fa
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

رفتن به کانال در Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

کانال ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 13 373 مشترک است و جایگاه 1 756 را در دسته حمل و نقل و رتبه 2 532 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 13 373 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 21 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 131 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 4 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 38.97% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.25% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 211 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 039 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 11 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 22 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته حمل و نقل تبدیل کرده‌اند.

13 375
مشترکین
+424 ساعت
+707 روز
+13130 روز
آرشیو پست ها
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የመንገድ ምርምርና ጥናት አካሄደ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በሀገር አቅፍ ደረጃ የምርምር ዓውደ ጥናት /Road Research/ በቀን ነሐሴ 23/12/2011
+3
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የመንገድ ምርምርና ጥናት አካሄደ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በሀገር አቅፍ ደረጃ የምርምር ዓውደ ጥናት /Road Research/ በቀን ነሐሴ 23/12/2011 ዓ.ም በሒልተን ሆቴል አካሄደ። አውደ ጥናቱ አላማ ያደረገው በመንገድ ዘርፍ ልማቱ ለተሰማሩ እና ከፍተኛ ልምድ ላላቸው ባለሙያዎች እንዲሁም ለዘርፉ ወሳኝ አካላቶች ልምዳቸውን ለማካፈል ትልቅ አጋጣሚ ፈጥሮ ለአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎች ጠቃሚ ግብአቶችን፤ ለጥናታዊ ፁሁፍ አቅራቢዎች ጥናቱን ለማጎልበት የሚያግዝ ገንቢ አስተያየቶች ተሰጥተውበታል። አውደ ጥናቱ በዘንድሮው ዓመት’Ensuring Effective Road Network Through Research” በሚል መሪ ቃል ለ6ተኛ ጊዜ ተካሂዷል። በዚህ ዓውደ ጥናት የተለያዩ የምርምር ተቋማት ፣ዮኒቨርስቲዎች፣አማካሪ ድርጅቶች፣የሃገር ውስጥ እና የውጪ ኮንትራክተሮች እንዲሁም የተለያዩ ባለድርሻ አካላቶች ተሳትፈውበታል። በዕለቱም በቁጥር ዘጠኝ(9) ችግር ፈቺ የሚባሉ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው በባለ ድርሻ አካላትና በሙህራን ውይይት ተደርጎባቸዋል። ከቀረቡት ዓውደ ጥናቶች መካከል የመንገድ ጥራት ችገር ፣የትራፊክ አደጋ መንሰኤና መፍትሄው ፣ በአይ.ቲ /ICT/ የተደገፈ የመንገድ ግንባታ ፣በገጠር ላሉ አካባቢዎች በምን መልኩ የመንገድ መሰረተ ልማት በስፋት ማዳረስ ይቻላል የሚሉት እና የተለያዩ ዓውደጥናቶች በተለያየ አካላት ቀርበዋል። በመጨረሻም በዕለቱ ጥናት ምርምር ላቀረቡ የምስክር ሰርተፌኬት ተሰጥቶ ዓውደ ጥናቱ ተጠናቋል።

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የ2011 እና የ2012 በጀት ዓመት አፈፃፀም እና እቅድ አሰመልክቶ ከሠራተኞች ጋር ነሐሴ 16 2011 ዓ.ም ውይይት አካሄደ። በዕለቱ በ2011 በጀት ዓመት የላቀ የሥራ አፈፃፀም ለነበራቸው የሥራ ክፍሎችና እንዲሁም ሠራተኛ የምስክር ወረቀትና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

"Ensuring Effective Road Network Through Research" 6th Annual Road Research Conference
"Ensuring Effective Road Network Through Research" 6th Annual Road Research Conference

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በ2011 በጀት ዓምት የሰራችወን ሰራዎች የያዘ መጽሄት በቅርብ እንለቃለን
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በ2011 በጀት ዓምት የሰራችወን ሰራዎች የያዘ መጽሄት በቅርብ እንለቃለን

sticker.webp0.27 KB

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የሥራ ማስታወቂያ በቅርብ ቀን #join #Share

የቴሌ ግራም ቻናላችን ወዳጅነቱን ያሣዩን

ERA has planned to procure construction works and related supervision services from eligible firms who are capable of constructing or supervising the following road projects in the 2012 Ethiopian Fiscal Year. The procurement process of the projects will commence soon.

