es
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Ir al canal en Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

El canal ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 13 373 suscriptores, ocupando la posición 1 756 en la categoría Transporte y el puesto 2 532 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 13 373 suscriptores.

Según los últimos datos del 21 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 131, y en las últimas 24 horas de 4, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 38.97%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.25% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 211 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 039 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 11.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 22 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Transporte.

13 375
Suscriptores
+424 horas
+707 días
+13130 días
Archivo de publicaciones
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የመንገድ ምርምርና ጥናት አካሄደ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በሀገር አቅፍ ደረጃ የምርምር ዓውደ ጥናት /Road Research/ በቀን ነሐሴ 23/12/2011
+3
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የመንገድ ምርምርና ጥናት አካሄደ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በሀገር አቅፍ ደረጃ የምርምር ዓውደ ጥናት /Road Research/ በቀን ነሐሴ 23/12/2011 ዓ.ም በሒልተን ሆቴል አካሄደ። አውደ ጥናቱ አላማ ያደረገው በመንገድ ዘርፍ ልማቱ ለተሰማሩ እና ከፍተኛ ልምድ ላላቸው ባለሙያዎች እንዲሁም ለዘርፉ ወሳኝ አካላቶች ልምዳቸውን ለማካፈል ትልቅ አጋጣሚ ፈጥሮ ለአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎች ጠቃሚ ግብአቶችን፤ ለጥናታዊ ፁሁፍ አቅራቢዎች ጥናቱን ለማጎልበት የሚያግዝ ገንቢ አስተያየቶች ተሰጥተውበታል። አውደ ጥናቱ በዘንድሮው ዓመት’Ensuring Effective Road Network Through Research” በሚል መሪ ቃል ለ6ተኛ ጊዜ ተካሂዷል። በዚህ ዓውደ ጥናት የተለያዩ የምርምር ተቋማት ፣ዮኒቨርስቲዎች፣አማካሪ ድርጅቶች፣የሃገር ውስጥ እና የውጪ ኮንትራክተሮች እንዲሁም የተለያዩ ባለድርሻ አካላቶች ተሳትፈውበታል። በዕለቱም በቁጥር ዘጠኝ(9) ችግር ፈቺ የሚባሉ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው በባለ ድርሻ አካላትና በሙህራን ውይይት ተደርጎባቸዋል። ከቀረቡት ዓውደ ጥናቶች መካከል የመንገድ ጥራት ችገር ፣የትራፊክ አደጋ መንሰኤና መፍትሄው ፣ በአይ.ቲ /ICT/ የተደገፈ የመንገድ ግንባታ ፣በገጠር ላሉ አካባቢዎች በምን መልኩ የመንገድ መሰረተ ልማት በስፋት ማዳረስ ይቻላል የሚሉት እና የተለያዩ ዓውደጥናቶች በተለያየ አካላት ቀርበዋል። በመጨረሻም በዕለቱ ጥናት ምርምር ላቀረቡ የምስክር ሰርተፌኬት ተሰጥቶ ዓውደ ጥናቱ ተጠናቋል።

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የ2011 እና የ2012 በጀት ዓመት አፈፃፀም እና እቅድ አሰመልክቶ ከሠራተኞች ጋር ነሐሴ 16 2011 ዓ.ም ውይይት አካሄደ። በዕለቱ በ2011 በጀት ዓመት የላቀ የሥራ አፈፃፀም ለነበራቸው የሥራ ክፍሎችና እንዲሁም ሠራተኛ የምስክር ወረቀትና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

"Ensuring Effective Road Network Through Research" 6th Annual Road Research Conference
"Ensuring Effective Road Network Through Research" 6th Annual Road Research Conference

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በ2011 በጀት ዓምት የሰራችወን ሰራዎች የያዘ መጽሄት በቅርብ እንለቃለን
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በ2011 በጀት ዓምት የሰራችወን ሰራዎች የያዘ መጽሄት በቅርብ እንለቃለን

sticker.webp0.27 KB

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የሥራ ማስታወቂያ በቅርብ ቀን #join #Share

የቴሌ ግራም ቻናላችን ወዳጅነቱን ያሣዩን

ERA has planned to procure construction works and related supervision services from eligible firms who are capable of constructing or supervising the following road projects in the 2012 Ethiopian Fiscal Year. The procurement process of the projects will commence soon.

