ar
Feedback
ትምህርት መረጃ( academic info)

ትምህርት መረጃ( academic info)

الذهاب إلى القناة على Telegram

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ትምህርት መረጃ( academic info)

تُعد قناة ትምህርት መረጃ( academic info) (@academic_info) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 10 567 مشتركاً، محتلاً المرتبة 18 707 في فئة التعليم والمرتبة 3 152 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 10 567 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 10 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 386، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 4، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 43.10‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 12.70‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 554 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 342 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 5.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
@ትምህርት መረጃ( academic info) Telegram: https://t.me/academic_info Facebook: https://www.facebook.com/share/1EqNsbE4CN/ email: accadamicinfo@gmail.com Instagram:https://www.instagram.com/academicinfor?igsh=ZW8xc2J0MXdxdDVj

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 11 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.

10 567
المشتركون
+424 ساعات
+917 أيام
+38630 أيام
أرشيف المشاركات
አንድ የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ራስ-ገዝ ለመሆን በሁሉም ፕሮግራሞች ለሦስት ተከታታይ ዓመታት 80 በመቶ ተማሪዎቹን በመውጫ ፈተና ማሳለፉን እንደ አንድ አካዳሚክ መመዘኛ ነጥብ የሚይዝ መመሪያ ትምህርት ሚኒስቴር አውጥቷል።ማንኛውም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ለመሆን በመመዘኛ ነጥቦቹ 60 በመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅበታል የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ካሉባቸው የአደረጃጀት እና የአሰራር ውሱንነቶች ወጥተው፣ ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድሩ የሚያስችላቸውን “የመንግስት ዩኒቨርሲቲ የራስ-ገዝነት የሽግግር መምረጫ መመሪያ ቁጥር 1143/2018” አውጥቷል። ትምህርት ሚኒስቴር መመሪያውን ማውጣት ያስፈለገበትን ምክንያት ሲያስረዳ፤ እስካሁን በነበረው አሰራር ዩኒቨርሲቲዎች በቂ ተቋማዊ ነፃነት ባለመኖሩ ምክንያት የመማር ማስተማር፣ የምርምር እና የማህበረሰብ አገልግሎት ተልዕኮዎቻቸውን በአግባቡ ለመወጣት እንቅፋት ሆኖባቸው መቆየቱን ገልጿል። በመሆኑም ተቋማቱ ከመንግስት ጣልቃ ገብነት ነፃ ሆነው በሰው ኃይል፣ በሀብት አጠቃቀም እና በአካዳሚክ ጉዳዮች ላይ ራሳቸውን እንዲያስተዳድሩ ማስቻል አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ገልጿል። ይህ መመሪያ በራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ አዋጅ ቁጥር 1294/2015 አንቀጽ 5 እና 45 መሠረት የተዘጋጀ ነው። እንደ መመሪያው ገለጻ፣ አንድ የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር በአራት ዋና ዋና አምዶች ላይ ተመስርቶ ግምገማ ይደረግበታል። እነዚህም አስተዳደር (30%)፣ ፋይናንስ (20%)፣ የሰው ኃይል (15%) እና አካዳሚክ (35%) ጉዳዮች ናቸው። የሽግግር ሂደቱም በተጨባጭ መረጃ፣ በላቀ ብቃት፣ በውጤታማነት፣ በአካታችነት፣ በግልጽነት እና በተጠያቂነት መርሆዎች ላይ ተመስርቶ የሚከናወን ይሆናል። ዩኒቨርሲቲዎች ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ለመሸጋገር በዝግጅት ምዕራፍ ወቅት ቢያንስ 60 በመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል። በመመሪያው ላይ በዝርዝር የተቀመጡ እና ተቋማቱ ሊያሟሏቸው የሚገቡ መመዘኛዎች መስፈርቶች መካከል:- • ተቋማቱ ቢያንስ 15 በመቶ የሚሆኑ የመማሪያ ክፍሎቻቸውን ወደ “ስማርት ክላስሩም” የቀየሩ • 80 በመቶ እና ከዚያ በላይ የሚሆኑ ተማሪዎቻቸው ብሄራዊ የመውጫ ፈተናን ያለፉ •ቢያንስ 5 በመቶ የሚሆኑ የትምህርት ፕሮግራሞቻቸው ዓለም አቀፍ እውቅና (Accreditation) ማግኘታቸው እና የዲጂታል ቤተ-መጽሐፍት አገልግሎታቸው ከ70 በመቶ በላይ መድረስ አለበት • አንድ ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር ላለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት የሂሳብ ምርመራ (Audit) ያስደረገና የኦዲት ግኝቱም “ንጹህ” (Unqualified) ወይም አስተያየት ያልተሰጠበት መሆን ይኖርበታል። • ተቋሙ ካለው አጠቃላይ በጀት ውስጥ ቢያንስ 15 በመቶውን ከውስጥ ገቢና ከውጭ የገቢ ምንጮች መሸፈን ይጠበቅበታል። • ለገቢ ምንጭነትም ቢያንስ አምስት እና ከዚያ በላይ የገቢ ማመንጫ ዘርፎችን ወደ ስራ ማስገባት እንደ ግዴታ ተቀምጧል። • የዩኒቨርሲቲው መምህራን የትምህርት ደረጃ ስብጥር 0፡ 60፡ 40 (የመጀመሪያ ዲግሪ 0%፣ ሁለተኛ ዲግሪ 60% እና ሦስተኛ ዲግሪ 40%) መድረስ እንዳለበት ተደንግጓል። • በተጨማሪም የአካዳሚክ ማዕረግ ስብጥሩ ሌክቸረር 46%፣ ረዳት ፕሮፌሰር 31%፣ ተባባሪ ፕሮፌሰር 20% እና ፕሮፌሰር እና ከዚያ በላይ 3% መሆኑ መረጋገጥ ይኖርበታል። • ተቋማቱ በምርምር ዘርፍ ያላቸውን ጥንካሬ ለማሳየትም ቢያንስ አምስት እና ከዚያ በላይ የሆኑ የአእምሯዊ ንብረት መብት (IP) ባለቤት መሆን እንዳለባቸው በመመሪያው ተመላክቷል። • ተቋማዊ አገልግሎትንና የተገልጋይ እርካታን በተመለከተም፣ ዩኒቨርሲቲዎች በመምህራን፣ በሠራተኞችና በተማሪዎች ዘንድ ቢያንስ 75 በመቶ የእርካታ ደረጃ ማረጋገጥ ይጠበቅባቸዋል። • ከአካባቢው ማህበረሰብና ከኢንዱስትሪ ተዋንያን ጋር ባላቸው ግንኙነት ደግሞ የ70 በመቶ የእርካታ ደረጃን በጥናት ማሳየት ይኖርባቸዋል። • በቴክኒክ ረገድም ካሏቸው ቤተ-ሙከራዎች (Laboratories) ውስጥ 10 በመቶ የሚሆኑት፣ ከወርክሾፖቻቸው ደግሞ 5 በመቶው በዓለም አቀፍ ስታንዳርድ የተደራጁ መሆናቸው በሽግግር ግምገማው ወቅት ትልቅ ዋጋ ይሰጠዋል። የሽግግር ሂደቱ በሁለት ደረጃዎች የሚከናወን ሲሆን፣ መጀመሪያ ዩኒቨርሲቲው በራሱ ኮሚቴ አማካኝነት የውስጥ ግለ-ግምገማ (Self-assessment) ያካሂዳል ይህ ግምገማ በዩኒቨርሲቲው ስራ አመራር ቦርድ ጸድቆ ለትምህርት ሚኒስቴር ይቀርባል። ሚኒስቴሩ የቀረበለትን ሪፖርት መነሻ በማድረግ በገለልተኛ ባለሙያዎች የታገዘ የመስክ ምልከታና ማረጋገጫ ከሰጠ በኋላ፣ መስፈርቱን አሟልተው ለተገኙ ተቋማት ወደ ራስ-ገዝነት እንዲሸጋገሩ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት የውሳኔ ሃሳብ ያቀርባል። ወደ ራስ-ገዝነት የተሸጋገረ ዩኒቨርሲቲ የሽግግር ጊዜው ለሁለት ተከታታይ ዓመታት የሚቆይ ሲሆን፣ በዚህ ጊዜ ውስጥ ተቋማዊና አካዳሚክ ነፃነቱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል አቅም ይገነባል። ይሁን እንጂ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ መግባት ካልቻለ፣ ሚኒስቴሩ ተጨማሪ ጊዜ ሊሰጠው ወይም ከቦርዱ ጋር በመመካከር ሌሎች ውሳኔዎችን ሊያስተላልፍ እንደሚችል መመሪያው ደንግጓል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ መመሪያ በፍትህ ሚኒስቴር ተመዝግቦ የጸደቀ መሆኑን ከትምህርት ሚኒስቴር አረጋግጧል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ @tikvahethiopia

