፍት እንደሚያገኝ ማሰብ አልቻልኩም ነበር። ያ የክፉው ሳቅ በሕይወቴ ውስጥ ካጋጠሙኝ አስፈሪ ድምፆች መካከል አንዱ ሆኖ ተመዝግቧል። በቤታችን ላይ ያለው የጭለማ መጋረጃ ሙሉ በሙሉ ወረደ። አሁን እኛ የተለመደውን የሰው ልጅ ሕይወት መኖር አቁመናል። ቀናቱ በሙሉ በጭጋግና በጭለማ የተሞሉ ነበሩ። የፀሐይ ብርሃን እንኳ ወደ ቤታችን ሲገባ የብርሃንነቱ ስሜት አይሰማንም ነበር። እህትየው ቤቷ ስትደርስ እቃዎቿ በሙሉ ተሰባብሮ አገኘች፡፡ ፖሊስ ዘንድ ‹ኡኡ› ብላ ‹እጠረጥረዋለሁ› ብላ ለሶስት ቀንም አሳስራኛለች፡፡ ግን መረጃ ሲያጡ እኔን ለቀቁኝ፡፡ እንደውም ለመርማሪው ‹ከለቀቃቹኝ እገላታለሁ› አልኩት፡፡  ብስጭት ላይ መሆኔ ገብቶት ‹ለሚስትህ ስትል ያን አታደርገውም ጥሩ ሰው እንደሆንክ ፊትህ ያስታውቃል ለአላህ ስትል ይቅር በላት አለኝ ፡፡› ካፊር ሁኖ ይቅርታን ያወቀ ሰው ሙስሊም ሁና እህቷ ላይ ምን አይነት አስነዋሪ ነገር እንዳደረገች አስቡት፡፡ ከዛ ግዜ ኋላ ባለቤቴ ሙሉ በሙሉ ከአልጋ መነሳት አቅቷታል ዓይኖቿ ተዘግተዋል። እኔም ቢሆን በአካልና በመንፈስ እጅግ የደከምኩ ሆንኩ።  ጎረቤቶቻችን እኛን እንደ ጨለማ ፍጡራን አይተውናል ዘመዶቻችንም ቢሆኑ ከእኛ ርቀዋል። እኔና ባለቤቴ ግን በዚያ በወረደው የጭለማ መጋረጃ መሃል እጆቻችንን አጥብቀን እንደያዝን ነበርን። "… ምንም ቢፈጠር… እወድሃለሁ…" ይህች የባለቤቴ የመጨረሻ የንቃተ ህሊና ቃል ነበረች። ከዚያ በኋላ ወደ ከባድ ኮማ መሰል እንቅልፍ ውስጥ ገባች። የጭለማው መጋረጃ ህይወታችንን ሙሉ በሙሉ የሸፈነበትና ወደ ይበልጥ አስፈሪው የፈተና ክፍል የተሻገርንበት ምዕራፍ ነበረ። የባለቤቴ ሁኔታ ወደ ከፋ ደረጃ ከተሸጋገረ በኋላ በቤታችን ውስጥ ያለው ስቃይ አዲስ መልክ ያዘ። አሁን ህመሙ ዝም ብሎ የአካል መዛል ሳይሆን እጅግ የሚያንቆራጥጥና የሚሰባብር    🔸አዎ የዳኑ ሁሉ እየመሰከሩ ነው🔸 💡💡لا غالبَ إلا الله💡💡 💠ቻናላችንን ለኡማው ያስተዋውቁ 👇 ⭐️ https://t.me/Qallbdoc ህክምና ለማግኘት👇 ✈️https://t.me/freeeeeeeeeeeere 👆 ህክምና ለማግኘት👇 ✈️https://t.me/UstazulQallb 👆 ዌብሳይት (ድህረ ገፅ) 👇 📱 https://qalebdoctor.com