REQUEST FOR EXPRESSIONS OF INTEREST For The Consultancy Service for Supervision of Heavy Road Maintenance Projects /National Competitive Bidding/

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1 ሺህ 440ኛው ዓመተ ሒጅራ የኢድ-አል አድሐ (ዓረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን

በ GPS ጠቀሜታ ዙርያ ለኢ.መ.ባ አሽከርካሪዎች ስልጠና ተሰጠ፡፡

https://t.me/ethioroads በ2012 በጀት ዓመት የተያዙ የመንገድ ኘሮጀክቶችን ዝርዝር በቅርብ ቀን @ethioroads #share #join

ኢትዮጵያና የአፍሪካ ልማት ባንክ የ98 ሚሊየን ዶላር የእርዳታ ስምምነት ተፈራረሙ

40.5 ኪ.ሜ የሚረዝመው የወራቤ-ቡዣበር መንገድ ግንባታ ሊጀመር ነው፡፡ በደቡብ ክልል ውስጥ የሚገኘውን የወራቤ-ቡዣበር 40.5 ኪ.ሜ መንገድ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ለመገንባት የሚያስችል የኮንትራት ስምምነት ሃምሌ 16 ቀን 2011 ዓ.ም የተፈረመ ሲሆን ፣ የዚህን መንገድ ግንባታ በአፋጣኝ ለማስጀመርም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ የዚህን መንገድ ግንባታ ለማካሄድ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጋር የውል ስምምነት የተፈራረመው አገር በቀሉ ማርካን ትሬዲንግ ፒ.ኤል.ሲ ሲሆን ፣ የመንገድ ግንባታውን የማማከርና የቁጥጥር ስራ የሚያከናውነው አማካሪ ድርጅት መረጣም በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ ለዚህ መንገድ ግንባታ የሚውለው 795,000,000.00ብር (ሰባት መቶ ዘጠና አምስት ሚሊዮን ብር) የግንባታ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ሲሆን ፣ የስራ ተቋራጩ መንገዱን ገንብቶ እንዲያጠናቀቅ የተሰጠው የጊዜ ገደብ ሶስት ዓመት ነው፡፡

በሀገራችን በአይነቱም ሆነ በዘመናዊነቱ ልዩ የሆነ ድልድይ ሊገነባ ነው፡፡ 380 ሜትር የሚረዝመውና በአይነቱ በሀገራችን ዘመናዊ የሆነው ድልድይ የሚገነባው በአባይ ወንዝ ላይ ነው፡፡ ለአጠቃላይ ግንባ
+3
በሀገራችን በአይነቱም ሆነ በዘመናዊነቱ ልዩ የሆነ ድልድይ ሊገነባ ነው፡፡ 380 ሜትር የሚረዝመውና በአይነቱ በሀገራችን ዘመናዊ የሆነው ድልድይ የሚገነባው በአባይ ወንዝ ላይ ነው፡፡ ለአጠቃላይ ግንባታው የኢትዮጵያ መንግስት ከ1.4 ቢሊዮን ብር በላይ ተመድቦለታል፡፡ ይህን ዘመናዊ ድልድይ ለመገንባት ጨረታውን አሸንፎ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጋር የውል ስምምነት የተፈራረመው አለማቀፉ የቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ (cccc) ነው፡፡ የምህንድስና እና የቁጥጥር ስራው ቦቴክ ቦስፈረስ የተባለ የቱርክ አማካሪ ድርጅት ከኢትዮጵያው እስታዲያ ኢንጅነሪንግ ስራዎች ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን ያከናውኑታል፡፡ በእስካሀኑ ሂደት የዲዛይን ስራው እየተካሄደ ሲሆን በቅርቡ ደግሞ የግንባታ ስራው እንደሚጀመር የሚጠበቀው የአባይ ወንዝ ድልድይ ለተቋራጩ የ3 ዓመት የጊዜ ገደብ ተሰጥቶታል፡፡ ከነባሩ አባይ ድልድይ ማለትም ባህርዳር ከተማ ውስጥ ከሚገኘው 2 ኪ.ሜ እርቀት ላይ የሚገነባው አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ የግንባታ ስራው ሲጠናቀቅ በዘመናዊነቱም እንዲሁም ማራኪነቱም በሀገራችን ግንባር ቀደም ይሆናል ተብሏል፡፡ በተመሳሳይም በርዝመቱ ከተከዜ ወንዝ 440 ሜትር ድልድይ በመቀጠል ሁለተኛው ይሆናል፡፡ አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ በጥቅሉ 43 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ሲሆን በግራና በቀኝ በአንድ ግዜ 6 ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችል ይሆናል፡፡ አንዱ መስመር ብቻ 21.5 ሜትር ስፋት ያለው ሲሆን በውስጡ ባለ ሶስት መስመር የተሸከርካሪ መሄጃ ፣ የብስክሌት ተጠቃሚዎች መስመር እንዲሁም 5 ሜትር የእግረኛ መሄጃን ያካቷል። ከድልድዩ ግንባታ ጎን ለጎን ተያያዥ የኮንክሪት ስትራክቸር ስራዎችና፣ የተሽከርካሪ መወጣጫ (ramp) ፣ የትራፊክ ምልከቶች፣ የድልድይ ላይ መብራቶች ስራም ይኖረዋል።