የእራስን እድል በራስ የመወሰን መብት..‼ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ዛሬ ይፋ ያደረጓቸው 8 ዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎችን:- በዚህ መሠረት 1.የሀገር ግንባታ 2.የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ የፖለቲካ ውክልና የምርጫ ሥርአት ጉዳዮች 3.የፌድራል ከተሞች አዲስአበባ እና ድሬዳዋ ጉዳይ 4.የሃይማኖት ጉዳዮች 5.የተቋማት ግንባታ የህግ የበላይነትና የሰብአዊ መብቶች 6.ማህበራዊና ኢኮኖሚ እንዲሁም የአርሶአደር እና አርብቶ አደር ጉዳዮች 7.ሙስና እና መልካም አስተዳደር 8.ሰላም ግንባታ 📌በኮሚሽኑ የተለዩት 8 አጀንዳዎች እያንዳንዳቸው በስራቸው ዝርዝር ንዑስ ጉዳዮችን አካተዋል ብለዋል። ለምሳሌ በ1ኛው አጀንደ ስር አጀንዳ ቁጥር 1 1. የሀገር ግንባታ    1.1. የማንነት እና የሀገር ባለቤትነት ጉዳዮች    እዛው ስር 2. ታሪክ እና ማንነት 2. የጋራ ሀገራዊ ማንነት እና እሴቶች... እሴቶችን የሚመለከቱ ጉዳዮች    እዚያው ስር 4. ሀገር ግንባታ እና ብዙሀንነት አስተዳደር ጉዳዮች 3. የቋንቋ ጉዳዮች    1.6. የባህል ታሪክ እና... ታሪክ እና ቅርስ ጥበቃ ጉዳዮች እንዲሁም ሌሎችም በርካታ ጉዳዮች አጀንዳ ቁጥር 2 2. የመንግስት አደረጃጀት እና ቅርፅ እንዲሁም የፖለቲካ ስርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ስርዓት    2.1. የመንግስት አደረጃጀት እና ቅርፅ    2.1.1. የመንግስት አደረጃጀት አስተዳደር ስርዓት አይነት    2.1.2. እራስን እድል በራስ የመወሰን መብት፤ በቅንፍ ውስጥ ሰላሳ ዘጠኝ እዝባር አንድ (39/1)    2.1.3. የብሄር ብሄረሰቦች ትርጓሜ፤ አንቀፅ ሰላሳ ዘጠኝ እዝባር አምስት (39/5) — ህገ-መንግስቱን... ህገ-መንግስቱን ማለቴ ነው    2.1.4. የፌደራል መንግስት እና የክልል መንግስታት መሪዎች የስልጣን ዘመን    2.1.5. የፌደራል እና የክልል መንግስታት ግንኙነት    እዚያው ስር፡ የስልጣን ክፍፍል የፌደራል እና የክልል መንግስት    እዚያው ስር አሁንም፡ የፊስካል ፌደራሊዝም እና የሀብት ክፍፍል    2.1.6. የክልል አስተዳደር እና ወሰኖች    እዚያው ስር፡ የአዳዲስ ክልሎች አመሰራረት    እዚያው ስር፡ የክልል አስተዳደራዊ ወሰኖች    2.1.7. የህግ አውጪው አካል ወይም ፓርላማ መዋቅር እና miና    2.1.8. ህገ-መንግስትን የመተርጎም ስልጣን    2.1.9. የህገ-መንግስት ማሻሻያ ስርዓት፤ አንቀፅ አንድ መቶ አራት (104) እና አንድ መቶ አምስት (105)    2.2. የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ስርዓት ጉዳዮች    ከስሩ 2.2.1. የሀገሪቱ የምርጫ ስርዓት    2.2.2. የመድብለ ፓርቲ ስርዓት    2.2.3. የፖለቲካ ፓርቲ አደረጃጀት    2.2.4. የመንግስት እና የገዢ ፓርቲ ሚና መለያየት    2.2.5. የምርጫ ክልሎች አወቃቀር    2.2.6. የፖለቲካ ፓርቲዎች የመንግስት ሀብት አጠቃቀም አጀንዳ ቁጥር 3 3. የፌደራል ከተሞች (አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ)    3.1. የአዲስ አበባ ጉዳይ    3.1.1. የአዲስ አበባ ህጋዊ አቋም    እዚያው ስር፡ አዲስ አበባ ከኦሮሚያ ክልል ጋር ያለው ግንኙነት    ከዚያው ስር፡ የአዲስ አበባ ከተማ የበጀት ድርሻ ጉዳይ    3.1.2. የፌደራል ዋና ከተማ ጉዳይ    3.1.3. የአዲስ አበባ ፖሊስ እና ፍርድ ቤት ጉዳይ    3.1.4. የአዲስ አበባ ወሰን እና የቦታዎች ስያሜዎች    3.1.5. የአዲስ አበባ ከተማ የስራ ቋንቋ    3.1.6. የአዲስ አበባ ከተማ ታሪካዊ ቅርሶች አካታችነት ጉዳይ    ...3.2. የድሬዳዋ ጉዳይ ....... አጀንዳዎቹ  ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በአገር አቀፍ ደረጃ በአዲስ አበባ በሚካሄደው ጉባዔ ላይ የሚመከርባቸው ናቸው፡፡

