ru
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Открыть в Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Канал ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 13 373 подписчиков, занимая 1 756 место в категории Транспорт и 2 532 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 13 373 подписчиков.

Согласно последним данным от 21 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 131, а за последние 24 часа — 4, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 38.97%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.25% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 5 211 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 039 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 11.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 22 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Транспорт.

13 375
Подписчики
+424 часа
+707 дней
+13130 день
Архив постов
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የመንገድ ምርምርና ጥናት አካሄደ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በሀገር አቅፍ ደረጃ የምርምር ዓውደ ጥናት /Road Research/ በቀን ነሐሴ 23/12/2011
+3
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የመንገድ ምርምርና ጥናት አካሄደ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በሀገር አቅፍ ደረጃ የምርምር ዓውደ ጥናት /Road Research/ በቀን ነሐሴ 23/12/2011 ዓ.ም በሒልተን ሆቴል አካሄደ። አውደ ጥናቱ አላማ ያደረገው በመንገድ ዘርፍ ልማቱ ለተሰማሩ እና ከፍተኛ ልምድ ላላቸው ባለሙያዎች እንዲሁም ለዘርፉ ወሳኝ አካላቶች ልምዳቸውን ለማካፈል ትልቅ አጋጣሚ ፈጥሮ ለአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎች ጠቃሚ ግብአቶችን፤ ለጥናታዊ ፁሁፍ አቅራቢዎች ጥናቱን ለማጎልበት የሚያግዝ ገንቢ አስተያየቶች ተሰጥተውበታል። አውደ ጥናቱ በዘንድሮው ዓመት’Ensuring Effective Road Network Through Research” በሚል መሪ ቃል ለ6ተኛ ጊዜ ተካሂዷል። በዚህ ዓውደ ጥናት የተለያዩ የምርምር ተቋማት ፣ዮኒቨርስቲዎች፣አማካሪ ድርጅቶች፣የሃገር ውስጥ እና የውጪ ኮንትራክተሮች እንዲሁም የተለያዩ ባለድርሻ አካላቶች ተሳትፈውበታል። በዕለቱም በቁጥር ዘጠኝ(9) ችግር ፈቺ የሚባሉ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው በባለ ድርሻ አካላትና በሙህራን ውይይት ተደርጎባቸዋል። ከቀረቡት ዓውደ ጥናቶች መካከል የመንገድ ጥራት ችገር ፣የትራፊክ አደጋ መንሰኤና መፍትሄው ፣ በአይ.ቲ /ICT/ የተደገፈ የመንገድ ግንባታ ፣በገጠር ላሉ አካባቢዎች በምን መልኩ የመንገድ መሰረተ ልማት በስፋት ማዳረስ ይቻላል የሚሉት እና የተለያዩ ዓውደጥናቶች በተለያየ አካላት ቀርበዋል። በመጨረሻም በዕለቱ ጥናት ምርምር ላቀረቡ የምስክር ሰርተፌኬት ተሰጥቶ ዓውደ ጥናቱ ተጠናቋል።

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የ2011 እና የ2012 በጀት ዓመት አፈፃፀም እና እቅድ አሰመልክቶ ከሠራተኞች ጋር ነሐሴ 16 2011 ዓ.ም ውይይት አካሄደ። በዕለቱ በ2011 በጀት ዓመት የላቀ የሥራ አፈፃፀም ለነበራቸው የሥራ ክፍሎችና እንዲሁም ሠራተኛ የምስክር ወረቀትና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

"Ensuring Effective Road Network Through Research" 6th Annual Road Research Conference
"Ensuring Effective Road Network Through Research" 6th Annual Road Research Conference

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በ2011 በጀት ዓምት የሰራችወን ሰራዎች የያዘ መጽሄት በቅርብ እንለቃለን
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በ2011 በጀት ዓምት የሰራችወን ሰራዎች የያዘ መጽሄት በቅርብ እንለቃለን

sticker.webp0.27 KB

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የሥራ ማስታወቂያ በቅርብ ቀን #join #Share

የቴሌ ግራም ቻናላችን ወዳጅነቱን ያሣዩን

ERA has planned to procure construction works and related supervision services from eligible firms who are capable of constructing or supervising the following road projects in the 2012 Ethiopian Fiscal Year. The procurement process of the projects will commence soon.

