fa
Feedback
ትምህርት መረጃ( academic info)

ትምህርት መረጃ( academic info)

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام ትምህርት መረጃ( academic info)

کانال ትምህርት መረጃ( academic info) (@academic_info) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 10 841 مشترک است و جایگاه 18 286 را در دسته آموزش و رتبه 3 070 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 10 841 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 31 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 390 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 15 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 58.12% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 19.21% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 6 300 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 082 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 8 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
@ትምህርት መረጃ( academic info) Telegram: https://t.me/academic_info Facebook: https://www.facebook.com/share/1EqNsbE4CN/ email: accadamicinfo@gmail.com Instagram:https://www.instagram.com/academicinfor?igsh=ZW8xc2J0MXdxdDVj

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 01 اوت, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کرده‌اند.

10 841
مشترکین
+1524 ساعت
+1267 روز
+39030 روز
آرشیو پست ها
በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ ተማሪዎች እና የሚያስተምሩ መምህራን ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ እንዲዘዋወሩ ጥያቄ ማቅረባቸው ተሰማ። በትግራይ በሚገኙ አራት የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ
በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ ተማሪዎች እና የሚያስተምሩ መምህራን ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ እንዲዘዋወሩ ጥያቄ ማቅረባቸው ተሰማ። በትግራይ በሚገኙ አራት የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ የተወሰኑ ተማሪዎች እና መምህራን በክልሉ ባለው የጸጥታ ስጋት ምክንያት ወደ ሌሎች የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲዛወሩ ጥያቄ እያቀረቡ እንደሚገኝ ተሰምቷል። በመቐለ፣ አክሱም፣ ዓዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎች እና የሚያስተምሩ መምህራን ጥያቄያቸውን ለመንግሥት እያቀረቡ ነው። ተማሪዎች እና መምህራን በክልሉ በሚታየው የጸጥታ ስጋት ምክንያት የቅሬታ ጥያቄ እያስገቡ ሲሆን፤ እስካሁን ከትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠ የዝውውር ውሳኔም ሆነ የተገባ ቃል አለመኖሩን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ኅብረት ፕሬዝዳንት ሓየሎም ስዩም ገልፀዋል። @ትምህርትመረጃ

የቅጥር ማስታወቂያ ከአዲስአበባ ዩንቨርስቲ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሞዴል ኮሚኒቲ ትምህርት ቤት (AAU-MCS) ለተለያዩ የሥራ መደቦች ፍላጎት ያላቸውና ብቁ የሆኑ ባለሙያዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ ትምህርት ቤቱ ከ2019 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ለአንደኛ ደረጃ (ከ1ኛ እስከ 7ኛ ክፍል) ተማሪዎች ከፍተኛ ጥራት ያለው ትምህርት ለመስጠት አቅዷል፡፡ ዝርዝር የሥራ መደቦችና የማመልከቻ ሁኔታ ለማግኘት 👇 https://www.aau.edu.et/announcements/detail?title=Vacancy~Announcement~AAU-MCS ➤ የሥራ መደብ፦ በተለያዩ ሙያዎች ➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 70 ➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪ (ለተወሰኑ የሥራ መደቦች ዲፕሎማ፣10ኛ እና 12ኛ ክፍል ተጠይቋል፡፡) ➤ የሥራ ቦታ፦ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 5 ኪሎ ➤ የቅጥር ሁኔታ፦ በሙሉ ጊዜ የተገለፁ መስፈርቶችን የምታሟሉ በሙሉ የማመልከቻ ደብዳቤ፣ CV፣ ሙሉ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውና የማይመለስ ኮፒ እንዲሁም አስፈላጊ ሰርተፊኬቶችን በመያዝ እስከ ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም ድረስ በሥራ ቀናት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ የሰው ሃብት ቢሮ በመገኘት ማመልከት ትችላላችሁ ተብሏል፡፡   (ዝርዝር የሥራ መደቦቹ እና መስፈርቶችን ከተያያዘው ፒዲኤፍ ይመልከቱ፡፡)

የመምህርነት የስራ ቅጥር ማስታወቂያ! (ሀምሌ 21/2018 ዓ.ም) መመዝገቢያ ሊንኮች 1. ለ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች https://docs.google.com/forms/d/1RRFzFMb2HEoCyRp_y
+3
የመምህርነት የስራ ቅጥር ማስታወቂያ! (ሀምሌ 21/2018 ዓ.ም) መመዝገቢያ ሊንኮች 1. ለ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች https://docs.google.com/forms/d/1RRFzFMb2HEoCyRp_ye5E-joooyGYzpAMfEvFBQdbJJs/edit 2. ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ 8ኛ ክፍል ላሉ ትምህርት ቤቶች https://docs.google.com/forms/d/1exSs8OJs3UzYpyzcqQ8e13-JiczbyGR1ohmYFpdHJOY/edit 3. Barnoota Sadarkaa 1ffaan duraa hanga kutaa 8ffaa isa jala jiraniif Bara Barnootaa https://docs.google.com/forms/d/1UXIAIH736rY4YoENoRNSmNsYkZsOJFrh6o7-G3qz53E/edit ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

What Do you think about Grade 12 national exam passing rate? comparing with last year
Anonymous voting

የትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶችን የአንድ ጊዜ የስራ ዘመን 6 ዓመት እንዲሆን የሚያዝ መመሪያ አውጥቷል። 👉 በመመሪያው ድንጋጌ መሰረት ለፕሬዝዳንትነትና የሚወዳደሩ ወንድ እጩዎች ቢያንስ የረዳት ፕሮፌሰርነትና ከዚያ በላይ የአካዳሚክ ማዕረግ ሊኖራቸው ይገባል። የየትምህርት ሚኒስቴር በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚሾሙ ፕሬዝዳንቶችና ምክትል ፕሬዝዳንቶች አሰያየምን የሚገዛ አዲስ መመሪያ (መመሪያ ቁጥር 1146/2018) ይፋ አድርጓል። ይህ መመሪያ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የነበረውን የአመራር አሰያየም ስርአት በመቀየር፣ በብቃትና በውድድር ላይ የተመሰረተ አሰራርን ለማስፈን ያለመ መሆኑን ይገልጻል። በአሁኑ ወቅት ዩኒቨርሲቲዎች በርካታ የሪፎርም ስራዎች ላይ እንደሚገኙ የገለጸው ሚኒስቴሩ፣ እነዚህን ለውጦች ለመምራት በሙያቸው የበሰሉ፣ በስነ-ምግባር የታነጹና በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ዘንድ ቅቡልነት ያላቸው አመራሮች እንደሚያስፈልጉ አጽንኦት ሰጥቷል። አዲሱ መመሪያ የአመራር ምርጫውን ግልጽ በሆነ የነጥብ ድልድል (30/30/40) እንዲመራ ደንግጓል። በዚህም መሰረት የትምህርት ዝግጅትና አካዳሚክ ማዕረግ 30 በመቶ ነጥብ የሚያዝበት ሲሆን ለፕሬዝዳንትነትና ለምክትል ፕሬዝዳንትነት የሚወዳደሩ እጩዎች ያላቸው የትምህርት ደረጃና የአካዳሚክ ማዕረግ ይመዘናል(ማዕረጉ ከፍ ባለ ቁጥር (ለምሳሌ ፕሮፌሰር) የሚያገኙት ነጥብ ከፍ ይላል)። የስራ ልምድም በተመሳሳይ 30 በመቶ ነጥብ የሚያዝበት ሲሆን እጩዎች በተቋም ግንባታና በአመራርነት ያሳለፉት ጊዜ በዝርዝር ተሰልቶ ነጥብ ይሰጠዋል። ሌላው በአመራር ምርጫ ወቅት ትልቁን ነጥብ የሚያዝበት ጉዳይ ስትራቴጂያዊ ዕቅድና አቀራረብ (40 በመቶ) ነው። ተወዳዳሪዎች የተቋሙን ችግሮች እንዴት እንደሚፈቱና ወደፊት እንዴት እንደሚመሩ

ትምህርት ሚኒስቴር በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና አዲስ ማዕቀፍ አዘጋጅቷል። ማዕቀፉ መምህራን በክረምት ስልጠና ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የሚሸጋገሩበት መሆኑ ተገልጿል። ሚ
ትምህርት ሚኒስቴር በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና አዲስ ማዕቀፍ አዘጋጅቷል። ማዕቀፉ መምህራን በክረምት ስልጠና ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የሚሸጋገሩበት መሆኑ ተገልጿል። ሚኒስቴሩ በቀን 06/11/2018 ዓ.ም ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ፣ ከአጠቃላይ ትምህርት ሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ጋር ተያይዞ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ማስገባት መቋረጡን አስታውሷል፡፡ ይሁን እንጂ በቀጣይ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት በተዘጋጀ የስልጠና ማዕቀፍ፣ በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል። በ2018 ዓ.ም የክረምት ስልጠናውን ለመስጠት ስምንት አሰልጣኝ ዩኒቨርሲቲዎች መመረጣቸውን ሚኒስቴሩ አሳውቋል። ለክረምት ስልጠናው የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች፦ 1. ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ 2. ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ 3. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 4. መቐለ ዩኒቨርሲቲ 5. ጅማ ዩኒቨርሲቲ 6. ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ 7. ጎንደር ዩኒቨርሲቲ 8. አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተቋማት እና የስልጠናው አሰጣጥ አግባብነት ከትምህርት ሚኒስቴር እስከሚገለጽ ድረስ ከላይ ከተገለፁት ዩኒቨርሲቲዎች በስተቀር በክረምት መምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና መስጠት የማይቻል መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳስቧል። ከ2011 ዓ.ም በፊት ስልጠና ጀምረው ያላጠናቀቁ መምህራን ከዚህ በፊት በተሰጠው ውሳኔ መሰረት እንዲያጠናቅቁ እንዲደረግ በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተላከው ደብዳቤ ይገልጻል።