🔻ፉዞ ሲህር 🔹 ይህ እንደ ስሙ አንድን ተጠቂ ፉዞ የሚደርግ ሲህር ነው፡፡ ምልክቶቹ🔹 1🔹#የታማሚው_ እሳቤ_ከቀን ወደ ቀን እየቀነሰ መምጣት ፡፡ አንድ ሲደመር አንድ እንኳ ሁለት መሆኑን አለመረዳት እስኪችል ድረስ፡፡ 2🔺#ቀላል_ያልሆነ_ድብት፡፡ ይህ ድብርት ሙሉ በሙሉ ሰውነቱን ይቆጣጠረዋል፡፡ መጨነቅ መጠበብ ቁርምት ብሎ መቀመጥ፡፡ 3🔻#ልክ_ባልሆነ_ፍጥነት_ነገሮችን ቶሎ መርሳት፡፡ ለነገሮች ያለን ትኩረት መጥፋት፡፡ አሁን የተነገረን ነገር ይረሳናል፡፡ 4🔹#ብዛት_ያለው_የፀጉር_መነቃቀል ፡፡ ይህ ም የቀን ተቀን እውነታ ይሆናል፡፡ 5🔺#ዶክተር_የሚለየው_ሴት ከሆነች የጡት አካባቢ ውጋት ወንድ ከሆነ የብልት ኣካባቢ ህመም ይኖራቸዋል፡፡ 6🔻#ክፉ_ፍራቻ_እውቀት_ያላቸውን አውጥተው አለማካፈል፡፡ እጅግ መፍራት፡፡ እነርሱ የያዙት እውቀት ውሸት እስኪመስላቸው ድረስ፡፡ 7🔹#ተዘጋጅተው_እንኳ_በህይወታቸው ሰው ፊት ቁሞ ማውራትን መፍራት፡፡ የሚያቁትም ሰው ዘንድ ። ጥያቄ ሲጠየቁ ድንግጥ ማለት፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን አጠገባቸው ኮሽ ሲል መበርገግ፡፡ 8🔻#ርዝቃቸውን_እስከማሳጣት የሚያደርስ_እንቅልፍ_ቢተኙ ቢተኙ አለመጥገብ፡፡ ከአልጋ መነሳትን መጥላት፡፡ 9🔺ብርሃን ቤታቸው ሲገባ ወይም የፀሀይን ብርሃን ሲያዩ እራሳቸውን ለማጥፋት መመኘት ፡፡ ተስፋ ሙሉ ለሙሉ መቁረጥ፡፡ 🕯🕯🕯🕯🕯ህክምናው🕯🕯🕯🕯🕯 ከ 2 ወይ ከ3 በታች ላለባቸው 1.ወደ አሏህ ሙሉ ለሙሉ መቃረብ 2.ለይልን በአግባቡ ሰግዶ ዱአእ ማድረግ 3.አታክልት በብዛት መመገብ 4.አያተል ኩርሲን እና ሙአወዘተይን ማብዛት #ፈጥነው_ይታከሙ_በቶሎ_ይዳኑ አዎ የዳኑ ሁሉ እየመሰከሩ ነው🔸 💡💡لا غالبَ إلا الله💡💡 💠ቻናላችንን ለኡማው ያስተዋውቁ 👇 ⭐️ https://t.me/Qallbdoc ህክምና ለማግኘት👇 ✈️https://t.me/freeeeeeeeeeeere 👆 ህክምና ለማግኘት👇 ✈️https://t.me/UstazulQallb 👆 ዌብሳይት (ድህረ ገፅ) 👇 📱 https://qalebdoctor.com

🎧ይህን ካለ.....¿ ከታላቁ ወንጀል ከውጊያ ቢሸሽ እንኳ፣ምሕረት ተደርጎለታል፣.......❔❔ 🤲🤲🤲🌗 https://t.me/Qallbdoc  ┄┄┉┉✽»🌹 ┄┄┉┉✽»🌹https://t.me/dr_of_heart

🖌ነቢዩ ሙሐመድ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ​"ክፉ (አመጸኛ) ባሪያ ማለት እርሱ (በሚሞትበት ጊዜ) ሰዎቹ፣ ምድሪቱ፣ ዛፎቹና እንስሳቱ ጭምር ከእርሱ ጥቃትና በደል አርፈው እፎይታን የሚያገኙበት ሰው ነ
🖌ነቢዩ ሙሐመድ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ​"ክፉ (አመጸኛ) ባሪያ ማለት እርሱ (በሚሞትበት ጊዜ) ሰዎቹ፣ ምድሪቱ፣ ዛፎቹና እንስሳቱ ጭምር ከእርሱ ጥቃትና በደል አርፈው እፎይታን የሚያገኙበት ሰው ነው።" https://t.me/Qallbdoc  💻┄┄┉┉✽» ┄┄┉┉✽»💻https://t.me/dr_of_heart