ውጤትዎን ይመልከቱ! ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት መታየት ጀምሯል። ውጤትዎን ለማየት 👇 https://result.
ውጤትዎን ይመልከቱ! ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት መታየት ጀምሯል። ውጤትዎን ለማየት 👇 https://result.ethernet.edu.et ሊንኩን ከተጫኑ በኋላ 'Exit Examination' ላይ 'View Results' የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ።

🔥 በ7ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ አሸናፊዎች መልካም የስራ ዘመን ተመኘን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ውጤት ይፋ አድርጓል። በተገለጹት ውጤቶች መሰረት ብልጽግና ፓርቲ በአብዛኞቹ ክልሎች የፓርላማ መቀመጫዎችን በመቆጣጠር ዋና አሸናፊ ሆኖ ተገኝቷል። አጠቃላይ የፓርላማ ምርጫ ውጤቶች 1. አዲስ አበባ ከተማ (23 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 20 መቀመጫዎች - ኢዜማ – 2 መቀመጫዎች - የግል ዕጩ – 1 መቀመጫ 2. አፋር ክልል (8 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 7 መቀመጫዎች - የአፋር ህዝብ ፓርቲ – 1 መቀመጫ 3. አማራ ክልል (130 መቀመጫዎች ላይ ምርጫ የተካሄደ) - ብልጽግና ፓርቲ – 117 መቀመጫዎች - አብን – 6 መቀመጫዎች - አዲህን – 3 መቀመጫዎች - አርጎባ አንድነት ጀበርቲ ፓርቲ – 1 መቀመጫ - ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት – 1 መቀመጫ - ኢዜማ – 1 መቀመጫ - ነጻነትና እኩልነት – 1 መቀመጫ 4. ቤኒሻንጉል ጉሙዝ (9 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 8 መቀመጫዎች - ጉሙዝ ብሔራዊ ንቅናቄ – 1 መቀመጫ 5. ድሬዳዋ (2 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 2 መቀመጫዎች 6. ጋምቤላ ክልል (3 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 3 መቀመጫዎች 7. ኦሮሚያ ክልል (173 መቀመጫዎች ላይ ውጤት ይፋ የሆነ) - ብልጽግና ፓርቲ – 167 መቀመጫዎች - የግል ዕጩዎች – 5 መቀመጫዎች - አዲስ ትውልድ ፓርቲ – 1 መቀመጫ 8. ሐረሪ ክልል (2 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 2 መቀመጫዎች 9. ሲዳማ ክልል (16 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 13 መቀመጫዎች - መድረክ – 3 መቀመጫዎች 10. ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ (20 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 17 መቀመጫዎች - ኢዜማ – 1 መቀመጫ - ነጻነትና እኩልነት – 1 መቀመጫ - ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት – 1 መቀመጫ 11. ደቡብ ኢትዮጵያ (45 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 35 መቀመጫዎች - ኢዜማ – 7 መቀመጫዎች - የጌድዮ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ – 1 መቀመጫ - የወላይታ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ – 1 መቀመጫ - የግል ዕጩ – 1 መቀመጫ 12. ማዕከላዊ ኢትዮጵያ (33 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 28 መቀመጫዎች - ኢዜማ – 2 መቀመጫዎች - የግል ዕጩ – 1 መቀመጫ - ትብብር ለኢትዮጵያ – 1 መቀመጫ - ነጻነትና እኩልነት – 1 መቀመጫ 13. ሶማሌ ክልል (22 መቀመጫዎች) - ብልጽግና ፓርቲ – 19 መቀመጫዎች - የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር – 1 መቀመጫ - ሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ – 1 መቀመጫ - ህብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት ፓርቲ – 1 መቀመጫ ማስታወሻ በትግራይ ክልል በ38 የፓርላማ መቀመጫዎች ምርጫ አለመካሄዱ ይታወቃል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ውጤት - ብልጽግና ፓርቲ – 144 መቀመጫዎች - ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት – 12 መቀመጫዎች - ኢዜማ – 10 መቀመጫዎች - ነጻነትና እኩልነት – 3 መቀመጫዎች - የወሎ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት – 1 መቀመጫ በአጠቃላይ የ7ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ውጤት ብልጽግና ፓርቲ በአብዛኞቹ ክልሎች ከፍተኛ ድል ማስመዝገቡን ያሳያል። በተለይም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ከ20 የፓርላማ መቀመጫዎች 17ቱን በማሸነፍ የበላይነቱን አረጋግጧል። መልካም የስራ ዘመን!

Humanitarian Consequences The crisis is not only an educational emergency but also a humanitarian emergency. Conflict has displaced hundreds of thousands of people in Amhara and severely disrupted access to basic services. Humanitarian agencies have repeatedly warned that insecurity continues to hinder relief efforts and threatens the well-being of millions of civilians. (GOV.UK) Appeal to the International Community The international community must not overlook the plight of children in the Amhara Region. Immediate action is needed to: Support the safe reopening of schools. Rehabilitate and reconstruct damaged educational facilities. Provide emergency learning opportunities for displaced children. Protect children from child labor and exploitation. Prevent child marriage and support vulnerable girls. Expand psychosocial and mental health services for conflict-affected children. Increase humanitarian assistance for families affected by conflict and displacement. Promote peaceful solutions that allow children to return safely to school. Conclusion The children of Amhara are paying the highest price for a conflict they did not create. Millions have lost access to education, many are entering child labor, and others face the threat of early marriage. Every day that schools remain closed is another day stolen from their future. The world must act urgently to ensure that these children are protected, educated, and given the opportunity to rebuild their lives in peace. (Africa Press English) "Every child has the right to learn, to be safe, and to dream of a better future. The children of Amhara deserve nothing less."