forecast correctly? the winer
forecast correctly? the winer

ረቂቅ መመሪያው COC ሳይፈተኑ ዲግሪ ለወሰዱ ከ2010 እስከ 2015 ዓ.ም ተመራቂዎች የተዘጋጀ ነው። - የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ም/ዋ/ዳይሬክተር ከመስከረም 2ዐ1ዐ ዓ.ም እስከ 2015 ዓ.
ረቂቅ መመሪያው COC ሳይፈተኑ ዲግሪ ለወሰዱ ከ2010 እስከ 2015 ዓ.ም ተመራቂዎች የተዘጋጀ ነው። - የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ም/ዋ/ዳይሬክተር ከመስከረም 2ዐ1ዐ ዓ.ም እስከ 2015 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ የመውጫ ፈተና ሳይፈተኑ የመጀመሪያ፣ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ዲግሪ የያዙ ተመራቂዎች የመውጫ (COC) ፈተና እንዲፈተኑ የሚያደርግ ረቁቅ መመሪያ በትምህርት ሚኒስቴር ተዘጋጅቷል። በረቂቅ ማሻሻያው ላይ የትምህርት ማኅበረሰቡ እና ባለድርሻ አካላት አስተያየት እንዲሰጡበት የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን መጠየቁ ይታወቃል። COC ሳይፈተኑ ዲግሪ የወሰዱ ከ2010 እስከ 2015 ዓ.ም ተመራቂዎች ሲባል ረቂቅ መመሪያው መዘጋጀቱን የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሽሻይ አማረ (ዶ/ር) ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ ከዲፕሎማ ወደ ዲግሪ ትምህርት ለመቀጠል የሲኦሲ ማረጋገጫ መኖር አንዱ መሠረታዊ መስፈርት ቢሆንም፣ ይህ ሳይሟላ ቀርቶ ለማረጋገጥ የተቸገሩ በመኖራቸው፣ መፍትሔ ለማግኘት ሲባል ረቂቅ ማሻሻያው መዘጋጀቱን ገልፀዋል። ባለሥልጣኑ መመርያውን ተፈጻሚ የሚያደርጉት ባለድርሻ አካላት በመሆናቸው የሚመለከታቸው በሙሉ በረቂቁ ላይ ያላቸውን ሃሳብና ማሻሻያ እስከ ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም በተዘጋጀ ድረ-ገፅ አስተያየት እንዲሰጡ መጠየቁን ጠቁመዋል፡፡ ማሻሻያው በዋናነት ለዲግሪ መግቢያ መስፈርት የተቀመጠውን የደረጃ አራት የብቃት ማረጋገጫ ፈተና ሳይወስዱ በቀጥታ በዲግሪ ተምረው የተመረቁትን ወይም በዲግሪ ለመማር ከተመዘገቡ በኋላ የደረጃ አራት የብቃት ማረጋገጫ ፈተና የወሰዱትን፣ በአገር ውስጥ በሚንቀሳቀሱ ማናቸውም የመንግሥት እና የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያለፉ ተመራቂዎችን በሙሉ እንደሚያጠቃልል በመመሪያው ተገልጿል።