  ✅ብርሀኔ ጠፋችብኝ ፍቅሬን ነጠቁኝ!! ክፍል 9 በአካባቢው ያሉ ሰዎችን በመጠየቅ አንድ ታዋቂ የሩቅያ ኡስታዝ ወደ ቤታችን እንዲመጣ ጋበዝኩ። ኡስታዙ ወደ ቤቱ ሲገባ ድባቡ በጣም ከበደው። "ይህ ቤት ውስጥ በጣም ከባድ የሆነ የጥቁር መተት ስራ አለ" አለ ወዲያውኑ። ባለቤቴ ላይ ሩቅያ መቅራት በጀመረበት ወቅት ክስተቱ ፍጹም አስፈሪ ሆነ። ባለቤቴ በአራት ወንዶች ሊያዙ የማይችል ታላቅ ኃይል አገኘች። ትጮኽ፣ ትወራጨው ኡስታዙን ለመምታት ትሞክር ነበር።  በውስጧ ያለው ጂኒ በእሷ አንደበት ሆኖ "ይህች ሴት የእኛ ናት! እህቷ ለእኛ አሳልፋ ሰጥታታለች! አንለቃትም!" እያለ ይዝት ነበር። ኡስታዙ ለሰዓታት ያህል በፅናት ቢቀራም ድግምቱ ከቤተሰቦቿ (ከሳሂር ወላጆቿ) ጋር የተያያዘ ስለሆነ በጣም ውስብስብ መሆኑን ነገረኝ። " እህቷ በየቀኑ ድግምቱን ታድሰዋለች። ከፍተኛ ትግልና ፅናት ይጠይቃል" በማለት ጥቂት የታጠበ ውሃና ዘይት ሰጥቶን ሄደ። ይህ የመጀመሪያው የሩቅያ ሙከራ የችግሩን ስፋትና ጥልቀት ይበልጥ ያሳየን እንጂ ፈጣን መፍትሄ ሊሰጠን አልቻለም። አሁን ያለኝ ንብረት በሙሉ ተሟጠጠ። መኪናዬን በዝቅተኛ ዋጋ ሸጥኩት። የቢሮዬን እቃዎች በሙሉ ለዕዳ መክፈያ ሰጠኋቸው። በአንድ ወቅት ስኬታማ የነበርኩት ሰው አሁን ለቤት ኪራይ መክፈያ የሚሆን ገንዘብ አጥቼ በባለቤቱ ፊት የምንገላታ ደካማ ሆንኩ። ይህ የኢኮኖሚ ውድቀት ስነ-አእምሮዬን ክፉኛ ነካው። ለባለቤቴ የሚሆን የተመጣጠነ ምግብ እንኳ መግዛት አልቻልኩም። እሷ በአልጋ ላይ ሆና " ስለ እኔ ብለህ ንብረትህን በሙሉ አጣህ… እኔን ትተኸኝ ብትሄድ ይሻል ነበር" እያለች በቁጭት ትናገራለች። እኔ ግን የእጆቿን መዳፍ እየሳምኩ "ገንዘብ ይመጣል ያንቺ ጤንነት ግን በምንም አይተካም" እላት ነበር። ነገር ግን በውስጤ ያለው ጭንቀትና ፍርሃት ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መጣ። አበዳሪዎች በየቀኑ ስልኬ ላይ ይደውላሉ ቤታችን ደጃፍ ላይ መጥተው ይጮኻሉ። የክፋቱ ኃይል እኛን በበሽታ ብቻ ሳይሆን በረሃብና በውርደትም ጭምር ለመግደል የወሰነ ይመስል ነበር። አንድ ቀን ምሽት ባለቤቴ እጅግ በጣም ከባድ በሆነ የህመም ስሜት ውስጥ ሆና ሳለ በድንገት ድምጿ ተቀይሮ ታላቅና አስፈሪ ሳቅ መሳቅ ጀመረች።  ያ ሳቅ የሷ ሳይሆን በውስጧ ያለው የክፉው ኃይል ሳቅ ነበረ። "አብዱል ሀኪም! ምንም ያህል ብትሞክር አታሸንፈንም! እህቷ እኛን ልካናለች ህይወታችሁን እናጠፋዋለን!" እያለ ይጮኽ ነበር። ያ ሳቅ በቤቱ ግድግዳዎች ላይ እያስተጋባ አእምሮዬን ሊያሳብደው ደረሰ። እጆቼን በጆሮዎቼ ላይ ጭኜ "ያ አላህ! እርዳኝ!" እያልኩ እጮኽ ነበር። የክፉው ሳቅ የእኛን ተስፋ መቁረጥ የሚመኝ የእኛን መሸነፍ የሚያበስር ሸይጣናዊ ድምፅ ነበረ።      🔸አዎ የዳኑ ሁሉ እየመሰከሩ ነው🔸 💡💡لا غالبَ إلا الله💡💡 💠ቻናላችንን ለኡማው ያስተዋውቁ 👇 ⭐️ https://t.me/Qallbdoc ህክምና ለማግኘት👇 ✈️https://t.me/freeeeeeeeeeeere 👆 ህክምና ለማግኘት👇 ✈️https://t.me/UstazulQallb 👆 ዌብሳይት (ድህረ ገፅ) 👇 📱 https://qalebdoctor.com  

🏴 #ቪድዮውን_ሳያዩ_ለህክምና_እንዳይመጡ 🔸አዎ የዳኑ ሁሉ እየመሰከሩ ነው🔸 💡💡لا غالبَ إلا الله💡💡 💠ቻናላችንን ለኡማው ያስተዋውቁ 👇 ⭐️     https://t.me/Qallbdoc ህክምና ለማግኘት👇 https://t.me/freeeeeeeeeeeere 👆 ህክምና ለማግኘት👇 https://t.me/UstazulQallb 👆 ዌብሳይት (ድህረ ገፅ) 👇 📱 https://qalebdoctor.com

