ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 533 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 368 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 174 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 533 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 30 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 10، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -6، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 24.86‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.87‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 862 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 620 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 9.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 01 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 533
المشتركون
-624 ساعات
-207 أيام
+1030 أيام
أرشيف المشاركات
photo content
+5

የዳሰነች ወረዳ አርብቶ አደሮች በተደረገላቸው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ መደሰታቸውን ገለፁ ....///.... የደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ የሲኤስ ክላስተር አርብቶአደሮች በተደረገላቸው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ መደሰታቸውን ገለፁ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍና ሥርጭት ክትትል ኮሚቴ በወረዳው የአየር ንብረት ለውጥ ባስከተለው የምግብ እጥረት ሳቢያ ድጋፍ የተደረገላቸውን የሲኤስ ክላስተር ባዮ ቀበሌ አርብቶ አደሮችን ጎብኝቷል። የቀበሌው ነዋሪ የሆኑት አቶ አብርሃም ምነ እንደተናገሩት የአየር ንብረት ለውጡ በሰዎችና በቤት እንስሳት ላይ የከፋ አደጋ ደቅኖ መቆየቱን አውስተዋል። የተደረገላቸው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ወቅቱን ያማከለ በመሆኑም ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና ሥርጭቱን ላከናወነው ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ምስጋናቸውን አቅርበዋል። አቶ ቦሀልባ ምነ የተባሉ የአካባቢው ነዋሪ በበኩላቸው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፉ መደረጉ ጥሩ መሆኑን ጠቅሰው ህፃናት ለሚበዙባቸው ቤተሰቦች ጭምር ሥርጭቱ መከናወኑን ገልፀዋል። እንደ እርሳቸው ገለፃ በቀበሌው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ያላገኙ ነዋሪዎች ቢኖሩም በጋራ የመካፈል ባህላችንን ተጠቅመን ድርቁን ለመከላከል ተችሏል። እስካሁን ለተደረገው የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ ምስጋናቸውን ያቀረቡት አቶ ቦሀልባ በቀጣይም ዘላቂ ድጋፍ እንደሚፈልጉ ተናግረዋል። ወ/ሮ ኦቾሎ ገልቴ በበኩላቸው የተደረገላቸው የበቆሎ ዱቄት ከዚህ በፊት እየፈጩ የሚጠቀሙበትን ጊዜና ጉልበት እንደቆጠበላቸው ተናግረዋል። በቀበሌው የተደረገው የአልሚ ምግቦች ድጋፍ የወለዱ እናቶችን ጤና  ከማሻሻሉም በላይ ልጆቻቸውን እንዲያጠቡ እንዳገዛቸውም ነው የገለፁት። በተያያዘ ዜና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአስቸኳይ ጊዜ ሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍና ሥርጭት ኮሚቴ ከዳሰነች ወረዳ አስተዳደር አመራሮች ጋር በሰብዓዊ እርዳታ ሥርጭቱ ላይ በቱርሚ ከተማ ውይይት አካሒዷል። በውይይቱ ላይ የሰብዓዊ እርዳታ ሥርጭቱን አፈፃፀም አስመልክቶ ገለፃ ያደረጉት የወረዳው ተወካይ አስተዳዳሪ አቶ ታደሰ ሎጎዲቴ እንደተናገሩት በወረዳው የሚገኙ 68 ሺህ 593 አርብቶአደሮች የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፉ ተጠቃሚ ሆነዋል። በወረዳው በሚገኙ 40 ቀበሌዎች የቀረበው የእርዳታ መጠንና  የተረጂ አርብቶ አደሮች ቁጥር አለመመጣጠን በሥርጭቱ ሥራ ላይ አሉታዊ ጫና ማሳደሩን አቶ ታደሰ ተናግረዋል።  እንደ ተወካይ አስተዳዳሪው ገለፃ በወረዳው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ከሃያ ሺህ በላይ አርብቶአደሮች ይገኛሉ። በ40 ቀበሌዎች የተከናወነው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ሥርጭት ፍትሐዊ በመሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ የወረዳው ምክር ቤት የቅርብ ክትትል ሲያደርግበት መቆየቱን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በወረዳው ላደረገው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ምስጋናቸውን የገለፁት አስተዳዳሪው በቀጣይም የወረዳው አርብቶ አደሮች በዘላቂነት ድጋፍ በሚያገኙበት ዙሪያ ላይ ከተቋሙ ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊዜያዊ የእርዳታ ድጋፍና ሥርጭት ኮሚቴ አባላት በበኩላቸው ተቋሙ በወረዳው ለሚገኙ አርብቶ አደሮች የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰዋል። ተቋሙ በወረዳው የሚገኙ አርብቶ አደሮችን በዘላቂነት ለማቋቋም የሚያስችል የማህበራዊ ልማት ዕቅድ ጥናት እያከናወነ መሆኑንም ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊዜያዊ እርዳታ ድጋፍና ሥርጭት ኮሚቴ በዛሬው ዕለትም በኛንጋቶም እና ሀመር ወረዳ የአስቸኳይ ጊዜ የእርዳታ ድጋፍ በተደረገላቸው አካባቢዎች የመስክ ምልከታ ያካሂዳል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 11 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

photo content
+6