REQUEST FOR EXPRESSIONS OF INTEREST For The Consultancy Service for Supervision of Heavy Road Maintenance Projects /National Competitive Bidding/

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1 ሺህ 440ኛው ዓመተ ሒጅራ የኢድ-አል አድሐ (ዓረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን

በ GPS ጠቀሜታ ዙርያ ለኢ.መ.ባ አሽከርካሪዎች ስልጠና ተሰጠ፡፡

https://t.me/ethioroads በ2012 በጀት ዓመት የተያዙ የመንገድ ኘሮጀክቶችን ዝርዝር በቅርብ ቀን @ethioroads #share #join

ኢትዮጵያና የአፍሪካ ልማት ባንክ የ98 ሚሊየን ዶላር የእርዳታ ስምምነት ተፈራረሙ

40.5 ኪ.ሜ የሚረዝመው የወራቤ-ቡዣበር መንገድ ግንባታ ሊጀመር ነው፡፡ በደቡብ ክልል ውስጥ የሚገኘውን የወራቤ-ቡዣበር 40.5 ኪ.ሜ መንገድ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ለመገንባት የሚያስችል የኮንትራት ስምምነት ሃምሌ 16 ቀን 2011 ዓ.ም የተፈረመ ሲሆን ፣ የዚህን መንገድ ግንባታ በአፋጣኝ ለማስጀመርም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ የዚህን መንገድ ግንባታ ለማካሄድ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጋር የውል ስምምነት የተፈራረመው አገር በቀሉ ማርካን ትሬዲንግ ፒ.ኤል.ሲ ሲሆን ፣ የመንገድ ግንባታውን የማማከርና የቁጥጥር ስራ የሚያከናውነው አማካሪ ድርጅት መረጣም በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ ለዚህ መንገድ ግንባታ የሚውለው 795,000,000.00ብር (ሰባት መቶ ዘጠና አምስት ሚሊዮን ብር) የግንባታ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ሲሆን ፣ የስራ ተቋራጩ መንገዱን ገንብቶ እንዲያጠናቀቅ የተሰጠው የጊዜ ገደብ ሶስት ዓመት ነው፡፡

በሀገራችን በአይነቱም ሆነ በዘመናዊነቱ ልዩ የሆነ ድልድይ ሊገነባ ነው፡፡ 380 ሜትር የሚረዝመውና በአይነቱ በሀገራችን ዘመናዊ የሆነው ድልድይ የሚገነባው በአባይ ወንዝ ላይ ነው፡፡ ለአጠቃላይ ግንባ
+3
በሀገራችን በአይነቱም ሆነ በዘመናዊነቱ ልዩ የሆነ ድልድይ ሊገነባ ነው፡፡ 380 ሜትር የሚረዝመውና በአይነቱ በሀገራችን ዘመናዊ የሆነው ድልድይ የሚገነባው በአባይ ወንዝ ላይ ነው፡፡ ለአጠቃላይ ግንባታው የኢትዮጵያ መንግስት ከ1.4 ቢሊዮን ብር በላይ ተመድቦለታል፡፡ ይህን ዘመናዊ ድልድይ ለመገንባት ጨረታውን አሸንፎ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጋር የውል ስምምነት የተፈራረመው አለማቀፉ የቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ (cccc) ነው፡፡ የምህንድስና እና የቁጥጥር ስራው ቦቴክ ቦስፈረስ የተባለ የቱርክ አማካሪ ድርጅት ከኢትዮጵያው እስታዲያ ኢንጅነሪንግ ስራዎች ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን ያከናውኑታል፡፡ በእስካሀኑ ሂደት የዲዛይን ስራው እየተካሄደ ሲሆን በቅርቡ ደግሞ የግንባታ ስራው እንደሚጀመር የሚጠበቀው የአባይ ወንዝ ድልድይ ለተቋራጩ የ3 ዓመት የጊዜ ገደብ ተሰጥቶታል፡፡ ከነባሩ አባይ ድልድይ ማለትም ባህርዳር ከተማ ውስጥ ከሚገኘው 2 ኪ.ሜ እርቀት ላይ የሚገነባው አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ የግንባታ ስራው ሲጠናቀቅ በዘመናዊነቱም እንዲሁም ማራኪነቱም በሀገራችን ግንባር ቀደም ይሆናል ተብሏል፡፡ በተመሳሳይም በርዝመቱ ከተከዜ ወንዝ 440 ሜትር ድልድይ በመቀጠል ሁለተኛው ይሆናል፡፡ አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ በጥቅሉ 43 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ሲሆን በግራና በቀኝ በአንድ ግዜ 6 ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችል ይሆናል፡፡ አንዱ መስመር ብቻ 21.5 ሜትር ስፋት ያለው ሲሆን በውስጡ ባለ ሶስት መስመር የተሸከርካሪ መሄጃ ፣ የብስክሌት ተጠቃሚዎች መስመር እንዲሁም 5 ሜትር የእግረኛ መሄጃን ያካቷል። ከድልድዩ ግንባታ ጎን ለጎን ተያያዥ የኮንክሪት ስትራክቸር ስራዎችና፣ የተሽከርካሪ መወጣጫ (ramp) ፣ የትራፊክ ምልከቶች፣ የድልድይ ላይ መብራቶች ስራም ይኖረዋል።