🏃 የንፋስ ሲህር (ጥንቆላዎች) ምልክቶች🏃 🖋በዶክተር አቡ ፈርሃን  ቢስሚላህ በዚያ ምድርን ያለምሶሶ ባኖረው ጨረቃንና ፀሃይን እንደየውበታቸው ላመላከተን ምድር ሰማይ ተራሮች ሊሸከሙት ያልቻሉትን ቁርአን ባወረደልን ጌታችን አላሁ ሱብሃነሁ ወተአላ ስም እጀምራለሁ፡፡ ምልክቶቹ  ክፍል 2 8. #የአናት_ቅላቸውን_እራሳቸውን በጣም ይበርዳቸዋል፡፡ አናታቸው ብዙ ግዜ በረዶ ሆኖ እግሮቻቸው እሳት ናቸው ይሞቃሉ፡፡ 9. #ቀላል_የማይባል ከጀርባ በኩላሊት ትይዩ ውጋት አለባቸው፡፡ ይህ ህመም ቅስፍ አድርጎ የሚይዝበት አጋጣሚ ሲኖር በሃኪም ደረጃም ጠጠርም ይሁን ምንም ነገር አይገኝባቸውም፡፡ 10. #ልክ_መሃል_እግራቸውን ተከትሎ ያቃጥላቸዋል ጀርባቸውን እንዲሁ!! ይህ ህመም ከምሽት ላይ ይበረታል፡፡ ብዙውን ግዜ ከጨጓራ ህመም ጋር ቢገናኝም እነኚህ ታማሚዎች ግን የጨጓራ ማስታገሻዎችን እንኳ ቢወስዱ ምልክቱ አይጠፋም፡፡ 11. #ብስናት_ብሎም_አክታቸው በጣም ይሸታል፡፡ ሽታው ያስታውቃል፡፡ ይህ በተለይ በጥዋቱ ክፍለ ግዜ በዝሁር ሰአትና ምሳቸውን ከበሉ ኋላ ይለያል!! 12. #ዶክተር_የማይቀርፈው_አፋቸውም ሽታ ጠአም አለው፡፡ ይህም ጠአም ቃናው ከምንም ይለያል፡፡ አፍ ሽታ ሁሉም የሰው ለጅ ላይ ያለ ቢሆንም በዚህ ሲህር የተጠቁ ሰዎች ግን አፋቸው በምንም ተአምር ቃናውን አይለውጥም !! 13. #ክፋ_መገጣጠምያ_ህመም። በርካታ አካላቶቻቸው ላይ ህመሞች ይበረታሉ፡፡ ዛሬ ቀኙን ነገ ግራውን እየተለዋወጠ ይይዘዋል፡፡  14. #ተግባራት_ላይ_ብሎም ትንሽ ሲራመዱ ድካም አለ፡፡ ይህም ሙሉ ለሙሉ ተስፋ ቆራጭ ሰዎች ሊያደርጋቸው ይችላል፡፡  15 #ርእሱን_ተከትለው_ሰርች በማድረግ ክፍል አንድም ያንብቡ #ፈጥነው_ይታከሙ_በቶሎ_ይዳኑ አዎ የዳኑ ሁሉ እየመሰከሩ ነው🔸 💡💡لا غالبَ إلا الله💡💡 💠ቻናላችንን ለኡማው ያስተዋውቁ 👇 ⭐️ https://t.me/Qallbdoc ህክምና ለማግኘት👇 ✈️https://t.me/freeeeeeeeeeeere 👆 ህክምና ለማግኘት👇 ✈️https://t.me/UstazulQallb 👆 ዌብሳይት (ድህረ ገፅ) 👇 📱 https://qalebdoctor.com

🌟እነሆ አመላካቾች እንጂ መሪዎች አደለንም 🌟እነሆ መካሪዎች እንጂ ነቃፊዎች አይደለንም 🌟እነሆ አስጠንቃቂዎች እንጂ አስገዳጆች አደለንም 👉አላማችን አንድም ቤት የአሏህን ስም ሳያነሳ ሳይዘክር ውሎ እንዳያድር ነው👈 👉እኛ የአቅማችንን እየጣርን ነው! እርሶስ? 👉ቤቶን በአሏህ ቃል የሚያበራ ያድርጉ 👉የታመመን ወደ ኛ ይምሩ የአፊያው ሰበብ ብንሆን እንጂ አዳኝ እንዳልሆንን ይጠቁሙ! 🌟ሲጨንቆት 🌟ሲፈሩ 🌟ሲጠቦት ያማክሩን          👉ይወቁ ሁሌም ከጎኖት ነን👈 🌟የውሻው ጩሀት የአንበሳውን ጉዞ አያስተጓጉልም🌟 የቴሌግራም አድራሻ👉 https://t.me/Qallbdoc https://t.me/dr_of_heart