አንድ የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ራስ-ገዝ ለመሆን በሁሉም ፕሮግራሞች ለሦስት ተከታታይ ዓመታት 80 በመቶ ተማሪዎቹን በመውጫ ፈተና ማሳለፉን እንደ አንድ አካዳሚክ መመዘኛ ነጥብ የሚይዝ መመሪያ ትምህርት ሚኒስቴር አውጥቷል።ማንኛውም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ለመሆን በመመዘኛ ነጥቦቹ 60 በመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅበታል የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ካሉባቸው የአደረጃጀት እና የአሰራር ውሱንነቶች ወጥተው፣ ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድሩ የሚያስችላቸውን “የመንግስት ዩኒቨርሲቲ የራስ-ገዝነት የሽግግር መምረጫ መመሪያ ቁጥር 1143/2018” አውጥቷል። ትምህርት ሚኒስቴር መመሪያውን ማውጣት ያስፈለገበትን ምክንያት ሲያስረዳ፤ እስካሁን በነበረው አሰራር ዩኒቨርሲቲዎች በቂ ተቋማዊ ነፃነት ባለመኖሩ ምክንያት የመማር ማስተማር፣ የምርምር እና የማህበረሰብ አገልግሎት ተልዕኮዎቻቸውን በአግባቡ ለመወጣት እንቅፋት ሆኖባቸው መቆየቱን ገልጿል። በመሆኑም ተቋማቱ ከመንግስት ጣልቃ ገብነት ነፃ ሆነው በሰው ኃይል፣ በሀብት አጠቃቀም እና በአካዳሚክ ጉዳዮች ላይ ራሳቸውን እንዲያስተዳድሩ ማስቻል አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ገልጿል። ይህ መመሪያ በራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ አዋጅ ቁጥር 1294/2015 አንቀጽ 5 እና 45 መሠረት የተዘጋጀ ነው። እንደ መመሪያው ገለጻ፣ አንድ የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር በአራት ዋና ዋና አምዶች ላይ ተመስርቶ ግምገማ ይደረግበታል። እነዚህም አስተዳደር (30%)፣ ፋይናንስ (20%)፣ የሰው ኃይል (15%) እና አካዳሚክ (35%) ጉዳዮች ናቸው። የሽግግር ሂደቱም በተጨባጭ መረጃ፣ በላቀ ብቃት፣ በውጤታማነት፣ በአካታችነት፣ በግልጽነት እና በተጠያቂነት መርሆዎች ላይ ተመስርቶ የሚከናወን ይሆናል። ዩኒቨርሲቲዎች ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ለመሸጋገር በዝግጅት ምዕራፍ ወቅት ቢያንስ 60 በመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል። በመመሪያው ላይ በዝርዝር የተቀመጡ እና ተቋማቱ ሊያሟሏቸው የሚገቡ መመዘኛዎች መስፈርቶች መካከል:- • ተቋማቱ ቢያንስ 15 በመቶ የሚሆኑ የመማሪያ ክፍሎቻቸውን ወደ “ስማርት ክላስሩም” የቀየሩ • 80 በመቶ እና ከዚያ በላይ የሚሆኑ ተማሪዎቻቸው ብሄራዊ የመውጫ ፈተናን ያለፉ •ቢያንስ 5 በመቶ የሚሆኑ የትምህርት ፕሮግራሞቻቸው ዓለም አቀፍ እውቅና (Accreditation) ማግኘታቸው እና የዲጂታል ቤተ-መጽሐፍት አገልግሎታቸው ከ70 በመቶ በላይ መድረስ አለበት • አንድ ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር ላለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት የሂሳብ ምርመራ (Audit) ያስደረገና የኦዲት ግኝቱም “ንጹህ” (Unqualified) ወይም አስተያየት ያልተሰጠበት መሆን ይኖርበታል። • ተቋሙ ካለው አጠቃላይ በጀት ውስጥ ቢያንስ 15 በመቶውን ከውስጥ ገቢና ከውጭ የገቢ ምንጮች መሸፈን ይጠበቅበታል። • ለገቢ ምንጭነትም ቢያንስ አምስት እና ከዚያ በላይ የገቢ ማመንጫ ዘርፎችን ወደ ስራ ማስገባት እንደ ግዴታ ተቀምጧል። • የዩኒቨርሲቲው መምህራን የትምህርት ደረጃ ስብጥር 0፡ 60፡ 40 (የመጀመሪያ ዲግሪ 0%፣ ሁለተኛ ዲግሪ 60% እና ሦስተኛ ዲግሪ 40%) መድረስ እንዳለበት ተደንግጓል። • በተጨማሪም የአካዳሚክ ማዕረግ ስብጥሩ ሌክቸረር 46%፣ ረዳት ፕሮፌሰር 31%፣ ተባባሪ ፕሮፌሰር 20% እና ፕሮፌሰር እና ከዚያ በላይ 3% መሆኑ መረጋገጥ ይኖርበታል። • ተቋማቱ በምርምር ዘርፍ ያላቸውን ጥንካሬ ለማሳየትም ቢያንስ አምስት እና ከዚያ በላይ የሆኑ የአእምሯዊ ንብረት መብት (IP) ባለቤት መሆን እንዳለባቸው በመመሪያው ተመላክቷል። • ተቋማዊ አገልግሎትንና የተገልጋይ እርካታን በተመለከተም፣ ዩኒቨርሲቲዎች በመምህራን፣ በሠራተኞችና በተማሪዎች ዘንድ ቢያንስ 75 በመቶ የእርካታ ደረጃ ማረጋገጥ ይጠበቅባቸዋል። • ከአካባቢው ማህበረሰብና ከኢንዱስትሪ ተዋንያን ጋር ባላቸው ግንኙነት ደግሞ የ70 በመቶ የእርካታ ደረጃን በጥናት ማሳየት ይኖርባቸዋል። • በቴክኒክ ረገድም ካሏቸው ቤተ-ሙከራዎች (Laboratories) ውስጥ 10 በመቶ የሚሆኑት፣ ከወርክሾፖቻቸው ደግሞ 5 በመቶው በዓለም አቀፍ ስታንዳርድ የተደራጁ መሆናቸው በሽግግር ግምገማው ወቅት ትልቅ ዋጋ ይሰጠዋል። የሽግግር ሂደቱ በሁለት ደረጃዎች የሚከናወን ሲሆን፣ መጀመሪያ ዩኒቨርሲቲው በራሱ ኮሚቴ አማካኝነት የውስጥ ግለ-ግምገማ (Self-assessment) ያካሂዳል ይህ ግምገማ በዩኒቨርሲቲው ስራ አመራር ቦርድ ጸድቆ ለትምህርት ሚኒስቴር ይቀርባል። ሚኒስቴሩ የቀረበለትን ሪፖርት መነሻ በማድረግ በገለልተኛ ባለሙያዎች የታገዘ የመስክ ምልከታና ማረጋገጫ ከሰጠ በኋላ፣ መስፈርቱን አሟልተው ለተገኙ ተቋማት ወደ ራስ-ገዝነት እንዲሸጋገሩ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት የውሳኔ ሃሳብ ያቀርባል። ወደ ራስ-ገዝነት የተሸጋገረ ዩኒቨርሲቲ የሽግግር ጊዜው ለሁለት ተከታታይ ዓመታት የሚቆይ ሲሆን፣ በዚህ ጊዜ ውስጥ ተቋማዊና አካዳሚክ ነፃነቱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል አቅም ይገነባል። ይሁን እንጂ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ መግባት ካልቻለ፣ ሚኒስቴሩ ተጨማሪ ጊዜ ሊሰጠው ወይም ከቦርዱ ጋር በመመካከር ሌሎች ውሳኔዎችን ሊያስተላልፍ እንደሚችል መመሪያው ደንግጓል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ መመሪያ በፍትህ ሚኒስቴር ተመዝግቦ የጸደቀ መሆኑን ከትምህርት ሚኒስቴር አረጋግጧል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ @tikvahethiopia