Below is a formal English briefing that you can share with international organizations, donors, human rights groups, media outlets, and the global community. The Education Crisis Facing Children in Ethiopia's Amhara Region A Call for International Attention and Action The ongoing conflict in Ethiopia's Amhara Region has created one of the most severe child protection and education crises in the country. Millions of children have been forced out of school due to insecurity, displacement, destruction of educational infrastructure, and the prolonged disruption of public services. As a result, many children are now exposed to child labor, early marriage, poverty, exploitation, and long-term social and psychological harm. Massive School Closures and Educational Disruption According to reports from UNICEF, the United Nations Office for the Coordination of Humanitarian Affairs (UNOCHA), and other humanitarian organizations, the education sector in Amhara has been devastated by conflict. More than 4.1 million children in the Amhara Region have been pushed out of school, while thousands of schools have been closed, damaged, destroyed, or rendered non-functional due to insecurity. (Xinhua News) Recent humanitarian reports indicate that approximately 4.4 million children in Amhara are currently out of school. More than 5,000 schools have been damaged, and thousands remain closed because of ongoing violence and instability. (GOV.UK) The United Nations Children's Fund (UNICEF) has also reported that conflict and displacement have contributed to a nationwide education emergency, with Amhara among the regions most severely affected. More than 10,000 schools across Ethiopia have been damaged by conflict and climate shocks, while over 9 million children are out of school nationwide. (China.org.cn) Rising Child Labor As families struggle to survive amid economic hardship and displacement, many children who should be attending school are instead working to support their households. In both rural and urban areas, children are increasingly engaged in daily labor activities, including agricultural work, street vending, transportation services, domestic labor, and other informal employment. When schools remain closed for extended periods, children lose not only educational opportunities but also protection from exploitation. The longer they remain outside the education system, the greater the risk that they will never return to school. Increased Risk of Child Marriage Girls are among the most vulnerable victims of the crisis. Humanitarian organizations have warned that conflict, poverty, displacement, and school closures significantly increase the likelihood of child marriage. UNICEF has documented that emergencies such as conflict and drought often lead families to resort to child marriage as a coping mechanism for economic survival. Reports indicate rising risks of child marriage in conflict-affected areas of Ethiopia. (UNICEF) When girls are forced out of school, they become more vulnerable to early marriage, gender-based violence, and lifelong social and economic disadvantages. Education is one of the strongest protections against child marriage, and the loss of access to education places thousands of girls at serious risk. Psychological and Social Consequences The impact of conflict extends beyond the classroom. Many children in Amhara have experienced violence, displacement, fear, and trauma. UNICEF has reported that conflict-affected children frequently suffer psychological distress and require psychosocial support. Millions of children have missed years of learning opportunities, while many schools have been occupied, damaged, or destroyed during periods of conflict. (UNICEF) Without immediate intervention, an entire generation risks suffering long-term educational loss, reduced employment opportunities, increased poverty, and diminished prospects for future development.

የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጋል። (ሰኔ 13/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገ
+1
የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጋል። (ሰኔ 13/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሠረት በኦንላይን (Computer-based Testing (CBT) የሚፈተኑ ተፈታኞ በስድስት ዙር የሚፈተኑ ሲሆን ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ይፈተናሉ። ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የሚፈተኑ ይሆናል። ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተፈታኞች የተፈጥሮ ሳይንስ በሶስተኛ ዙር ላይ የሚፈተኑ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ በአራተኛ ዙር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚፈተኑ ይሆናል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! @ትምህርት መረጃ( academic info) Telegram: https://t.me/academic_info Facebook: https://www.facebook.com/share/1EqNsbE4CN/ email: accadamicinfo@gmail.com Instagram:https://www.instagram.com/academicinfor?igsh=ZW8xc2J0MXdxdDVj

በሚገኙበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት ወይም የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ያልተሰጣቸው የዩኒቨርሲቲ መምህራን ስም ዝርዝርን እንዲልኩ ትምህርት ሚኒስቴር ሁሉንም የመንግሥት ዩኒቨርሲዎች
በሚገኙበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት ወይም የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ያልተሰጣቸው የዩኒቨርሲቲ መምህራን ስም ዝርዝርን እንዲልኩ ትምህርት ሚኒስቴር ሁሉንም የመንግሥት ዩኒቨርሲዎች ጠይቋል። በቀን 04/10/2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ኮራ ጡሹ ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲዎች የተጻፈ ደብዳቤ፣ ከሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት ውስጥ የመምህራኑ ዝርዝር ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዲላክ አዟል። @academic info

የቴሌግራም አካውንታችሁን Log Out ከማድረጋችሁ በፊት ተጠንቀቁ! ብዙ ተጠቃሚዎች አካውንታቸውን Log Out አድርገው በድጋሚ ለመግባት ሲሞክሩ "Code አንልክም፤ በኢሜይል እንዲላክ Premium ግዙ" የሚል መልዕክት እየመጣባቸው ተቸግረዋል ችግሩ ምንድነው? ቴሌግራም የደህንነት መጠበቂያ ኢሜይል (Recovery Email) ያላስገቡ ተጠቃሚዎች አካውንታቸውን በሌላ ስልክ ወይም ከወጡ በኋላ ለመግባት ሲሞክሩ የኤስኤምኤስ (SMS) ኮድ ከመላክ ይልቅ በኢሜይል እንዲላክ ያስገድዳል ኢሜይል ከሌለህ ደግሞ በክፍያ (Premium) እንድትገባ ሊጠይቅህ ይችላል መፍትሄው፦ 1. አካውንታችሁ ሳይዘጋ፦ አሁኑኑ Settings=>Privacy and Security => Two-Step Verification ውስጥ በመግባት ትክክለኛ የኢሜይል አድራሻችሁን አስገቡ 2. አካውንቱ ለተዘጋበት ሰው፦ በሌላ ስልክ ወይም ኮምፒውተር ላይ አካውንቱ ክፍት ካልሆነ፣ የቴሌግራም Support መጠየቅ ወይም ጥቂት ቀናትን ጠብቆ በድጋሚ መሞከር ሊያስፈልግ ይችላል ማሳሰቢያ፦ አካውንታችሁ በሌላ ስልክ ላይ ክፍት ካልሆነ በስተቀር Log Out አታድርጉ! ድንገት ቴሌግራም ላይ "Log out" ብታደርጉ ያለምንም code እንደገና ለመግባት passkey feature ን ይጠቀሙ ! ይህን setting on ለማድረግ Telegram setting ላይ በመግባት -> privacy and security -> passkeys -> create passkeys የሚለውን በመጫን passkey ይፈጠሩ ! ይህ ለምን ይጠቅማል ? ድንገት ከ telegram log out ብትሉ በቀላሉ በ አሻራ / pattern/screen lock ወይ face በቀላሉ እንድንገባ ያደርጋል !

አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ - ለአዲስ ተሽከርካሪዎች ብቻ ከዛሬ ጀምሮ እየተሰጠ ነው 🔴 የነባር ተሽከርካሪዎች መውሰጃ ጊዜ አልታወቀም፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከዛሬ ጀምሮ አዲሱ የተሽከርካሪ
+1
አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ - ለአዲስ ተሽከርካሪዎች ብቻ ከዛሬ ጀምሮ እየተሰጠ ነው 🔴 የነባር ተሽከርካሪዎች መውሰጃ ጊዜ አልታወቀም፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከዛሬ ጀምሮ አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ መሰጠት ጀምሯል። የከተማዋ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ ዘገየ በላይነህ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ፥ ከሴኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አዲሱ ሰሌዳ ለከተማዋ ተሽከርካሪዎች መሰጠት ተጀምሯል። በዚህ መሰረትም ተመዝግበው ሲጠባበቁ የነበሩ አሽከርካሪዎች በተመዘገቡበት ቅርንጫፍ በኩል ስልክ ተደውሎ እንዲወስዱ ይደረጋል ብለዋል። አዲሱ ሰሌዳ የሚሰጠው ለአዳዲስ ተሽከርካሪዎች ብቻ መሆኑንም ነው ዋና ሥራ አስኪያጁ ያስገነዘቡት፡፡ ነባሩን የተሽከርካሪ ሰሌዳ የሚጠቀሙትን በተመለከተ ወደፊት በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በኩል ይፋ እንደሚደረግ አመልክተዋል፡፡ (የዋጋ ዝርዝሩ ተያይዟል)

#ተጨማሪ ከሰኔ 17-19/2018 ዓ.ም የሚሰጠውን የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና የምትወስዱ ተመዛኞች ማክሰኞ ሰኔ 16/2018 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው
#ተጨማሪ   ከሰኔ 17-19/2018 ዓ.ም የሚሰጠውን የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና የምትወስዱ ተመዛኞች ማክሰኞ ሰኔ 16/2018 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ መከታተል ይኖርባችኋል ተብሏል፡፡ የተመዛኞች ስም እና የተመደቡበትን የፈተና ማዕከል ዝርዝር በ https://t.me/M0H_EThiopia/2842 እና  https://t.me/M0H_EThiopia/2851 ላይ ማየት ይችላሉ፡፡ በፈተናው ወቅት የብሔራዊ መታወቂያ እንዲሁም ሲስተሙ የሚሰጠውን QR Code ያለው የፈተና መግቢያ (ስሊፕ) ፕሪንት አድርጋችሁ መያዝ ይኖርባችኋል፡፡   ምንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ (ስልክ፣ የእጅ ሰዓት፣ መነፅር (የተረጋገጠ የዕይታ ችግር ከሌለ በስተቀር)፣ ቦርሳ እና ሌሎች እቃዎች፣ ምንም አይነት ማጣቀሻዎች እና ባዶ ወረቀቶች እንዲሁም ምግብ ወይም መጠጥ (የተረጋገጠ የጤና ችግር ከሌለ በስተቀር) ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት አይፈቀድም፡፡ በፈተናው ወቅት ተመዛኞች በሁለቱም ክፍለ ጊዜ (ጠዋት እና ከሰዓት) የፈተና ክፍሉን ለቀው ከመውጣታቸው በፊት አቴንዳንስ ላይ መፈረም ይጠበቅባቸዋል። ተመዛኞች ስማቸው ከተጠቀሰበት የመፈተኛ ጣቢያ ውጪ በፍጹም ፈተናውን መውሰድ አይፈቀድም፡፡  

የ2018 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና መርሐግብር (Exit Exam Schedule) (Tentative) የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል። 