​ሰኔና ሰኞ! ስንቱን ታዘባችሁ!? ​ለማጋለጥ ሳይሆን ለማስተማር በሚል መርህ፣ እስኪ በየቤታችሁ እንመልከት። ስንቱ ያማረ ልብስ ለብሶ፣ በነጠላ ተውቦ፣ ቂቤውን ተቀብቶ "ሲያንጓርር" አለፈ? ስንቱስ
​ሰኔና ሰኞ! ስንቱን ታዘባችሁ!? ​ለማጋለጥ ሳይሆን ለማስተማር በሚል መርህ፣ እስኪ በየቤታችሁ እንመልከት። ስንቱ ያማረ ልብስ ለብሶ፣ በነጠላ ተውቦ፣ ቂቤውን ተቀብቶ "ሲያንጓርር" አለፈ? ስንቱስ ከቤቱ ጠፍቶ ውሎ፣ አመሻሽቶ ወደ ቤቱ ገባ? ​ይህ ቀን እጅግ ልንጠነቀቅ የሚገባው፣ "ወሰን ገላ" የሚሰኝ ጂን የሚነግስበት ነው። የዛር መንፈስ ያላቸው ሰዎች ለዚህ መንፈስ ለመገበር የሚቆነጃጁበት፣ ጠንቋይ (ሷሂር) ዘንድ ድቤ የሚመቱበት ወቅት ነው። ስንቶቻችሁ ቤት በዚህ አጋጣሚ ጠንቋዮች መኖራቸውን አረጋገጣችሁ? ተጠንቀቁ! በዚህ ሰዓት በብዙ ሰዎች ላይ የቆየ ሲህር ይታደሳል። እነዚህ ጂኖች ስለሚገበርላቸው ጉልበታቸው ይበረታል፤ የሲህሩም ተፅዕኖ ይጠናከራል። ዛር ያለባቸውን ወደኛ በማምጣት፣ ህክምና በማድረግ እነዚህን የዛር ባሮች ከቀንበራቸው ማላቀቅ የግድ ነው። ​አላህ (ሱ.ወ) በቁርአን እንዲህ ይላል፡-
​"የሰሩትም የተንኮል ስራ (ሲህር) እንጂ ሌላ አይደለም። ጠንቋይም ከየትም በመጣ (በማንኛውም ቦታ) አይሳካለትም።" (ሱረቱ ጣሃ፡ 69)
​እንዲሁም የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ከሲህርና ከመጥፎ ነገሮች መራቅን አስመልክተው ያስጠነቀቁትን እናስታውስ። በአቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንደተዘገበው ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡-
​"ሰባቱን አጥፊ ወንጀሎች ተቆጠቡ። ... ሲህር መስራትም ከነዚህ ውስጥ ይጠቀሳል።" (ቡኻሪ እና ሙስሊም)
​በዚህ አጋጣሚ፣ ይህን ፖስት ተከትላችሁ በየሶሻል ሚዲያው የምታስተምሩ ወንድም እህቶች፣ መረጃውን ያገኛችሁበትን "የቀልብ ዶክተር"ን መጠቀስ አትርሱ። ማስተማሩ በራሱ መልካም ሆኖ ሳለ፣ መረጃው የመነጨበትን ምንጭ መጥቀስ ለባለቤቱ ክብር መስጠት ነው። ​አላህ ከሲህር ጥቃቶች ሁሉ ይጠብቃችሁ! ከክፉ ጂኖችና ከመጥፎ ዓይን በራህመቱ ይሰውራችሁ። አሚን!🤲

🏴 #ቪድዮውን_ሳያዩ_ለህክምና_እንዳይመጡ 🔸አዎ የዳኑ ሁሉ እየመሰከሩ ነው🔸 💡💡لا غالبَ إلا الله💡💡 💠ቻናላችንን ለኡማው ያስተዋውቁ 👇 ⭐️     https://t.me/Qallbdoc ህክምና ለማግኘት👇 https://t.me/freeeeeeeeeeeere 👆 ህክምና ለማግኘት👇 https://t.me/UstazulQallb 👆 ዌብሳይት (ድህረ ገፅ) 👇 📱 https://qalebdoctor.com

    ✅ብርሀኔ ጠፋችብኝ ፍቅሬን ነጠቁኝ!! ክፍል 8 ምግብ ስትበላ ወዲያውኑ ታስታውከው ነበር። ውሃ እንኳ መዋጥ አስቸጋሪ ሆነላት። ዓይኖቿ ውስጥ ያለው ብርሃን እየጠፋ ወደ ከባድ ግራጫነት ተቀየሩ። እኔ በየቀኑ ከጎኗ ተቀምጬ እጆቿን እያሸሁ ቁርዓን እቀራለሁ። ቁርዓን ስቀራላት ሰውነቷ ክፉኛ ይንቀጠቀጣል በሌላ ድምፅም መጮኽ ትጀምራለች። "አቁም! አትቅራ!" እያለ ያ በውስጧ ያለው ክፉ ኃይል በእሷ አንደበት ይጮኽ ነበር። እኔ ግን እያለቀስኩም ቢሆን ንባቤን እቀጥላለሁ። የበሽታው መረብ እሷን ብቻ ሳይሆን እኔንም ጭምር ማዳከም ጀመረ። እጆቼ መንቀጥቀጥ አእምሮዬ መዘናጋት ጀመረ። በአካባቢያችን ያሉ ጎረቤቶች ስለ ቤታችን ሁኔታ ማወቅ ጀመሩ። በሌሊት የሚሰማው ጩኸት የዕቃዎች መሰባበር ድምፅ እና የእኛ መኮማተር አልተሸሸገላቸውም። ነገር ግን ጎረቤቶቻችን እኛን ለመርዳት ወይም ለማፅናናት ከመሞከር ይልቅ እኛን እንደ እርጉም እንደ እብድ ማህበረሰብ መመልከት ጀመሩ። መንገድ ላይ ሲያዩኝ ፊታቸውን ያዞሩ ነበር። "እነሱ ቤት ውስጥ ሸይጣን አለ…እንዳትቀርቧቸው" የሚለው ወሬ በአካባቢው በሙሉ ተናፈሰ። ልጆቻቸውን ወደ እኛ ቤት እንዳይመጡ መከልከል ጀመሩ። ሙሉ በሙሉ ተገለልን። በአንድ ወቅት ሰዎችን በክብርና በደስታ እቀበልበት የነበረው ቤቴ አሁን ማንም የማይጠጋው የተረገመ ደሴት ሆነ። ይህ ማህበራዊ መገለል በውስጣችን ያለውን ስቃይ ይበልጥ አከበደው። በሰው ሀገር ሳይሆን በገዛ ሀገራችን በገዛ ሰፈራችን እንደ ባዕድና እንደ ጠላት መታየታችን የውስጥ ቁስላችንን ይበልጥ አመረቀዘው። የጎረቤት መራቅ የብቸኝነታችንን ጽዋ ሞላው። ምንም እንኳን ፈተናው ቢበረታም እኛ ግን ከቁርዓን ጥበቃ ውጭ ሌላ አማራጭ አልነበረንም። በየቀኑ ሱረቱል በቀራህን በቤቱ ውስጥ በከፍተኛ ድምፅ እንከፍታለን።  እኔም ራሴ በየቀኑ እጆቼን ባለቤቴ ራስ ላይ ጭኜ አያቶችን እደግማለሁ። ቁርዓኑ በሚቀራበት ጊዜ በቤቱ ውስጥ ታላቅ ጦርነት ይካሄድ ነበር። የመስታወቶች በራሳቸው ጊዜ መፈንዳት የመጋረጃዎች መቅደድ እና በግድግዳው ላይ የሚንሸራተቱ ጥላዎች ቁርዓኑ ክፉውን ኃይል እያቃጠለው መሆኑን ያሳዩ ነበር። ነገር ግን ድግምቱ በየቀኑ ስለሚታደስ ለአንድ አፍታ እንኳ እፎይታ ማግኘት አልቻልንም ነበር። ባለቤቴ ቁርዓኑ ሲቀራላት ጥቂት የሰላም ደቂቃዎችን ታገኛለች። ያኔ ዓይኖቿን ከፍ አድርጋ "ትንሽም ቢሆን ስትቀራልኝ ቁርዓኑ የውስጤን እሳት ያጠፋዋል… እባክህ አታቁም" ትለኛለች።  እኔም ጉሮሮዬ እስኪደርቅ ድምፄ እስኪዘጋ ድረስ ሌሊቱን ሙሉ ንባቤን እቀጥላለሁ። የቁርዓን ጥበቃ ብቻ ባይኖር ኖሮ በዚያኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ እንደምንጠፋ አውቃለሁ።    🔸አዎ የዳኑ ሁሉ እየመሰከሩ ነው🔸 💡💡لا غالبَ إلا الله💡💡 💠ቻናላችንን ለኡማው ያስተዋውቁ 👇 ⭐️ https://t.me/Qallbdoc ህክምና ለማግኘት👇 ✈️https://t.me/freeeeeeeeeeeere 👆 ህክምና ለማግኘት👇 ✈️https://t.me/UstazulQallb 👆 ዌብሳይት (ድህረ ገፅ) 👇 📱 https://qalebdoctor.com  

