fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 533 مشترک است و جایگاه 8 368 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 174 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 533 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 30 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 10 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -6 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 24.86% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.87% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 862 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 620 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 9 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 01 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 533
مشترکین
-624 ساعت
-207 روز
+1030 روز
آرشیو پست ها
photo content
+1

photo content
+9

በማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቱ ላይ የስርቆት ወንጀል እየተፈፀመ ነው ………///……… 82 በመቶ የደረሰው የአዋሽ- ወልዲያ- ሀራ ገበያ የባቡር መስመር የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት ተደጋጋሚ ስርቆት እየተፈፀመበት መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ተክለወይኒ ብርሃነ እንዳስታወቁት በፕሮጀክቱ ላይ እስከ አሁን ከተተከሉ 175 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች መካከል በ37ቱ ላይ ስርቆት ተፈፅሞባቸዋል። ከመስከረም 2 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በተፈፀመው ስርቆት 6 ሺህ የሚሆኑ የምሰሶ ብረቶች ተፈተው የተወሰዱ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 262 የሚሆኑት በፖሊስ በኤግዚቢትነት ተይዘው እንደሚገኙ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ዱብዱብ በሚባል ቀበሌ በፕሮጀክቱ ላይ የተፈፀመው ስርቆት የግንባታ ሥራውን በተያዘለት ጊዜና በጀት ለማጠናቀቅ እንቅፋት እንደሚሆንም አመልክተዋል። አቶ ተክለወይኒ እንዳሉት ስርቆቱ ከተፈፀመ ጀምሮ ችግሩ በስፋት በሚስተዋልበት አካባቢ ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን የቁጥጥርና የጥበቃ ሥራ በመጀመሩ የስርቆት ወንጀሉ የመቀነስ አዝማሚያ አሳይቷል፡፡ ስርቆቱን በተቋሙ፣ በሥራ ተቋራጩ እና በፀጥታ አካላት ብቻ ማስቆም ስለማይቻል ህዝቡ በአካባቢው የተተከሉ የመስመር ተሸካሚ ምሶሶዎችን በእኔነትና በኃላፊነት ስሜት እንዲጠብቅ ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሆነም አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ፕሮግራም-2 የፕሮጀክት አስተዳደር-1 ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮናስ አባዲ በበኩላቸው በፕሮጀክቱ ላይ እየተፈፀመ ያለውን የስርቆት ወንጀል ለመከላከል ከፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ በስርቆቱ የተሳተፉ አካላትን በቁጥጥር ስር ለማዋል እና ህዝቡ ንብረቱን በሚጠብቅበት መንገድ ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር፤ በየደረጃው ካሉ የዞን፣ የወረዳና የከተማ የፀጥታ አካላት የተውጣጣ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ መገባቱን ተናግረዋል። የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ የግንባታ ሥራ ተቋራጭ ፒንጋኦ ግሩፕ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ዣይ በበኩላቸው በፕሮጀክቱ ላይ በተፈፀመው ስርቆት ምክንያት በአሁኑ ሰዓት የግንባታ ሥራውን በአግባቡ ማከናወን አልተቻለም ብለዋል። ከአንድ ምሶሶ ከ150 እስከ 200 የሚጠጉ ብረቶች ተፈተው እንደተወሰዱ የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ተሰርቀው የተወሰዱትን ብረቶች ለመተካት 12 ነጥብ 5 ማሊዮን ብር እንደሚጠይቅ ተናግረዋል። በፕሮጀክቱ ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት በወቅቱ መፍትሄ ካልተሰጠው ግንባታውን በተያዘለት በጀት እና ጊዜ አጠናቆ ለማስረከብ ፈታኝ እንደሚያደርገው እና የግንባታ እንቅስቃሴውን አደጋ ላይ እንደሚጥለውም የሥራ ኃላፊዎች አስገንዝበዋል። እስከ አሁን ከስርቆት ወንጀሉ ጋር በተገናኘ ሰባት ሰዎች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ እና ከዚህ ውስጥ አራቱ ከንብረቱ ጋር እጅ ከፈንጅ የተያዙ መሆናቸውን ከአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ፖሊስ ኮሚሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል። የአዋሽ - ወልዲያ - ሀራ ገበያ የባቡር መስመር የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት በመቶ ደርሷል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 06 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

የህፃናት ማቆያ ማዕከሉ 34 ህፃናትን ተቀብሎ እስተናገደ ነው ……..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህፃናት ማቆያ ማዕከል 34 የሰራተኞች ህፃናትን ተቀብሎ በማዋል ሴት ሰራተኞች በተረጋጋ ስሜት ሥራቸውን እንዲያከናዉኑ እያገዘ መሆኑን የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሲ ኢደኤ እንደተናገሩት ማዕከሉ የተቋሙን ሴት ሰራተኞች ህፃናት ልጆች ተቀብሎ ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 2፡00 ስዓት እስከ ቀኑ 11፡00 ስዓት ድረስ በመንከባከብ ላይ ይገኛል፡፡ ማዕከሉ በመቋቋሙ ሠራተኞቹ የስራ ጊዜያቸውን ሳያባክኑ እና ለልጆቻቸው ደህንነት ስጋት ሳይሰማቸው ስራቸውን በአግባቡ እንዲያከናውኑ እያገዘ ነው ብለዋል፡፡ የህፃናት ማቆያ ማዕከሉ ከ6 ወር እስከ 4 ኣመት ድረስ ላሉ የተቋሙ ሴት ሰራተኞች ልጆች የመኝታ፣ የመጫወቻ፣ የምግብና ሌሎች ተጨማሪ አገልግሎቶችን የሚሰጥ መሆኑ ደረጃውን የጠበቀ ማቆያ እንደሚያደርገው ወ/ሮ ሌንሴ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህፃናት ማቆያ ማዕከል 1 ነርስ እና ስድስት ልዩ ልዩ አገልግሎት የሚሰጡ ሠራተኞችን አሉት፡፡ ኮተቤ በሚገኘው አዲሱ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገነባው የህፃናት ማቆያ ማዕከል ሜክሲኮ ከነበረው የማቆያ ማዕከል ጋር ሲነፃፀር በዘመናዊ መልክ ከመገንባቱ ባሻገር ተቋሙ ለሰራተኖቹ የሰጠውን ትኩረት ያሳያል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ህይወታቸውን በኤች አይ ቪ/ኤድስ ላጡ የተቋሙ ሠራተኞች ልጆች የገንዘብ እገዛ እየተደረገ መሆኑን በመምሪያው የስርዓተ ፆታ ባለሙያ አቶ ተስፋዬ ዮሐንስ ገልፀዋል፡፡ እንደ ባለሙያው ገለፃ ከ 18 ዓመት በታች ለሆኑ የተቋሙ ሰራተኞች ልጆች በየወሩ 500 ብር ገንዘብ ድጋፍ እየተደረገ ነው፡፡ በዋናው መ/ቤትና በተለያዩ የተቋሙ የስራ አካባቢዎች የውይይት መድረኮችን በመፍጠር ሠራተኞች ስለ ቫይረሱ የተሻለ ግንዛቤ እያገኙ መሆናቸውን እና እያንዳንዱ የተቋሙ ሠራተኞች ከደመወዙ ላይ ተቆራጭ በማድረግ ኤች አይ ቪ በደማቸው የሚገኝ ሠራተኞችና ቤተሰቦታቸውን እንደሚደጉም ባለሙያው አስታውቀዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 06 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content