የእራስን እድል በራስ የመወሰን መብት..‼ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ዛሬ ይፋ ያደረጓቸው 8 ዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎችን:- በዚህ መሠረት 1.የሀገር ግንባታ 2.የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ የፖለቲካ ውክልና የምርጫ ሥርአት ጉዳዮች 3.የፌድራል ከተሞች አዲስአበባ እና ድሬዳዋ ጉዳይ 4.የሃይማኖት ጉዳዮች 5.የተቋማት ግንባታ የህግ የበላይነትና የሰብአዊ መብቶች 6.ማህበራዊና ኢኮኖሚ እንዲሁም የአርሶአደር እና አርብቶ አደር ጉዳዮች 7.ሙስና እና መልካም አስተዳደር 8.ሰላም ግንባታ 📌በኮሚሽኑ የተለዩት 8 አጀንዳዎች እያንዳንዳቸው በስራቸው ዝርዝር ንዑስ ጉዳዮችን አካተዋል ብለዋል። ለምሳሌ በ1ኛው አጀንደ ስር አጀንዳ ቁጥር 1 1. የሀገር ግንባታ    1.1. የማንነት እና የሀገር ባለቤትነት ጉዳዮች    እዛው ስር 2. ታሪክ እና ማንነት 2. የጋራ ሀገራዊ ማንነት እና እሴቶች... እሴቶችን የሚመለከቱ ጉዳዮች    እዚያው ስር 4. ሀገር ግንባታ እና ብዙሀንነት አስተዳደር ጉዳዮች 3. የቋንቋ ጉዳዮች    1.6. የባህል ታሪክ እና... ታሪክ እና ቅርስ ጥበቃ ጉዳዮች እንዲሁም ሌሎችም በርካታ ጉዳዮች አጀንዳ ቁጥር 2 2. የመንግስት አደረጃጀት እና ቅርፅ እንዲሁም የፖለቲካ ስርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ስርዓት    2.1. የመንግስት አደረጃጀት እና ቅርፅ    2.1.1. የመንግስት አደረጃጀት አስተዳደር ስርዓት አይነት    2.1.2. እራስን እድል በራስ የመወሰን መብት፤ በቅንፍ ውስጥ ሰላሳ ዘጠኝ እዝባር አንድ (39/1)    2.1.3. የብሄር ብሄረሰቦች ትርጓሜ፤ አንቀፅ ሰላሳ ዘጠኝ እዝባር አምስት (39/5) — ህገ-መንግስቱን... ህገ-መንግስቱን ማለቴ ነው    2.1.4. የፌደራል መንግስት እና የክልል መንግስታት መሪዎች የስልጣን ዘመን    2.1.5. የፌደራል እና የክልል መንግስታት ግንኙነት    እዚያው ስር፡ የስልጣን ክፍፍል የፌደራል እና የክልል መንግስት    እዚያው ስር አሁንም፡ የፊስካል ፌደራሊዝም እና የሀብት ክፍፍል    2.1.6. የክልል አስተዳደር እና ወሰኖች    እዚያው ስር፡ የአዳዲስ ክልሎች አመሰራረት    እዚያው ስር፡ የክልል አስተዳደራዊ ወሰኖች    2.1.7. የህግ አውጪው አካል ወይም ፓርላማ መዋቅር እና miና    2.1.8. ህገ-መንግስትን የመተርጎም ስልጣን    2.1.9. የህገ-መንግስት ማሻሻያ ስርዓት፤ አንቀፅ አንድ መቶ አራት (104) እና አንድ መቶ አምስት (105)    2.2. የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ስርዓት ጉዳዮች    ከስሩ 2.2.1. የሀገሪቱ የምርጫ ስርዓት    2.2.2. የመድብለ ፓርቲ ስርዓት    2.2.3. የፖለቲካ ፓርቲ አደረጃጀት    2.2.4. የመንግስት እና የገዢ ፓርቲ ሚና መለያየት    2.2.5. የምርጫ ክልሎች አወቃቀር    2.2.6. የፖለቲካ ፓርቲዎች የመንግስት ሀብት አጠቃቀም አጀንዳ ቁጥር 3 3. የፌደራል ከተሞች (አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ)    3.1. የአዲስ አበባ ጉዳይ    3.1.1. የአዲስ አበባ ህጋዊ አቋም    እዚያው ስር፡ አዲስ አበባ ከኦሮሚያ ክልል ጋር ያለው ግንኙነት    ከዚያው ስር፡ የአዲስ አበባ ከተማ የበጀት ድርሻ ጉዳይ    3.1.2. የፌደራል ዋና ከተማ ጉዳይ    3.1.3. የአዲስ አበባ ፖሊስ እና ፍርድ ቤት ጉዳይ    3.1.4. የአዲስ አበባ ወሰን እና የቦታዎች ስያሜዎች    3.1.5. የአዲስ አበባ ከተማ የስራ ቋንቋ    3.1.6. የአዲስ አበባ ከተማ ታሪካዊ ቅርሶች አካታችነት ጉዳይ    ...3.2. የድሬዳዋ ጉዳይ ....... አጀንዳዎቹ  ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በአገር አቀፍ ደረጃ በአዲስ አበባ በሚካሄደው ጉባዔ ላይ የሚመከርባቸው ናቸው፡፡

ውጤትዎን ይመልከቱ! ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት መታየት ጀምሯል። ውጤትዎን ለማየት 👇 https://result.
ውጤትዎን ይመልከቱ! ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት መታየት ጀምሯል። ውጤትዎን ለማየት 👇 https://result.ethernet.edu.et ሊንኩን ከተጫኑ በኋላ 'Exit Examination' ላይ 'View Results' የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ።