🔵የንፋስ ሲህር (ጥንቆላዎች) ምልክቶች🔵 🖋በዶክተር አቡ ፈርሃን  ቢስሚላህ በዚያ ምድርን ያለምሶሶ ባኖረው ጨረቃንና ፀሃይን እንደየውበታቸው ላመላከተን ምድር ሰማይ ተራሮች ሊሸከሙት ያልቻሉትን ቁርአን ባወረደልን ጌታችን አላሁ ሱብሃነሁ ወተአላ ስም እጀምራለሁ፡፡ ምልክቶቹ ክፍል 1  1. #የሱብሂ_ሰላት ኋላ ያለው ቀዝቃዛ ነፋሻማ ጣፋጭ አየር ለነርሱ ልክ እንደ አላርጂክ ነው፡፡ ይወጋቸዋል ያሳክካቸዋል ያስነጥሳቸዋል ሰላም አይሰጣቸውም፡፡ 2. #ቀንና_ለማታ ንፋስ ሽው ብሎ ባለፈ ቁጥር ያወራቸዋል፡፡ ይህም የሆነ ሰው የጠራቸው አልያም ከሆነ ቦታ ለነርሱ ብቻ መልእክት የተላለፈ መስሎ ይታያቸዋል፡፡ 3. #ልብ_እና _የሆድ_ውጋት፡፡ ይህ እንደማንኛውም ቁርጠት አይደለም፡፡ ሆዳቸው በጋዝ ይሞላል ፡፡ ከሆዳቸውም አየር በጣም ያስቸግራቸዋል፡፡ ቅስፍ አድርጎ እየወጋ ይተዋቸዋል፡፡ 4. #ብዙ_ግዜ_መግሪብ አዛን በሚልበት ወቅት አልያም የፀሃይን መግባት ተከትሎ በጣሙኑ ጭንቀት ይወርሳቸዋል፡፡ በውል የማያውቁት ጭንቀት ሰለባ ይሆናሉ፡፡ 5. #ዶማ_ልብ የደነደነ ንፍቅና አላቸው። ቢስሚላህ አልሃምዱሊላህ ከማለት ተራራ መግፋት ይቀላቸዋል፡፡ እነኚህን ቃላት በሉ ሲባሉም ያማቸዋል፡፡  6. #ክፉ_አመል ሰላት አይገራላቸውም፡፡ ቢገራላቸው እንኳ ውዱእ አድርገው ሰላት ሲቆሙ አየር ያመልጣቸዋል፡፡ወ ዱእ ያስፈታቸዋል፡፡ 7. #ተራ_ወስዋስ ያስቸግራቸዋል፡፡ ይህም ሲባል ሰላት ላይ ሲቆሙ ‹‹ፈስተሃል በደምብ  አልሃረምክም›› ‹‹እከሌ እየሰማህ ነው›› ‹‹እከሌ እንዲህ ልኮብሃል›› ‹‹እንዲህ አድርጎብሃል ››  ይላቸዋል፡፡ 8. #ርሀብ_ቶሎ ቶሎ መሰማት። እየበሉ ይርባቸዋል ጥዋት ማታ ሲበሉ ታያቸዋለህ። ህክምናው በቀልብ ዶክተር ቻናል ይቀጥላል!! #ፈጥነው_ይታከሙ_በቶሎ_ይዳኑ 🔸አዎ የዳኑ ሁሉ እየመሰከሩ ነው🔸 💡💡لا غالبَ إلا الله💡💡 💠ቻናላችንን ለኡማው ያስተዋውቁ 👇 ⭐️     https://t.me/Qallbdoc ህክምና ለማግኘት👇 https://t.me/freeeeeeeeeeeere 👆 ህክምና ለማግኘት👇 https://t.me/UstazulQallb 👆 ዌብሳይት (ድህረ ገፅ) 👇 📱 https://qalebdoctor.com

