es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 533 suscriptores, ocupando la posición 8 368 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 174 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 533 suscriptores.

Según los últimos datos del 30 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 10, y en las últimas 24 horas de -6, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 24.86%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.87% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 862 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 620 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 9.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 01 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 533
Suscriptores
-624 horas
-207 días
+1030 días
Archivo de publicaciones
photo content
+3

በሪጅኑ በኤሌክትሪክ ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በተፈፀመ ሥርቆት ከ 9 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ኪሳራ ደርሷል ……..///…….... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሪጅን 1 የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች መምሪያ በሚያስተዳድራቸው የከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በተፈፀመ ሥርቆት ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ኪሳራ ደረሰ፡፡ መምሪያው እንዳስታወቀው በአዲስ አበባ ከተማ እና በዙሪያው በሚገኙ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በበጀት ዓመቱ ሦስት ወራት ውስጥ 1 ሺህ 771 ብረቶች እና 7 ሺህ 84 ብሎንና የብሎን ማሰሪያዎች በሌቦች ተሰርቀዋል፡፡ ሥርቆቱ በዋናነት የተፈጸመው ከገጣፎ - ቃሊቲ እና ከለገጣፎ - ሱልልታ በተዘረጉ ባለ 230 ኪሎ ቮልትመስመሮች እንዲሁም ከቃሊቲ - ገፈርሣ እና ከቃሊቲ - ወረገኑ በተዘረጉ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ነው፡፡ በዚህም ተቋሙ በ3 ወር ውስጥ ብቻ በተፈፀመ ስርቆት ምክንያት የተቋረጠውን የኢነርጅ መጠን ሳይጨምር ጉዳት ለደረሰባቸው የተለያዩ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ አካላት መልሶ መተኪያ 8 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ወጪ ማድረጉን ገልጿል፡፡ በጥገና ወቅት የሚያስፈልጉ የጉልበት ሠራተኛ፣ የነዳጅና የተለያዩ ግብዓቶችን ለማሟላት ደግሞ 720 ሺህ ብር ወጪ ማድረጉን ያስታወቀው ሪጅኑ ባለፉት ሶስት ወራት ብቻ በኤሌክትሪክ መሰረተልማት ስርቆት ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራ መድረሱን መምሪያው አመልክቷል፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ወንደሰን ወልደማርያም በሰጡት አስተያየት የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎችና ሽቦዎች ስርቆትን ለመከላከል በሚደረገው እንቅስቃሴ የፀጥታ አካላት ምላሽ ፈጣን አለመሆን ችግሩ እንዲባባስ ምክንያት ሆኗል። ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ተከሰው በሚቀርቡ ወንጀለኞች ላይ የፍትህ አካላት የሚጥሉት ቅጣት አስተማሪ አለመሆኑና ግብዓት ለማግኘት ሲሉ ስርቆቱን የሚደግፉና የሚረከቡ የብረታ-ብረት ፋብሪካዎችና ባለሀብቶች እንቅስቃሴ ሊፈተሽ እንደሚገባም ዳይሬክተሩ አሳስቧል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 08 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም 82 በመቶ ደርሷል .......////....... ለአዋሽ- ወልዲያ- ሀራ ገበያ የባቡር መስመር የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በመገንባት ላይ የሚገኘውን የማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቅ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ተክለወይኒ ብርሃነ እንደገለፁት በፕሮጀክቱ ላይ 206 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመር ግንባታ እና በመተሃራ፣ በደብረ ብርሃን፣ በሸዋ ሮቢት እና በከሚሴ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የማስፋፊያ ሥራዎች ይከናወናሉ። በፕሮጀክቱ ላይ ከሚተከሉ 553 የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች መካከል የ175 ምሶሶዎች ተከላ እና የ427 የምሰሶ መትከያ የመሠረት ቁፋሮ ሥራዎች መከናዎናቸውን አቶ ተክለወይኒ ተናግረዋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያዎቹ የማስፋፊያ ሥራ መጠናቀቁን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ የባቡር ጣቢያዎችን (Traction Station) ከተቋሙ የብሔራዊ የኃይል ቋት ጋር የሚያገናኙ የኮሙዩኒኬሽን መሳሪያዎችን ለማስቀመጥ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ፈቃድ እየተጠበቀ እንደሚገኝም አብራርተዋል፡፡ እንደ አቶ ተክለወይኒ ገለፃ ለፕሮጀክቱ ግንባታ ሥራ ከሚያስፈልጉ ዕቃዎች ውስጥ 84 ነጥብ 1 በመቶ የሚሆነው ተመርቶ ወደ ፕሮጀክቱ ሳይት የገባ ሲሆን የካሳ ክፍያ ሥራው ደግሞ 96 በመቶ ተጠናቋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያዎቹ የሙከራና የፍተሻ ሥራ በቅርቡ እንደሚከናወን ያነሱት አቶ ተክለወይኒ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀምም 82 በመቶ ደርሷል ብለዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በምድር ባቡር በኩል የሚከናወኑ የትራክሽን ጣቢያዎች ግንባታ አለመጠናቀቅና ወደ ተጠናቀቁ ጣቢያዎች ለመግባት የመግቢያ ፈቃድ አለመገኘቱ በፕሮጀክቱ የግንባታ እንቅስቃሴ ላይ ችግር እየፈጠረ ነው፡፡ ፕሮጀክቱን በማጠናቀቅ ለባቡር መስመሩ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን በኩል የሚከናወኑ ሥራዎች በወቅቱ ሊፈጸሙ እንደሚገባ አቶ ተክለወይኒ ጠቁመዋል፡፡ ከመተሃራ ማከፋፈያ ጣቢያ አስከ አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ድረስ ያለው የፕሮጀክቱ ሥራ በአካባቢው ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት ለአንድ ዓመት ያህል ተቋርጦ መቆየቱን ያስታወሱት አቶ ተክለወይኒ የግንባታ ሥራውን ለማስቀጠል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መግባባት ላይ በመደረሱ ተቋራጩ በቅርቡ ሥራውን እንደሚጀምር አስታውቀዋል፡፡ ፕሮጀክቱን በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቅ ርብርብ እየተደረገ ቢሆንም በፕሮጀክቱ ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት እና በአንዳንድ አካባቢዎች የሚስተዋለው የፀጥታ ችግር በተያዘለት መርሃ ግብር ለማጠናቀቅ እንቅፋት ሊሆኑ እንደሚችል ተናግረዋል። የፕሮጀክቱን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ፒንጋኦ ግሩፕ (Pinggao Group) እንዲሁም የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የማስፋፊያ ሥራን ቲ.ቢ.ኤ (TBEA,Co.Ltd) የተሰኙ ሁለት የቻይና ኩባንያዎች እያከናወኑት የሚገኝ ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ የሥራ ክፍል ደግሞ በማማከር ሥራው ላይ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡ የፕሮጀክቱ የፋይናንስ ወጪ ከ16 ነጥብ 85 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እና ከ174 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ሲሆን የፋይናንስ ወጪው ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የሚሸፈን ነው፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 07 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1