uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 533 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 368-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 174-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 533 obunachiga ega bo‘ldi.

30 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 10 ga, so‘nggi 24 soatda esa -6 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 24.86% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.87% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 862 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 620 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 9 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 01 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 533
Obunachilar
-624 soatlar
-207 kunlar
+1030 kunlar
Postlar arxiv
photo content
+3

በሪጅኑ በኤሌክትሪክ ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በተፈፀመ ሥርቆት ከ 9 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ኪሳራ ደርሷል ……..///…….... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሪጅን 1 የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች መምሪያ በሚያስተዳድራቸው የከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በተፈፀመ ሥርቆት ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ኪሳራ ደረሰ፡፡ መምሪያው እንዳስታወቀው በአዲስ አበባ ከተማ እና በዙሪያው በሚገኙ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በበጀት ዓመቱ ሦስት ወራት ውስጥ 1 ሺህ 771 ብረቶች እና 7 ሺህ 84 ብሎንና የብሎን ማሰሪያዎች በሌቦች ተሰርቀዋል፡፡ ሥርቆቱ በዋናነት የተፈጸመው ከገጣፎ - ቃሊቲ እና ከለገጣፎ - ሱልልታ በተዘረጉ ባለ 230 ኪሎ ቮልትመስመሮች እንዲሁም ከቃሊቲ - ገፈርሣ እና ከቃሊቲ - ወረገኑ በተዘረጉ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ነው፡፡ በዚህም ተቋሙ በ3 ወር ውስጥ ብቻ በተፈፀመ ስርቆት ምክንያት የተቋረጠውን የኢነርጅ መጠን ሳይጨምር ጉዳት ለደረሰባቸው የተለያዩ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ አካላት መልሶ መተኪያ 8 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ወጪ ማድረጉን ገልጿል፡፡ በጥገና ወቅት የሚያስፈልጉ የጉልበት ሠራተኛ፣ የነዳጅና የተለያዩ ግብዓቶችን ለማሟላት ደግሞ 720 ሺህ ብር ወጪ ማድረጉን ያስታወቀው ሪጅኑ ባለፉት ሶስት ወራት ብቻ በኤሌክትሪክ መሰረተልማት ስርቆት ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራ መድረሱን መምሪያው አመልክቷል፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ወንደሰን ወልደማርያም በሰጡት አስተያየት የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎችና ሽቦዎች ስርቆትን ለመከላከል በሚደረገው እንቅስቃሴ የፀጥታ አካላት ምላሽ ፈጣን አለመሆን ችግሩ እንዲባባስ ምክንያት ሆኗል። ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ተከሰው በሚቀርቡ ወንጀለኞች ላይ የፍትህ አካላት የሚጥሉት ቅጣት አስተማሪ አለመሆኑና ግብዓት ለማግኘት ሲሉ ስርቆቱን የሚደግፉና የሚረከቡ የብረታ-ብረት ፋብሪካዎችና ባለሀብቶች እንቅስቃሴ ሊፈተሽ እንደሚገባም ዳይሬክተሩ አሳስቧል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 08 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም 82 በመቶ ደርሷል .......////....... ለአዋሽ- ወልዲያ- ሀራ ገበያ የባቡር መስመር የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በመገንባት ላይ የሚገኘውን የማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቅ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ተክለወይኒ ብርሃነ እንደገለፁት በፕሮጀክቱ ላይ 206 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመር ግንባታ እና በመተሃራ፣ በደብረ ብርሃን፣ በሸዋ ሮቢት እና በከሚሴ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የማስፋፊያ ሥራዎች ይከናወናሉ። በፕሮጀክቱ ላይ ከሚተከሉ 553 የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች መካከል የ175 ምሶሶዎች ተከላ እና የ427 የምሰሶ መትከያ የመሠረት ቁፋሮ ሥራዎች መከናዎናቸውን አቶ ተክለወይኒ ተናግረዋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያዎቹ የማስፋፊያ ሥራ መጠናቀቁን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ የባቡር ጣቢያዎችን (Traction Station) ከተቋሙ የብሔራዊ የኃይል ቋት ጋር የሚያገናኙ የኮሙዩኒኬሽን መሳሪያዎችን ለማስቀመጥ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ፈቃድ እየተጠበቀ እንደሚገኝም አብራርተዋል፡፡ እንደ አቶ ተክለወይኒ ገለፃ ለፕሮጀክቱ ግንባታ ሥራ ከሚያስፈልጉ ዕቃዎች ውስጥ 84 ነጥብ 1 በመቶ የሚሆነው ተመርቶ ወደ ፕሮጀክቱ ሳይት የገባ ሲሆን የካሳ ክፍያ ሥራው ደግሞ 96 በመቶ ተጠናቋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያዎቹ የሙከራና የፍተሻ ሥራ በቅርቡ እንደሚከናወን ያነሱት አቶ ተክለወይኒ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀምም 82 በመቶ ደርሷል ብለዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በምድር ባቡር በኩል የሚከናወኑ የትራክሽን ጣቢያዎች ግንባታ አለመጠናቀቅና ወደ ተጠናቀቁ ጣቢያዎች ለመግባት የመግቢያ ፈቃድ አለመገኘቱ በፕሮጀክቱ የግንባታ እንቅስቃሴ ላይ ችግር እየፈጠረ ነው፡፡ ፕሮጀክቱን በማጠናቀቅ ለባቡር መስመሩ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን በኩል የሚከናወኑ ሥራዎች በወቅቱ ሊፈጸሙ እንደሚገባ አቶ ተክለወይኒ ጠቁመዋል፡፡ ከመተሃራ ማከፋፈያ ጣቢያ አስከ አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ድረስ ያለው የፕሮጀክቱ ሥራ በአካባቢው ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት ለአንድ ዓመት ያህል ተቋርጦ መቆየቱን ያስታወሱት አቶ ተክለወይኒ የግንባታ ሥራውን ለማስቀጠል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መግባባት ላይ በመደረሱ ተቋራጩ በቅርቡ ሥራውን እንደሚጀምር አስታውቀዋል፡፡ ፕሮጀክቱን በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቅ ርብርብ እየተደረገ ቢሆንም በፕሮጀክቱ ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት እና በአንዳንድ አካባቢዎች የሚስተዋለው የፀጥታ ችግር በተያዘለት መርሃ ግብር ለማጠናቀቅ እንቅፋት ሊሆኑ እንደሚችል ተናግረዋል። የፕሮጀክቱን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ፒንጋኦ ግሩፕ (Pinggao Group) እንዲሁም የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የማስፋፊያ ሥራን ቲ.ቢ.ኤ (TBEA,Co.Ltd) የተሰኙ ሁለት የቻይና ኩባንያዎች እያከናወኑት የሚገኝ ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ የሥራ ክፍል ደግሞ በማማከር ሥራው ላይ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡ የፕሮጀክቱ የፋይናንስ ወጪ ከ16 ነጥብ 85 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እና ከ174 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ሲሆን የፋይናንስ ወጪው ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የሚሸፈን ነው፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 07 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1