🤎🤲🏻ጥልቅ ፍቅር እስከሞት ነው 🤲🤲🤲🌗 https://t.me/Qallbdoc  ┄┄┉┉✽»🌹 ┄┄┉┉✽»🌹https://t.me/dr_of_heart

🎧  #የምሽት #ስንቅ #ለቀልባችን🎧     #የቀልብ #ዶክተር #የአፊያዎ #መንደር! https://t.me/Qallbdoc  https://t.me/dr_of_heart   #የእለቱ #መልዕክት👇👇👇 🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴 💭 አጥፊ ንግግር! ረሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦ ﴿إِنَّ الْعَبْدَ لَيَتَكَلَّمُ بِالْكَلِمَةِ مِنْ سَخَطِ اللَّهِ لَا يُلْقِي لَهَا بَالًا يَهْوِي بِهَا فِي جَهَنَّمَ﴾ “አንድ ባሪያ አሏህን የሚያስቆጣ አንዲት ንግግርን ይናገራል በሷ የሚያመጣበትን መዘዝ ሳያውቅ ከዛ ወደ ጀሀነም ይወረወራል።” 🌴 ቡኻሪ ዘግበውታል: 6478🌴

​ሰኔና ሰኞ! ስንቱን ታዘባችሁ!? ​ለማጋለጥ ሳይሆን ለማስተማር በሚል መርህ፣ እስኪ በየቤታችሁ እንመልከት። ስንቱ ያማረ ልብስ ለብሶ፣ በነጠላ ተውቦ፣ ቂቤውን ተቀብቶ በዝምታ "ሲያንጎርር" አለፈ?
​ሰኔና ሰኞ! ስንቱን ታዘባችሁ!? ​ለማጋለጥ ሳይሆን ለማስተማር በሚል መርህ፣ እስኪ በየቤታችሁ እንመልከት። ስንቱ ያማረ ልብስ ለብሶ፣ በነጠላ ተውቦ፣ ቂቤውን ተቀብቶ በዝምታ "ሲያንጎርር" አለፈ? ስንቱስ ከቤቱ ጠፍቶ ውሎ፣ አመሻሽቶ ወደ ቤቱ ገባ? ​ይህ ቀን እጅግ ልንጠነቀቅ የሚገባው፣ "ወሰን ገላ" የሚሰኝ ጂን የሚነግስበት ነው። የዛር መንፈስ ያላቸው ሰዎች ለዚህ መንፈስ ለመገበር የሚቆነጃጁበት፣ ጠንቋይ (ሷሂር) ዘንድ ድቤ የሚመቱበት ወቅት ነው። ስንቶቻችሁ ቤት በዚህ አጋጣሚ ጠንቋዮች መኖራቸውን አረጋገጣችሁ? ተጠንቀቁ! በዚህ ሰዓት በብዙ ሰዎች ላይ የቆየ ሲህር ይታደሳል። እነዚህ ጂኖች ስለሚገበርላቸው ጉልበታቸው ይበረታል፤ የሲህሩም ተፅዕኖ ይጠናከራል። ዛር ያለባቸውን ወደኛ በማምጣት፣ ህክምና በማድረግ እነዚህን የዛር ባሮች ከቀንበራቸው ማላቀቅ የግድ ነው። ​አላህ (ሱ.ወ) በቁርአን እንዲህ ይላል፡-
​"የሰሩትም የተንኮል ስራ (ሲህር) እንጂ ሌላ አይደለም። ጠንቋይም ከየትም በመጣ (በማንኛውም ቦታ) አይሳካለትም።" (ሱረቱ ጣሃ፡ 69)
​እንዲሁም የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ከሲህርና ከመጥፎ ነገሮች መራቅን አስመልክተው ያስጠነቀቁትን እናስታውስ። በአቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንደተዘገበው ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡-
​"ሰባቱን አጥፊ ወንጀሎች ተቆጠቡ። ... ሲህር መስራትም ከነዚህ ውስጥ ይጠቀሳል።" (ቡኻሪ እና ሙስሊም)
​በዚህ አጋጣሚ፣ ይህን ፖስት ተከትላችሁ በየሶሻል ሚዲያው የምታስተምሩ ወንድም እህቶች፣ መረጃውን ያገኛችሁበትን "የቀልብ ዶክተር"ን መጠቀስ አትርሱ። ማስተማሩ በራሱ መልካም ሆኖ ሳለ፣ መረጃው የመነጨበትን ምንጭ መጥቀስ ለባለቤቱ ክብር መስጠት ነው። ​አላህ ከሲህር ጥቃቶች ሁሉ ይጠብቃችሁ! ከክፉ ጂኖችና ከመጥፎ ዓይን በራህመቱ ይሰውራችሁ። አሚን!🤲

