fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 533 مشترک است و جایگاه 8 368 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 174 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 533 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 30 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 10 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -6 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 24.86% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.87% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 862 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 620 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 9 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 01 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 533
مشترکین
-624 ساعت
-207 روز
+1030 روز
آرشیو پست ها
photo content
+3

በሪጅኑ በኤሌክትሪክ ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በተፈፀመ ሥርቆት ከ 9 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ኪሳራ ደርሷል ……..///…….... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሪጅን 1 የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች መምሪያ በሚያስተዳድራቸው የከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በተፈፀመ ሥርቆት ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ኪሳራ ደረሰ፡፡ መምሪያው እንዳስታወቀው በአዲስ አበባ ከተማ እና በዙሪያው በሚገኙ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በበጀት ዓመቱ ሦስት ወራት ውስጥ 1 ሺህ 771 ብረቶች እና 7 ሺህ 84 ብሎንና የብሎን ማሰሪያዎች በሌቦች ተሰርቀዋል፡፡ ሥርቆቱ በዋናነት የተፈጸመው ከገጣፎ - ቃሊቲ እና ከለገጣፎ - ሱልልታ በተዘረጉ ባለ 230 ኪሎ ቮልትመስመሮች እንዲሁም ከቃሊቲ - ገፈርሣ እና ከቃሊቲ - ወረገኑ በተዘረጉ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ነው፡፡ በዚህም ተቋሙ በ3 ወር ውስጥ ብቻ በተፈፀመ ስርቆት ምክንያት የተቋረጠውን የኢነርጅ መጠን ሳይጨምር ጉዳት ለደረሰባቸው የተለያዩ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ አካላት መልሶ መተኪያ 8 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ወጪ ማድረጉን ገልጿል፡፡ በጥገና ወቅት የሚያስፈልጉ የጉልበት ሠራተኛ፣ የነዳጅና የተለያዩ ግብዓቶችን ለማሟላት ደግሞ 720 ሺህ ብር ወጪ ማድረጉን ያስታወቀው ሪጅኑ ባለፉት ሶስት ወራት ብቻ በኤሌክትሪክ መሰረተልማት ስርቆት ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራ መድረሱን መምሪያው አመልክቷል፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ወንደሰን ወልደማርያም በሰጡት አስተያየት የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎችና ሽቦዎች ስርቆትን ለመከላከል በሚደረገው እንቅስቃሴ የፀጥታ አካላት ምላሽ ፈጣን አለመሆን ችግሩ እንዲባባስ ምክንያት ሆኗል። ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ተከሰው በሚቀርቡ ወንጀለኞች ላይ የፍትህ አካላት የሚጥሉት ቅጣት አስተማሪ አለመሆኑና ግብዓት ለማግኘት ሲሉ ስርቆቱን የሚደግፉና የሚረከቡ የብረታ-ብረት ፋብሪካዎችና ባለሀብቶች እንቅስቃሴ ሊፈተሽ እንደሚገባም ዳይሬክተሩ አሳስቧል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 08 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም 82 በመቶ ደርሷል .......////....... ለአዋሽ- ወልዲያ- ሀራ ገበያ የባቡር መስመር የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በመገንባት ላይ የሚገኘውን የማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቅ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ተክለወይኒ ብርሃነ እንደገለፁት በፕሮጀክቱ ላይ 206 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመር ግንባታ እና በመተሃራ፣ በደብረ ብርሃን፣ በሸዋ ሮቢት እና በከሚሴ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የማስፋፊያ ሥራዎች ይከናወናሉ። በፕሮጀክቱ ላይ ከሚተከሉ 553 የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች መካከል የ175 ምሶሶዎች ተከላ እና የ427 የምሰሶ መትከያ የመሠረት ቁፋሮ ሥራዎች መከናዎናቸውን አቶ ተክለወይኒ ተናግረዋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያዎቹ የማስፋፊያ ሥራ መጠናቀቁን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ የባቡር ጣቢያዎችን (Traction Station) ከተቋሙ የብሔራዊ የኃይል ቋት ጋር የሚያገናኙ የኮሙዩኒኬሽን መሳሪያዎችን ለማስቀመጥ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ፈቃድ እየተጠበቀ እንደሚገኝም አብራርተዋል፡፡ እንደ አቶ ተክለወይኒ ገለፃ ለፕሮጀክቱ ግንባታ ሥራ ከሚያስፈልጉ ዕቃዎች ውስጥ 84 ነጥብ 1 በመቶ የሚሆነው ተመርቶ ወደ ፕሮጀክቱ ሳይት የገባ ሲሆን የካሳ ክፍያ ሥራው ደግሞ 96 በመቶ ተጠናቋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያዎቹ የሙከራና የፍተሻ ሥራ በቅርቡ እንደሚከናወን ያነሱት አቶ ተክለወይኒ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀምም 82 በመቶ ደርሷል ብለዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በምድር ባቡር በኩል የሚከናወኑ የትራክሽን ጣቢያዎች ግንባታ አለመጠናቀቅና ወደ ተጠናቀቁ ጣቢያዎች ለመግባት የመግቢያ ፈቃድ አለመገኘቱ በፕሮጀክቱ የግንባታ እንቅስቃሴ ላይ ችግር እየፈጠረ ነው፡፡ ፕሮጀክቱን በማጠናቀቅ ለባቡር መስመሩ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን በኩል የሚከናወኑ ሥራዎች በወቅቱ ሊፈጸሙ እንደሚገባ አቶ ተክለወይኒ ጠቁመዋል፡፡ ከመተሃራ ማከፋፈያ ጣቢያ አስከ አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ድረስ ያለው የፕሮጀክቱ ሥራ በአካባቢው ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት ለአንድ ዓመት ያህል ተቋርጦ መቆየቱን ያስታወሱት አቶ ተክለወይኒ የግንባታ ሥራውን ለማስቀጠል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መግባባት ላይ በመደረሱ ተቋራጩ በቅርቡ ሥራውን እንደሚጀምር አስታውቀዋል፡፡ ፕሮጀክቱን በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቅ ርብርብ እየተደረገ ቢሆንም በፕሮጀክቱ ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት እና በአንዳንድ አካባቢዎች የሚስተዋለው የፀጥታ ችግር በተያዘለት መርሃ ግብር ለማጠናቀቅ እንቅፋት ሊሆኑ እንደሚችል ተናግረዋል። የፕሮጀክቱን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ፒንጋኦ ግሩፕ (Pinggao Group) እንዲሁም የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የማስፋፊያ ሥራን ቲ.ቢ.ኤ (TBEA,Co.Ltd) የተሰኙ ሁለት የቻይና ኩባንያዎች እያከናወኑት የሚገኝ ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ የሥራ ክፍል ደግሞ በማማከር ሥራው ላይ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡ የፕሮጀክቱ የፋይናንስ ወጪ ከ16 ነጥብ 85 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እና ከ174 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ሲሆን የፋይናንስ ወጪው ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የሚሸፈን ነው፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 07 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1