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፥ ከ560 ሺህ በላይ ተፈታኞች ከሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ/ም እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ለመውሰድ መመዝገባቸውን አሳውቋል። ከተመዘገቡት ውስጥ አብዛኛዎቹ ተማሪዎች ፈተናውን በበይነ-መረብ እንደሚወስዱ የመሰረተ ልማት ውስንነት ባሉባቸው አካባቢዎች ፈተናው በወረቀት እንደሚሰጥ ተገልጿል። ✅ የተፈጥሮ ሳይንስ ፦ 306,964 ተማሪዎች፤ ✅ የማህበራዊ ሳይንስ ፦ 257,255 ተማሪዎች ለፈተናው 667 ማዕከላት እንደተዘጋጁ ተገልጿል።

photo content

#Update ሀገር አቀፍ ፈተናዎች በሚሰጥባቸው የጊዜ መርሐግብር ላይ ማሻሻያ መደረጉን ሰምተናል። በዚህም፥ ➫ የሪሚዲያል ፈተና ከግንቦት 27/2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም ➫ የቅድመ-
#Update ሀገር አቀፍ ፈተናዎች በሚሰጥባቸው የጊዜ መርሐግብር ላይ ማሻሻያ መደረጉን ሰምተናል። በዚህም፥ ➫ የሪሚዲያል ፈተና ከግንቦት 27/2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም ➫ የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም ➫ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም የሚሰጡ መሆኑ ተገልጿል። ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ የመርሐግብር ለውጡን ከዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ አመራሮች ለማረጋገጥ ችሏል። የመርሐግብር ለውጥ መደረጉን የተወሰኑ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በማኅበራዊ ትስስር ገፆቻቸው እያጋሩ ይገኛሉ።

🔔 አስቸኳይ! የፊታችን ሰኞ መሠጠት የሚጀምረውን የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና ለመውሰድ የተመዘገባቹ በአስቸኳይ የማረጋገጥ ሥራ እንድታደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል። የማረጋገጥ ሥራው (Self V
+1
🔔 አስቸኳይ! የፊታችን ሰኞ መሠጠት የሚጀምረውን የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና ለመውሰድ የተመዘገባቹ በአስቸኳይ የማረጋገጥ ሥራ እንድታደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል። የማረጋገጥ ሥራው (Self Verification) ከ2-3 ደቂቃዎች ብቻ የሚወስድና የተፈታኞችን የትምህርት ሰነዶች ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል። ተከታዩን ሊንክ (https://verify.ethernet.edu.et/) ከተጫኑ በኋላ Remedial Examination የሚለውን ይጫኑ፣ Start Verification የሚለውን በመጫንና የሚያስፈልገውን በመሙላት ያረጋግጡ። የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና ከግንቦት 17-20/2018 ዓ.ም እእንደሚሰጥ ይታወቃል።

አጭበርባሪ ነው ብር እንዳትከፍሉ
አጭበርባሪ ነው ብር እንዳትከፍሉ

#ማስታወሻ የቅድመ-ምረቃ ትምህርት የመውጫ ፈተና #በድጋሚ በግል ተፈታኞች ምዝገባ ዛሬ ግንቦት 12/2018 ዓ.ም ይጠናቀቃል፡፡ የመመዝገቢያ ሊንኩን https://exam.ethernet.edu.et በመጠቀምና የተዘረዘሩ መስፈርቶችን በማሟላት ምዝገባዎን በቀሩት ሰዓታት ያድርጉ። ለመመዝገብ የአገልግሎት ክፍያ 750 ብር በቴሌብር በኩል መክፈል ይጠበቅባችኋል፡፡ የ2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ከሰኔ 02-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወቃል፡፡