🏴 #ቪድዮውን_ሳያዩ_ለህክምና_እንዳይመጡ 🔸አዎ የዳኑ ሁሉ እየመሰከሩ ነው🔸 💡💡لا غالبَ إلا الله💡💡 💠ቻናላችንን ለኡማው ያስተዋውቁ 👇 ⭐️     https://t.me/Qallbdoc ህክምና ለማግኘት👇 https://t.me/freeeeeeeeeeeere 👆 ህክምና ለማግኘት👇 https://t.me/UstazulQallb 👆 ዌብሳይት (ድህረ ገፅ) 👇 📱 https://qalebdoctor.com

  ✅ብርሀኔ ጠፋችብኝ ፍቅሬን ነጠቁኝ!! ክፍል 7 "አብዱል ሀኪም ምን እየሆንክ ነው?" እያሉ የድሮ የንግድ አጋሮቼ ይደውሉልኝ ነበር። እኔ ግን ምን እየተፈጠረ እንዳለ ማስረዳት አልችልም ነበር። ምክንያቱም እኔ የማደርገው እያንዳንዱ ጥረት የምነካው እያንዳንዱ ነገር ወደ አመድነት ይቀየር ስለነበር። ይህ የኢኮኖሚ ውድቀት በቤታችን ላይ ያለውን ጫና ይበልጥ አበረታው። መድሃኒት ለመግዛት ለቤት ኪራይና ለዕለት ምግብ የሚሆን ገንዘብ ማጣት ጀመርን። ያ በስኬቱ የሚታወቀው ወጣት አሁን ለአንድ ሺህ ብር የሚለምንበት ደረጃ ላይ ደረሰ። የተዘጋው በር የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የህይወታችን መተንፈሻ ጭምር የተዘጋበት አስቸጋሪ ወቅት ነበረ። በነገራችሁ ላይ ይህ ሁሉ ሲሆን ለምን ዝም አላችሁ ልንባል እንችላለን እኔ ሰው ፊት እህቷን አንቄ ልገድላት ስል በስንት ግርግር ነው የተለያየነው፡፡ በፖሊስም ከሳን በሽምግልና አልቆ ነበር፡፡ ‹‹መተት አሰራችብን›› ብንል ጭንቀታችንን እውነታወን የተረዳ አልነበረም፡፡ እንደውም ‹‹እብዶች ናቸው› ወደሚለው ሳንሄድ የቀረን አይመስለኝም፡፡ የባለቤቴ እንባ የየቀኑ ምግባችን ሆነ። እሷ የራሷ አካል እየደከመ መሄዱን ስትመለከት እና ለእኔ መከራ ምክንያት እሷና ቤተሰቦቿ መሆናቸውን ስታስብ ከፍተኛ የጥፋተኝነት ስሜት ይሰማት ነበር። " እባክህ እኔን ፈታኝና ሂድ… እኔ ካንተ ካልራቅኩ ህይወትህ አይስተካከልም… እኔ ላንተ እርግማን ነኝ" እያለች እግሬ ስር ወድቃ ታለቅስ ነበር። እኔ ግን እጆቿን ይዤ ወደ ላይ አነሳትና "በፍጹም! አላህ በአንድ ላይ ያገናኘንን ትዳር በሸይጣን ተንኮል አላፈርሰውም። ህይወቴ ቢጠፋም ካንቺ ጎን ነኝ" እላት ነበር።  የእሷ እንባ የፍርሃት ሳይሆን ለእኔ ያላት ጥልቅ ፍቅርና በእህቷ ጭካኔ የተነሳ የተሰበረው ልቧ መግለጫ ነበረ። ያንን ንጹህ ፊቷን በእንባ ታጥቦ ስመለከት በውስጤ ለፍትህና ለፈውስ ያለኝ ጉጉት ይበልጥ ይጨምር ነበር። ነገር ግን ክፋቱ ኃይል የእሷን እንባ እንደ ጥንካሬው ምንጭ የሚጠቀምበት ይመስል እሷ ባለቀሰች ቁጥር በቤቱ ውስጥ ያለው አስፈሪ ድምፅ ይበልጥ ይጮኽ ነበር። ያኔ በሽታው መረቡን ሙሉ በሙሉ ዘረጋ። ባለቤቴ ከአልጋ መነሳት አቃታት። ሰውነቷ ላይ እንግዳ የሆኑ ጥቁርና ሰማያዊ ብልዝ ምልክቶች መታየት ጀመሩ። ልክ አንድ ሰው በዱላ ክፉኛ የደበደባት ያህል። ነገር ግን ማንም የነካት አልነበረም። እነዚህ ምልክቶች በጥቁር አስማቱ አማካኝነት በጂኒዎች (ሸይጣናት) የሚደርሱባት የአካል ጥቃቶች ምልክቶች እንደነበሩ አልጠራጠርም።