Addis Ketema Woreda 13 Education Office Official Page
رفتن به کانال در Telegram
This channel is available for educational expertise, school supervisors, directors, teachers & other stakeholders.
نمایش بیشتر805
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-77 روز
-1330 روز
آرشیو پست ها
ሰላም ለሁላችን!
የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል የውጤት መግለጫ ስለመጣ የተፈታኝ ተማሪዎች ቁጥር የሚገልፅ ደብዳቤ ይዛችው ከክ/ከተማ ትምህርት ፅ/ቤት እንድትቀበሉ እናሣስባችኋለን
Waajjirri barnootaa aanaa 13 manneen barnootaa mootummaa sadeen waliin tahuudhaan sosochii galmee barattootaa bara 2019 tiif naannoo Burcuqqoo irraa eegaluudhaan hanga kattaatti sagalee guddistuu,beeksisaa fi biroosharii qopheessuun ergaa dabarsaa ooleera.
13/12/18 A.L.I
ወረዳ 13 ት/ት ጽ/ቤት በዛሬው ዕለት ከ3ቱም የመንግስት ት/ት ቤቶች በጋራ በመሆን ባነር፣ማስታወቅያ እና የተለያዩ ብሮሸሮችን በማዘጋጀት የ2019 ት/ት ዘመን የተማሪወች ምዝገባ ቅስቅሳ ከብርጭቆ እስከ ከታ ድረስ በመሄድ ቅስቀሳ ተደርጓል።
13/12/18 ዓ.ም
ማሣሠቢያ :- ከታች ስማችው የተዘረዘረው የግል አንደኛ ደረጃ እና ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶቸ በሙሉ በተደጋጋሚ ለ2019ዓ.ም የትምህርት ዘመን የተመዘገቡትን የተማሪዎች ቁጥር እድትልኩልን ብንጠይቅም ያላካችው ሲሆን እስከ ዛሬ ማለትም ሀምሌ 27/2010 8:00 ድረስ በሀርድና በሶፍት እድትልኩልን እያልን በድጋሚ እናሳስባቸኋለን፡፡
ፋሪስ አካዳሚ ;አይከን አካዳሚ; ቅዱስፍራንችስኮስ ቅድመ መደበኛ እና አንደኛ ደረጃ ; አልሒሳን አካዳሚ; አርዲ ዪዝ ቅድመ መደበኛ እና አንደኛ ደረጃ ት/ቤት
በወረዳችን ውስጥ ለምትገኙ የመንግስት እና የግል አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶቸ በሙሉ ከታች በተቀመጠው የተማሪዎች የምዝባ ቅፅ መሰረት እስከ ዛሮ ድረስ የተመዘገቡትን የተማሪዎች ቁጥር እድትልኩልን እያል እናሳስባቸኋለን፡፡
ሰላም እንዴት ናችሁ ለ2019 አ.ም በአዳሪ ት/ቤቶችና እና ሳይንስ ሸርድ ትቤት ለመማር የተመዘገቡ ተማሪዎችን በበይነ መረብ ፈተናውን ለመስጠት ድላችን 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመፈተኛ ጣቢያ መሆኑን አውቃችሁ ፡-
1. የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች እሮብ በ22/11/2018
2. የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ደግሞ ሀሙስ በ23/11/2018 ፈተናው እንደሚሰጥ ይታወቃል ፡፡ በመሆኑም በተጠቀሰው ቀን ከጠዋቱ 2፡00 እንዲገኙ ጥሪ እንድታስተላልፉላቸው በጥብቅ እናሳስባለን !!!
የተፈታኝ ተማሪዎች ሊስት ከዚህ በታች ባለው Excel ይመልከቱ
ማሳሰቢያ ፡- በመረጃ ክፍተት ተማሪዎቻችን እድሉ እንዳያመልጣቸው ሁላችንም የድርሻችን እንወጣ !!!
መልካም ጊዜ
ማስታወቂያ፦
የቅድመ 1ኛ ደረጃ ት/ት ለምታስተምሩ የመንግስት እና የግል ት/ቤቶች።
በትምህርት ቤታችሁ፦ በቅድመ 1ኛ ሞግዚትነት በቋሚ ቅጥር ተቀጥረው እያስተማሩ ያሉ ሞግዚቶችን፣ ወይም ደግሞ በሰርተፍኬት በቋሚ ቅጥር ተቀጥረው እያስተማሩ ያሉ መምህራንን፦
ሀ. ለቅድመ 1ኛ መምህርነት ዲፕሎማ፣
ለ. ለPVA መምህርነት ዲፕሎማ፣
በመንግስት ስፖንሠርነት ለመማር ፍላጎት ያላቸውን ሞግዚቶችን እና የሠርተፊኬት መምህራንን በመለየት፣ በት/ቤታችሁ በ2ቱ የስራ መስኮች በቋሚነት ተቀጥረው እየሠሩ ስለመሆናቸው የሚገልፅ ህጋዊ ደብዳቤ እና የት/ት ማስረጃቸውን በማስያዝ አዲስ ከተማ ክ/ከተማ ት/ፅ/ቤት በአካል ቀርበው እንዲመዘገቡ እስከ አርብ 17/11/18ዓ.ም 8:00 ሰአት ድረስ ብቻ እንድትልኩልን እያሳሰብን፣ የት/ት ዕድሉ በ2ቱም ቋንቋ መሆኑን እንገልፃለን።
ማሳሰቢያ:-
* ከተጠቀሠው ቀንና ሰአት ካለፈ በኋላ የሚመጣን አናስተናግድም።
* ጥራት የሌለው መረጃ ከቀረበ አንቀበልም፤
* ማንኛውም የሰርተፍኬት መምህር መቅረት የለበትም።
* ፈቃድ ላይ ያሉ እና እረፍት የወጡ መምህራንና ሞግዚቶች እንዳይዘነጉ አደራ !!!
በወረዳችን ውስጥ ለምትገኙ የግል እና የመንግስት ክልላዊ ፈተና አስፈታኞች ትምህርት ቤቶች በሙሉ ከታች በተቀመጠው ቅፅ መሠረት የተማሪዎቻችሁን ውጤት ተንትናችው እስከ ሐምሌ 16/2018ዓ.ም ድረስ በሀርድ እና በሶፍት ኮፒ ገቢ እድታደርጉ እያልን እናሣስባችኃለን።
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የወረዳ 13 ትምህርት ፅ/ቤት QR Code scan በማድረግ አጠቃላይ አገልግሎታችንን ይመልከቱ
