en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 533 subscribers, ranking 8 368 in the Technologies & Applications category and 2 174 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 533 subscribers.

According to the latest data from 30 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 10 over the last 30 days and by -6 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 24.86%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.87% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 862 views. Within the first day, a publication typically gains 2 620 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 01 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 533
Subscribers
-624 hours
-207 days
+1030 days
Posts Archive
photo content
+5

የዳሰነች ወረዳ አርብቶ አደሮች በተደረገላቸው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ መደሰታቸውን ገለፁ ....///.... የደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ የሲኤስ ክላስተር አርብቶአደሮች በተደረገላቸው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ መደሰታቸውን ገለፁ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍና ሥርጭት ክትትል ኮሚቴ በወረዳው የአየር ንብረት ለውጥ ባስከተለው የምግብ እጥረት ሳቢያ ድጋፍ የተደረገላቸውን የሲኤስ ክላስተር ባዮ ቀበሌ አርብቶ አደሮችን ጎብኝቷል። የቀበሌው ነዋሪ የሆኑት አቶ አብርሃም ምነ እንደተናገሩት የአየር ንብረት ለውጡ በሰዎችና በቤት እንስሳት ላይ የከፋ አደጋ ደቅኖ መቆየቱን አውስተዋል። የተደረገላቸው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ወቅቱን ያማከለ በመሆኑም ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና ሥርጭቱን ላከናወነው ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ምስጋናቸውን አቅርበዋል። አቶ ቦሀልባ ምነ የተባሉ የአካባቢው ነዋሪ በበኩላቸው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፉ መደረጉ ጥሩ መሆኑን ጠቅሰው ህፃናት ለሚበዙባቸው ቤተሰቦች ጭምር ሥርጭቱ መከናወኑን ገልፀዋል። እንደ እርሳቸው ገለፃ በቀበሌው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ያላገኙ ነዋሪዎች ቢኖሩም በጋራ የመካፈል ባህላችንን ተጠቅመን ድርቁን ለመከላከል ተችሏል። እስካሁን ለተደረገው የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ ምስጋናቸውን ያቀረቡት አቶ ቦሀልባ በቀጣይም ዘላቂ ድጋፍ እንደሚፈልጉ ተናግረዋል። ወ/ሮ ኦቾሎ ገልቴ በበኩላቸው የተደረገላቸው የበቆሎ ዱቄት ከዚህ በፊት እየፈጩ የሚጠቀሙበትን ጊዜና ጉልበት እንደቆጠበላቸው ተናግረዋል። በቀበሌው የተደረገው የአልሚ ምግቦች ድጋፍ የወለዱ እናቶችን ጤና  ከማሻሻሉም በላይ ልጆቻቸውን እንዲያጠቡ እንዳገዛቸውም ነው የገለፁት። በተያያዘ ዜና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአስቸኳይ ጊዜ ሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍና ሥርጭት ኮሚቴ ከዳሰነች ወረዳ አስተዳደር አመራሮች ጋር በሰብዓዊ እርዳታ ሥርጭቱ ላይ በቱርሚ ከተማ ውይይት አካሒዷል። በውይይቱ ላይ የሰብዓዊ እርዳታ ሥርጭቱን አፈፃፀም አስመልክቶ ገለፃ ያደረጉት የወረዳው ተወካይ አስተዳዳሪ አቶ ታደሰ ሎጎዲቴ እንደተናገሩት በወረዳው የሚገኙ 68 ሺህ 593 አርብቶአደሮች የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፉ ተጠቃሚ ሆነዋል። በወረዳው በሚገኙ 40 ቀበሌዎች የቀረበው የእርዳታ መጠንና  የተረጂ አርብቶ አደሮች ቁጥር አለመመጣጠን በሥርጭቱ ሥራ ላይ አሉታዊ ጫና ማሳደሩን አቶ ታደሰ ተናግረዋል።  እንደ ተወካይ አስተዳዳሪው ገለፃ በወረዳው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ከሃያ ሺህ በላይ አርብቶአደሮች ይገኛሉ። በ40 ቀበሌዎች የተከናወነው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ሥርጭት ፍትሐዊ በመሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ የወረዳው ምክር ቤት የቅርብ ክትትል ሲያደርግበት መቆየቱን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በወረዳው ላደረገው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ምስጋናቸውን የገለፁት አስተዳዳሪው በቀጣይም የወረዳው አርብቶ አደሮች በዘላቂነት ድጋፍ በሚያገኙበት ዙሪያ ላይ ከተቋሙ ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊዜያዊ የእርዳታ ድጋፍና ሥርጭት ኮሚቴ አባላት በበኩላቸው ተቋሙ በወረዳው ለሚገኙ አርብቶ አደሮች የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰዋል። ተቋሙ በወረዳው የሚገኙ አርብቶ አደሮችን በዘላቂነት ለማቋቋም የሚያስችል የማህበራዊ ልማት ዕቅድ ጥናት እያከናወነ መሆኑንም ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊዜያዊ እርዳታ ድጋፍና ሥርጭት ኮሚቴ በዛሬው ዕለትም በኛንጋቶም እና ሀመር ወረዳ የአስቸኳይ ጊዜ የእርዳታ ድጋፍ በተደረገላቸው አካባቢዎች የመስክ ምልከታ ያካሂዳል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 11 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

photo content
+6