ይፋ የተደሩጉት የፔንታጎን ሰነዶች ምን ይዘዋል ? የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በመንግሥት እጅ የሚገኙና ከምድር ውጭ ያሉ ህይወት ያላቸው ፍጥረታትን እንዲሁም ያልታወቁ በራሪ አካላትን (UFO) ጋር የተያያዙ ሚስጥራዊ ፋይሎች ለሕዝብ ይፋ እንዲሆኑ ትዕዛዝ በሰጡት መሰረት ትላንት ይፋ ተደርጓል። መረጃው በሀገሪቱ የመከላከያ ሚኒስቴር በኩል በ war.gov/ufo በሚል አድራሻ ነው ይፋ የተደረገው። በዚህ ድረ-ገጽ በምስጢር ተይዘው የነበሩ የUFO (ወይም UAP) መረጃዎች ተካተውበታል። ለመጀመሪያ ጊዜ ለሕዝብ ይፋ የሆኑ ቪዲዮዎች ፣ ፎቶግራፎች እና በአሜሪካ መንግስት የተሰበሰቡ ሰነዶች ይገኙበታል። ሰነዶቹ ምን ይዘዋል ? - እ.ኤ.አ በ1965 በተካሄደው 'ጄምኒ 7' (Gemini 7) የህዋ ተልዕኮ ላይ ጠፈርተኛው ፍራንክ ቦማን ከቁጥጥር ማዕከሉ ጋር ያደረገው የድምጽ ንግግር በሰነዱ ተካቷል። በዚህ ንግግር ላይ "በትሪሊየኖች የሚቆጠሩ ጥቃቅን ቅንጣቶች" በመንኮራኩሩ ግራ በኩል መመልከቱን ገልጾ ነበር። - የአሜሪካ የጦር አውሮፕላኖች በመካከለኛው ምስራቅ (በተለይም በኢራቅ እና ሶሪያ) ላይ ሲበሩ የቀረጿቸው የቪዲዮ ምስሎች ይፋ ሆነዋል። በቪዲዮዎቹ ላይ ክብ ቅርጽ ያላቸው እና በከፍተኛ ፍጥነት የሚምዘገዘጉ አካላት ታይተዋል። - የአፖሎ 11 ጠፈርተኛ በዝ አልድሪን በ1969 በሰጠው ቃል በጨረቃ ጉዞ ወቅት ለማስረዳት የሚከብዱ ነገሮችን ተመልክቷል። " አንዳች የብርሃን ምንጭ ተመልክቻለሁ። ምናልባት ጨረራ ሊሆን ይችላል ብለን ወስደነዋል " ብሏል። - በ1969 ጨረቃ ላይ የተራመደው እና የአፖሎ 12 አባል የነበረው ጠፈርተኛ አለን ቢን " የብርሃን ቅንጣቶች እና ጨረሮች " መመልከቱን ተናግሯል። እነዚህ የብርሃን ፍንጥቅጣቂዎች "ከጨረቃ ያመለጡ" እንደሚመስሉ ገልጾ "ሕዋ ላይ ሲንሳፈፉ" ነበርም ብሏል። - በ1972 በአፖሎ 17 ተልዕኮ ውስጥ የነበሩ ሁለት ጠፈርተኞች መንኮራኮር ውስጥ ሳሉ የብርሃን ነጸብራቅ ማየታቸውን ገልጸዋል። - በ1957 ኤፍቢአይ ቃለ መጠይቅ ያደረገለት ግለሰብ ትልቅ፣ ክብ ተንቀሳቃሽ አካል ከምድር ሲነሳ መመልከቱን ገልጿል። - በ2023 በተደረገ ቃለ መጠይቅ ከደማቅ ብርሃን የሚወጣ ብረታማ ቁስ ሲንሳፈፍ ማየቱን አንድ አሜሪካዊ ገልጿል። - በ2022 የተቀረጸ ተንቀሳቃሽ ምሥል በትክክል የት እንደሆነ ባልታወቀ የመካከለኛው ምሥራቅ አካባቢ ክብ ቅርጽ ያለው ቁስ ከግራ ወደ ቀኝ ሲንቀሳቀስ ያሳያል። " ምናልባት ሚሳዔል ሊሆን ይችላል " የሚል መግለጫ ከተንቀሳቃሽ ምሥሉ ጋር ተያይዞ ቀርቧል። - ከኢራቅ፣ ከሶሪያ እና ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የተገኙ ተንቀሳቃሽ ምሥሎች "ምንነታቸው ያልተለየ እንግዳ ክስተቶች" በሚል ተቀምጠዋል። #BBC #UFO #Pentagon ግንቦት 1 ቀን 2018 ዓ/ም

8 ትሪሊዮን ብር አጠቃላይ እዳ‼️ የኢትዮጵያ አጠቃላይ ዕዳ 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለጸ ‼️ ​የኢትዮጵያ አጠቃላይ የውጭ እና የሀገር ውስጥ ዕዳ 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ለፓርላማ አስታወቁ። ሚኒስትሩ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፣ መንግስት ከአሜሪካ ጋር በየዓመቱ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚያገኝበትን አዲስ የድጋፍ ስምምነት ተፈራርሟል። ​ከአጠቃላይ ዕዳው ውስጥ 33.5 ቢሊዮን ዶላሩ የውጭ ዕዳ ሲሆን፣ ቀሪው 18.3 ቢሊዮን ዶላር ደግሞ የሀገር ውስጥ ዕዳ መሆኑ ተጠቁሟል። 22.1 ቢሊዮን ዶላሩ የፌደራል መንግስት፣ 11.5 ቢሊዮን ዶላሩ ደግሞ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ዕዳ ነው። 17.5 ቢሊዮን ዶላሩ የፌደራል መንግስት ሲሆን፣ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ድርሻ 0.8 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነው። ​የልማት ድርጅቶች ዕዳ ዝቅ ሊል የቻለው በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው መሠረት ከንግድ ባንክ ተበድረውት የነበረው ዕዳ ወደ ገንዘብ ሚኒስቴር በመዞሩ እንደሆነ ተብራርቷል። ሚኒስትሩ ዕዳው "በጣም ጤናማ" በሚባል ደረጃ ላይ እንደሚገኝና የውጭ ዕዳ የመክፈል አቅምም እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል። ​በበጀት ዓመቱ ለዕዳ ክፍያ ከተመደበው 463.4 ቢሊዮን ብር ውስጥ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 226.5 ቢሊዮን ብር ተከፍሏል። በሌላ በኩል፣ ከውጭ ሀብት አሰባሰብ ረገድ በዘጠኝ ወራት 3.1 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 2 ቢሊዮን ዶላር (የዕቅዱን 65.1%) ማሳካት ተችሏል። ከዚህ ውስጥ 914.2 ሚሊዮን ዶላሩ ከዓለም ባንክ የተገኘ ነው። ​አሜሪካ በየዓመቱ የምታደርገውን የ1 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ በተመለከተ፣ ስምምነቱ በቅርቡ በካቢኔ እንደሚጸድቅና ይህም ቀደም ሲል ተቋርጦ በነበረው ድጋፍ ምክንያት በጤና፣ ትምህርትና ግብርና ዘርፎች ላይ ተፈጥሮ የነበረውን ጫና እንደሚያቃልል ተገልጿል። ሸገር ሬዲዮ