🔥 በ7ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ አሸናፊዎች መልካም የስራ ዘመን ተመኘን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ውጤት ይፋ አድርጓል። በተገለጹት ውጤቶች መሰረት ብልጽግና ፓርቲ በአብዛኞቹ ክልሎች የፓርላማ መቀመጫዎችን በመቆጣጠር ዋና አሸናፊ ሆኖ ተገኝቷል። አጠቃላይ የፓርላማ ምርጫ ውጤቶች 1. አዲስ አበባ ከተማ (23 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 20 መቀመጫዎች - ኢዜማ – 2 መቀመጫዎች - የግል ዕጩ – 1 መቀመጫ 2. አፋር ክልል (8 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 7 መቀመጫዎች - የአፋር ህዝብ ፓርቲ – 1 መቀመጫ 3. አማራ ክልል (130 መቀመጫዎች ላይ ምርጫ የተካሄደ) - ብልጽግና ፓርቲ – 117 መቀመጫዎች - አብን – 6 መቀመጫዎች - አዲህን – 3 መቀመጫዎች - አርጎባ አንድነት ጀበርቲ ፓርቲ – 1 መቀመጫ - ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት – 1 መቀመጫ - ኢዜማ – 1 መቀመጫ - ነጻነትና እኩልነት – 1 መቀመጫ 4. ቤኒሻንጉል ጉሙዝ (9 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 8 መቀመጫዎች - ጉሙዝ ብሔራዊ ንቅናቄ – 1 መቀመጫ 5. ድሬዳዋ (2 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 2 መቀመጫዎች 6. ጋምቤላ ክልል (3 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 3 መቀመጫዎች 7. ኦሮሚያ ክልል (173 መቀመጫዎች ላይ ውጤት ይፋ የሆነ) - ብልጽግና ፓርቲ – 167 መቀመጫዎች - የግል ዕጩዎች – 5 መቀመጫዎች - አዲስ ትውልድ ፓርቲ – 1 መቀመጫ 8. ሐረሪ ክልል (2 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 2 መቀመጫዎች 9. ሲዳማ ክልል (16 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 13 መቀመጫዎች - መድረክ – 3 መቀመጫዎች 10. ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ (20 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 17 መቀመጫዎች - ኢዜማ – 1 መቀመጫ - ነጻነትና እኩልነት – 1 መቀመጫ - ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት – 1 መቀመጫ 11. ደቡብ ኢትዮጵያ (45 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 35 መቀመጫዎች - ኢዜማ – 7 መቀመጫዎች - የጌድዮ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ – 1 መቀመጫ - የወላይታ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ – 1 መቀመጫ - የግል ዕጩ – 1 መቀመጫ 12. ማዕከላዊ ኢትዮጵያ (33 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 28 መቀመጫዎች - ኢዜማ – 2 መቀመጫዎች - የግል ዕጩ – 1 መቀመጫ - ትብብር ለኢትዮጵያ – 1 መቀመጫ - ነጻነትና እኩልነት – 1 መቀመጫ 13. ሶማሌ ክልል (22 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 19 መቀመጫዎች - የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር – 1 መቀመጫ - ሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ – 1 መቀመጫ - ህብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት ፓርቲ – 1 መቀመጫ ማስታወሻ በትግራይ ክልል በ38 የፓርላማ መቀመጫዎች ምርጫ አለመካሄዱ ይታወቃል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ውጤት - ብልጽግና ፓርቲ – 144 መቀመጫዎች - ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት – 12 መቀመጫዎች - ኢዜማ – 10 መቀመጫዎች - ነጻነትና እኩልነት – 3 መቀመጫዎች - የወሎ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት – 1 መቀመጫ በአጠቃላይ የ7ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ውጤት ብልጽግና ፓርቲ በአብዛኞቹ ክልሎች ከፍተኛ ድል ማስመዝገቡን ያሳያል። በተለይም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ከ20 የፓርላማ መቀመጫዎች 17ቱን በማሸነፍ የበላይነቱን አረጋግጧል። መልካም የስራ ዘመን!

Humanitarian Consequences The crisis is not only an educational emergency but also a humanitarian emergency. Conflict has displaced hundreds of thousands of people in Amhara and severely disrupted access to basic services. Humanitarian agencies have repeatedly warned that insecurity continues to hinder relief efforts and threatens the well-being of millions of civilians. (GOV.UK) Appeal to the International Community The international community must not overlook the plight of children in the Amhara Region. Immediate action is needed to: Support the safe reopening of schools. Rehabilitate and reconstruct damaged educational facilities. Provide emergency learning opportunities for displaced children. Protect children from child labor and exploitation. Prevent child marriage and support vulnerable girls. Expand psychosocial and mental health services for conflict-affected children. Increase humanitarian assistance for families affected by conflict and displacement. Promote peaceful solutions that allow children to return safely to school. Conclusion The children of Amhara are paying the highest price for a conflict they did not create. Millions have lost access to education, many are entering child labor, and others face the threat of early marriage. Every day that schools remain closed is another day stolen from their future. The world must act urgently to ensure that these children are protected, educated, and given the opportunity to rebuild their lives in peace. (Africa Press English) "Every child has the right to learn, to be safe, and to dream of a better future. The children of Amhara deserve nothing less."