REQUEST FOR EXPRESSIONS OF INTEREST For The Consultancy Service for Supervision of Heavy Road Maintenance Projects /National Competitive Bidding/

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1 ሺህ 440ኛው ዓመተ ሒጅራ የኢድ-አል አድሐ (ዓረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን

በ GPS ጠቀሜታ ዙርያ ለኢ.መ.ባ አሽከርካሪዎች ስልጠና ተሰጠ፡፡

https://t.me/ethioroads በ2012 በጀት ዓመት የተያዙ የመንገድ ኘሮጀክቶችን ዝርዝር በቅርብ ቀን @ethioroads #share #join

ኢትዮጵያና የአፍሪካ ልማት ባንክ የ98 ሚሊየን ዶላር የእርዳታ ስምምነት ተፈራረሙ

40.5 ኪ.ሜ የሚረዝመው የወራቤ-ቡዣበር መንገድ ግንባታ ሊጀመር ነው፡፡ በደቡብ ክልል ውስጥ የሚገኘውን የወራቤ-ቡዣበር 40.5 ኪ.ሜ መንገድ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ለመገንባት የሚያስችል የኮንትራት ስምምነት ሃምሌ 16 ቀን 2011 ዓ.ም የተፈረመ ሲሆን ፣ የዚህን መንገድ ግንባታ በአፋጣኝ ለማስጀመርም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ የዚህን መንገድ ግንባታ ለማካሄድ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጋር የውል ስምምነት የተፈራረመው አገር በቀሉ ማርካን ትሬዲንግ ፒ.ኤል.ሲ ሲሆን ፣ የመንገድ ግንባታውን የማማከርና የቁጥጥር ስራ የሚያከናውነው አማካሪ ድርጅት መረጣም በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ ለዚህ መንገድ ግንባታ የሚውለው 795,000,000.00ብር (ሰባት መቶ ዘጠና አምስት ሚሊዮን ብር) የግንባታ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ሲሆን ፣ የስራ ተቋራጩ መንገዱን ገንብቶ እንዲያጠናቀቅ የተሰጠው የጊዜ ገደብ ሶስት ዓመት ነው፡፡

በሀገራችን በአይነቱም ሆነ በዘመናዊነቱ ልዩ የሆነ ድልድይ ሊገነባ ነው፡፡ 380 ሜትር የሚረዝመውና በአይነቱ በሀገራችን ዘመናዊ የሆነው ድልድይ የሚገነባው በአባይ ወንዝ ላይ ነው፡፡ ለአጠቃላይ ግንባ
+3
በሀገራችን በአይነቱም ሆነ በዘመናዊነቱ ልዩ የሆነ ድልድይ ሊገነባ ነው፡፡ 380 ሜትር የሚረዝመውና በአይነቱ በሀገራችን ዘመናዊ የሆነው ድልድይ የሚገነባው በአባይ ወንዝ ላይ ነው፡፡ ለአጠቃላይ ግንባታው የኢትዮጵያ መንግስት ከ1.4 ቢሊዮን ብር በላይ ተመድቦለታል፡፡ ይህን ዘመናዊ ድልድይ ለመገንባት ጨረታውን አሸንፎ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጋር የውል ስምምነት የተፈራረመው አለማቀፉ የቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ (cccc) ነው፡፡ የምህንድስና እና የቁጥጥር ስራው ቦቴክ ቦስፈረስ የተባለ የቱርክ አማካሪ ድርጅት ከኢትዮጵያው እስታዲያ ኢንጅነሪንግ ስራዎች ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን ያከናውኑታል፡፡ በእስካሀኑ ሂደት የዲዛይን ስራው እየተካሄደ ሲሆን በቅርቡ ደግሞ የግንባታ ስራው እንደሚጀመር የሚጠበቀው የአባይ ወንዝ ድልድይ ለተቋራጩ የ3 ዓመት የጊዜ ገደብ ተሰጥቶታል፡፡ ከነባሩ አባይ ድልድይ ማለትም ባህርዳር ከተማ ውስጥ ከሚገኘው 2 ኪ.ሜ እርቀት ላይ የሚገነባው አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ የግንባታ ስራው ሲጠናቀቅ በዘመናዊነቱም እንዲሁም ማራኪነቱም በሀገራችን ግንባር ቀደም ይሆናል ተብሏል፡፡ በተመሳሳይም በርዝመቱ ከተከዜ ወንዝ 440 ሜትር ድልድይ በመቀጠል ሁለተኛው ይሆናል፡፡ አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ በጥቅሉ 43 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ሲሆን በግራና በቀኝ በአንድ ግዜ 6 ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችል ይሆናል፡፡ አንዱ መስመር ብቻ 21.5 ሜትር ስፋት ያለው ሲሆን በውስጡ ባለ ሶስት መስመር የተሸከርካሪ መሄጃ ፣ የብስክሌት ተጠቃሚዎች መስመር እንዲሁም 5 ሜትር የእግረኛ መሄጃን ያካቷል። ከድልድዩ ግንባታ ጎን ለጎን ተያያዥ የኮንክሪት ስትራክቸር ስራዎችና፣ የተሽከርካሪ መወጣጫ (ramp) ፣ የትራፊክ ምልከቶች፣ የድልድይ ላይ መብራቶች ስራም ይኖረዋል።