fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 533 مشترک است و جایگاه 8 338 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 162 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 533 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 29 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 6 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -1 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 25.10% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.85% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 901 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 619 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 8 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 30 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 533
مشترکین
-124 ساعت
-167 روز
+630 روز
آرشیو پست ها
photo content
+5

የዳሰነች ወረዳ አርብቶ አደሮች በተደረገላቸው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ መደሰታቸውን ገለፁ ....///.... የደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ የሲኤስ ክላስተር አርብቶአደሮች በተደረገላቸው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ መደሰታቸውን ገለፁ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍና ሥርጭት ክትትል ኮሚቴ በወረዳው የአየር ንብረት ለውጥ ባስከተለው የምግብ እጥረት ሳቢያ ድጋፍ የተደረገላቸውን የሲኤስ ክላስተር ባዮ ቀበሌ አርብቶ አደሮችን ጎብኝቷል። የቀበሌው ነዋሪ የሆኑት አቶ አብርሃም ምነ እንደተናገሩት የአየር ንብረት ለውጡ በሰዎችና በቤት እንስሳት ላይ የከፋ አደጋ ደቅኖ መቆየቱን አውስተዋል። የተደረገላቸው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ወቅቱን ያማከለ በመሆኑም ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና ሥርጭቱን ላከናወነው ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ምስጋናቸውን አቅርበዋል። አቶ ቦሀልባ ምነ የተባሉ የአካባቢው ነዋሪ በበኩላቸው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፉ መደረጉ ጥሩ መሆኑን ጠቅሰው ህፃናት ለሚበዙባቸው ቤተሰቦች ጭምር ሥርጭቱ መከናወኑን ገልፀዋል። እንደ እርሳቸው ገለፃ በቀበሌው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ያላገኙ ነዋሪዎች ቢኖሩም በጋራ የመካፈል ባህላችንን ተጠቅመን ድርቁን ለመከላከል ተችሏል። እስካሁን ለተደረገው የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ ምስጋናቸውን ያቀረቡት አቶ ቦሀልባ በቀጣይም ዘላቂ ድጋፍ እንደሚፈልጉ ተናግረዋል። ወ/ሮ ኦቾሎ ገልቴ በበኩላቸው የተደረገላቸው የበቆሎ ዱቄት ከዚህ በፊት እየፈጩ የሚጠቀሙበትን ጊዜና ጉልበት እንደቆጠበላቸው ተናግረዋል። በቀበሌው የተደረገው የአልሚ ምግቦች ድጋፍ የወለዱ እናቶችን ጤና  ከማሻሻሉም በላይ ልጆቻቸውን እንዲያጠቡ እንዳገዛቸውም ነው የገለፁት። በተያያዘ ዜና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአስቸኳይ ጊዜ ሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍና ሥርጭት ኮሚቴ ከዳሰነች ወረዳ አስተዳደር አመራሮች ጋር በሰብዓዊ እርዳታ ሥርጭቱ ላይ በቱርሚ ከተማ ውይይት አካሒዷል። በውይይቱ ላይ የሰብዓዊ እርዳታ ሥርጭቱን አፈፃፀም አስመልክቶ ገለፃ ያደረጉት የወረዳው ተወካይ አስተዳዳሪ አቶ ታደሰ ሎጎዲቴ እንደተናገሩት በወረዳው የሚገኙ 68 ሺህ 593 አርብቶአደሮች የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፉ ተጠቃሚ ሆነዋል። በወረዳው በሚገኙ 40 ቀበሌዎች የቀረበው የእርዳታ መጠንና  የተረጂ አርብቶ አደሮች ቁጥር አለመመጣጠን በሥርጭቱ ሥራ ላይ አሉታዊ ጫና ማሳደሩን አቶ ታደሰ ተናግረዋል።  እንደ ተወካይ አስተዳዳሪው ገለፃ በወረዳው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ከሃያ ሺህ በላይ አርብቶአደሮች ይገኛሉ። በ40 ቀበሌዎች የተከናወነው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ሥርጭት ፍትሐዊ በመሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ የወረዳው ምክር ቤት የቅርብ ክትትል ሲያደርግበት መቆየቱን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በወረዳው ላደረገው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ምስጋናቸውን የገለፁት አስተዳዳሪው በቀጣይም የወረዳው አርብቶ አደሮች በዘላቂነት ድጋፍ በሚያገኙበት ዙሪያ ላይ ከተቋሙ ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊዜያዊ የእርዳታ ድጋፍና ሥርጭት ኮሚቴ አባላት በበኩላቸው ተቋሙ በወረዳው ለሚገኙ አርብቶ አደሮች የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰዋል። ተቋሙ በወረዳው የሚገኙ አርብቶ አደሮችን በዘላቂነት ለማቋቋም የሚያስችል የማህበራዊ ልማት ዕቅድ ጥናት እያከናወነ መሆኑንም ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊዜያዊ እርዳታ ድጋፍና ሥርጭት ኮሚቴ በዛሬው ዕለትም በኛንጋቶም እና ሀመር ወረዳ የአስቸኳይ ጊዜ የእርዳታ ድጋፍ በተደረገላቸው አካባቢዎች የመስክ ምልከታ ያካሂዳል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 11 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

photo content
+6