Below is a formal English briefing that you can share with international organizations, donors, human rights groups, media outlets, and the global community. The Education Crisis Facing Children in Ethiopia's Amhara Region A Call for International Attention and Action The ongoing conflict in Ethiopia's Amhara Region has created one of the most severe child protection and education crises in the country. Millions of children have been forced out of school due to insecurity, displacement, destruction of educational infrastructure, and the prolonged disruption of public services. As a result, many children are now exposed to child labor, early marriage, poverty, exploitation, and long-term social and psychological harm. Massive School Closures and Educational Disruption According to reports from UNICEF, the United Nations Office for the Coordination of Humanitarian Affairs (UNOCHA), and other humanitarian organizations, the education sector in Amhara has been devastated by conflict. More than 4.1 million children in the Amhara Region have been pushed out of school, while thousands of schools have been closed, damaged, destroyed, or rendered non-functional due to insecurity. (Xinhua News) Recent humanitarian reports indicate that approximately 4.4 million children in Amhara are currently out of school. More than 5,000 schools have been damaged, and thousands remain closed because of ongoing violence and instability. (GOV.UK) The United Nations Children's Fund (UNICEF) has also reported that conflict and displacement have contributed to a nationwide education emergency, with Amhara among the regions most severely affected. More than 10,000 schools across Ethiopia have been damaged by conflict and climate shocks, while over 9 million children are out of school nationwide. (China.org.cn) Rising Child Labor As families struggle to survive amid economic hardship and displacement, many children who should be attending school are instead working to support their households. In both rural and urban areas, children are increasingly engaged in daily labor activities, including agricultural work, street vending, transportation services, domestic labor, and other informal employment. When schools remain closed for extended periods, children lose not only educational opportunities but also protection from exploitation. The longer they remain outside the education system, the greater the risk that they will never return to school. Increased Risk of Child Marriage Girls are among the most vulnerable victims of the crisis. Humanitarian organizations have warned that conflict, poverty, displacement, and school closures significantly increase the likelihood of child marriage. UNICEF has documented that emergencies such as conflict and drought often lead families to resort to child marriage as a coping mechanism for economic survival. Reports indicate rising risks of child marriage in conflict-affected areas of Ethiopia. (UNICEF) When girls are forced out of school, they become more vulnerable to early marriage, gender-based violence, and lifelong social and economic disadvantages. Education is one of the strongest protections against child marriage, and the loss of access to education places thousands of girls at serious risk. Psychological and Social Consequences The impact of conflict extends beyond the classroom. Many children in Amhara have experienced violence, displacement, fear, and trauma. UNICEF has reported that conflict-affected children frequently suffer psychological distress and require psychosocial support. Millions of children have missed years of learning opportunities, while many schools have been occupied, damaged, or destroyed during periods of conflict. (UNICEF) Without immediate intervention, an entire generation risks suffering long-term educational loss, reduced employment opportunities, increased poverty, and diminished prospects for future development.

የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጋል። (ሰኔ 13/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገ
+1
የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጋል። (ሰኔ 13/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሠረት በኦንላይን (Computer-based Testing (CBT) የሚፈተኑ ተፈታኞ በስድስት ዙር የሚፈተኑ ሲሆን ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ይፈተናሉ። ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የሚፈተኑ ይሆናል። ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተፈታኞች የተፈጥሮ ሳይንስ በሶስተኛ ዙር ላይ የሚፈተኑ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ በአራተኛ ዙር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚፈተኑ ይሆናል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! @ትምህርት መረጃ( academic info) Telegram: https://t.me/academic_info Facebook: https://www.facebook.com/share/1EqNsbE4CN/ email: accadamicinfo@gmail.com Instagram:https://www.instagram.com/academicinfor?igsh=ZW8xc2J0MXdxdDVj

በሚገኙበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት ወይም የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ያልተሰጣቸው የዩኒቨርሲቲ መምህራን ስም ዝርዝርን እንዲልኩ ትምህርት ሚኒስቴር ሁሉንም የመንግሥት ዩኒቨርሲዎች
በሚገኙበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት ወይም የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ያልተሰጣቸው የዩኒቨርሲቲ መምህራን ስም ዝርዝርን እንዲልኩ ትምህርት ሚኒስቴር ሁሉንም የመንግሥት ዩኒቨርሲዎች ጠይቋል። በቀን 04/10/2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ኮራ ጡሹ ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲዎች የተጻፈ ደብዳቤ፣ ከሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት ውስጥ የመምህራኑ ዝርዝር ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዲላክ አዟል። @academic info

የቴሌግራም አካውንታችሁን Log Out ከማድረጋችሁ በፊት ተጠንቀቁ! ብዙ ተጠቃሚዎች አካውንታቸውን Log Out አድርገው በድጋሚ ለመግባት ሲሞክሩ "Code አንልክም፤ በኢሜይል እንዲላክ Premium ግዙ" የሚል መልዕክት እየመጣባቸው ተቸግረዋል ችግሩ ምንድነው? ቴሌግራም የደህንነት መጠበቂያ ኢሜይል (Recovery Email) ያላስገቡ ተጠቃሚዎች አካውንታቸውን በሌላ ስልክ ወይም ከወጡ በኋላ ለመግባት ሲሞክሩ የኤስኤምኤስ (SMS) ኮድ ከመላክ ይልቅ በኢሜይል እንዲላክ ያስገድዳል ኢሜይል ከሌለህ ደግሞ በክፍያ (Premium) እንድትገባ ሊጠይቅህ ይችላል መፍትሄው፦ 1. አካውንታችሁ ሳይዘጋ፦ አሁኑኑ Settings=>Privacy and Security => Two-Step Verification ውስጥ በመግባት ትክክለኛ የኢሜይል አድራሻችሁን አስገቡ 2. አካውንቱ ለተዘጋበት ሰው፦ በሌላ ስልክ ወይም ኮምፒውተር ላይ አካውንቱ ክፍት ካልሆነ፣ የቴሌግራም Support መጠየቅ ወይም ጥቂት ቀናትን ጠብቆ በድጋሚ መሞከር ሊያስፈልግ ይችላል ማሳሰቢያ፦ አካውንታችሁ በሌላ ስልክ ላይ ክፍት ካልሆነ በስተቀር Log Out አታድርጉ! ድንገት ቴሌግራም ላይ "Log out" ብታደርጉ ያለምንም code እንደገና ለመግባት passkey feature ን ይጠቀሙ ! ይህን setting on ለማድረግ Telegram setting ላይ በመግባት -> privacy and security -> passkeys -> create passkeys የሚለውን በመጫን passkey ይፈጠሩ ! ይህ ለምን ይጠቅማል ? ድንገት ከ telegram log out ብትሉ በቀላሉ በ አሻራ / pattern/screen lock ወይ face በቀላሉ እንድንገባ ያደርጋል !

አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ - ለአዲስ ተሽከርካሪዎች ብቻ ከዛሬ ጀምሮ እየተሰጠ ነው 🔴 የነባር ተሽከርካሪዎች መውሰጃ ጊዜ አልታወቀም፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከዛሬ ጀምሮ አዲሱ የተሽከርካሪ
+1
አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ - ለአዲስ ተሽከርካሪዎች ብቻ ከዛሬ ጀምሮ እየተሰጠ ነው 🔴 የነባር ተሽከርካሪዎች መውሰጃ ጊዜ አልታወቀም፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከዛሬ ጀምሮ አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ መሰጠት ጀምሯል። የከተማዋ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ ዘገየ በላይነህ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ፥ ከሴኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አዲሱ ሰሌዳ ለከተማዋ ተሽከርካሪዎች መሰጠት ተጀምሯል። በዚህ መሰረትም ተመዝግበው ሲጠባበቁ የነበሩ አሽከርካሪዎች በተመዘገቡበት ቅርንጫፍ በኩል ስልክ ተደውሎ እንዲወስዱ ይደረጋል ብለዋል። አዲሱ ሰሌዳ የሚሰጠው ለአዳዲስ ተሽከርካሪዎች ብቻ መሆኑንም ነው ዋና ሥራ አስኪያጁ ያስገነዘቡት፡፡ ነባሩን የተሽከርካሪ ሰሌዳ የሚጠቀሙትን በተመለከተ ወደፊት በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በኩል ይፋ እንደሚደረግ አመልክተዋል፡፡ (የዋጋ ዝርዝሩ ተያይዟል)

#ተጨማሪ ከሰኔ 17-19/2018 ዓ.ም የሚሰጠውን የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና የምትወስዱ ተመዛኞች ማክሰኞ ሰኔ 16/2018 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው
#ተጨማሪ   ከሰኔ 17-19/2018 ዓ.ም የሚሰጠውን የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና የምትወስዱ ተመዛኞች ማክሰኞ ሰኔ 16/2018 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ መከታተል ይኖርባችኋል ተብሏል፡፡ የተመዛኞች ስም እና የተመደቡበትን የፈተና ማዕከል ዝርዝር በ https://t.me/M0H_EThiopia/2842 እና  https://t.me/M0H_EThiopia/2851 ላይ ማየት ይችላሉ፡፡ በፈተናው ወቅት የብሔራዊ መታወቂያ እንዲሁም ሲስተሙ የሚሰጠውን QR Code ያለው የፈተና መግቢያ (ስሊፕ) ፕሪንት አድርጋችሁ መያዝ ይኖርባችኋል፡፡   ምንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ (ስልክ፣ የእጅ ሰዓት፣ መነፅር (የተረጋገጠ የዕይታ ችግር ከሌለ በስተቀር)፣ ቦርሳ እና ሌሎች እቃዎች፣ ምንም አይነት ማጣቀሻዎች እና ባዶ ወረቀቶች እንዲሁም ምግብ ወይም መጠጥ (የተረጋገጠ የጤና ችግር ከሌለ በስተቀር) ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት አይፈቀድም፡፡ በፈተናው ወቅት ተመዛኞች በሁለቱም ክፍለ ጊዜ (ጠዋት እና ከሰዓት) የፈተና ክፍሉን ለቀው ከመውጣታቸው በፊት አቴንዳንስ ላይ መፈረም ይጠበቅባቸዋል። ተመዛኞች ስማቸው ከተጠቀሰበት የመፈተኛ ጣቢያ ውጪ በፍጹም ፈተናውን መውሰድ አይፈቀድም፡፡  

የ2018 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና መርሐግብር (Exit Exam Schedule) (Tentative) የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል።