EvaSUE |ኢቫሱ
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎችና ምሩቃን ማሕበር [ኢቫሱ] -ከ1950ዎቹ ጀምሮ #ተቀዳሚ_ዐላማ፤የምንኖርለት:- <<ተማሪዎችን በማገልገል የእግዚአብሔርን መንግስት ማስፋት>> ኢቫሱ፣ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ #176 የዩኒቨርሲቲና ኮሌጅ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ሕብረቶችን በማቀፍ ያገለግላል። #በዚህ_ቻናል:- ☞ለካምፓስ ሕብረቶች የሚጠቅሙ መልእክቶች ይተላለፉበታል!
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام EvaSUE |ኢቫሱ
کانال EvaSUE |ኢቫሱ (@evasue58) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 16 057 مشترک است و جایگاه 5 329 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 104 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 16 057 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 01 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 342 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 5 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 18.01% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.55% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 2 890 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 533 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 33 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎችና ምሩቃን ማሕበር [ኢቫሱ] -ከ1950ዎቹ ጀምሮ
#ተቀዳሚ_ዐላማ፤የምንኖርለት:-
<<ተማሪዎችን በማገልገል የእግዚአብሔርን መንግስት ማስፋት>>
ኢቫሱ፣ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ #176 የዩኒቨርሲቲና ኮሌጅ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ሕብረቶችን በማቀፍ ያገለግላል።
#በዚህ_ቻናል:-
☞ለካምፓስ ሕብረቶች የሚጠቅሙ መልእክቶች ይተላለፉበ...”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 02 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
ሉኪዮስ ቅምሻዐይኖቼን ወደ ተራሮች አነሣሁ፤ ረድኤቴ ከወዴት ይመጣል? ረድኤቴ ሰማይንና ምድርን ከፈጠረ፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ይመጣል። መዝሙር 121፥1-2 ልብ በብዙ ዝለት ስታልፍ ዐይኖች ረድኤት ፍለጋ ማይንከራተቱበት የለም ። የጠብቅነው ሳይሆን ሲቀር ፣ የፈለግነው ፤ከደጅ ቢርቅ ፣ የወደድነው የከዳን ለት ፣ የሰበሰብነው ተበትኖ ውጥንቅጡ ሲጠፋብን ፣ የታመነው ጉልበታችን ዝልፍልፍ ሲል ፤ ነፍስያችን ዙሪያ ገባውን ተመልክቶ በፍርኃት ሲሸበብ ረድኤት ፍለጋ ዐይኖቻችን ወዲህ ወዲያ ይንገላወዳሉ ። ዐይን የሰውነት መብራት ነው ። ዐይን ያረፈበት ልብ ያመነበት ነው ። መላ አካል የት አለህ ቢሉት ልብ ያለበት እንዲል ። የዐይን መንከራተት እንዲሁም መራኮት የልብን መታወክ ያሳብቃል ። ልብ የታወከ እንደሆነ ረፍት ለጋሽ ረድኤት ፍለጋ መኳተን የሚጠበቅ እንጂ ቅንጦት አይደለም ። ዐይኖቻችን ረድኤት ፈለጋ ቸኩለው ሚያርፉት ከፊት ተደግኖ ባለው ተራራ እንጂ ተራራውን ከፈጠረው አይደለም ። ክርስቲያን ከተደገነው ተራራ የሚልቀውን አምላከ እግዚአብሔርን ማየት ሚችልበት የእምነት ጋሻ የተላበሰ ካለሆነ በቀር ተራራውን ከለላ ፣ ጠባቂ እና አኗሪ በማድረግ መዛሉ አይቀርምና ዘማሪው የረድኤቱን ምንጭ ሲገልጥ " ረድኤቴ ሰማይንና ምድርን ከፈጠረ፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ይመጣል።" ብሎ መግለጡ ምነኛ ግሩም ነው ። ፊታችን ከተደገነው ተራራ ይልቅ ሰማይንና ምድርን የፈጠረውን አምላክ እግዚአብሔር ማየትስ ምነኛ መታደል ነው ። ✍️ጌታሁን አያኖ
ቃል ጸሎት እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ፤ በክንፎችህም ጥላ ሰውረኝ፤ መዝሙር 17፥8አቤቱ ጠብቀኝ ! ትድግናህ የሚያሻኝ ድኩም ፣ ጠብቆትህ የሚያስፈልገኝ ፣ ለአውሬ ለሌባ ተጋላጫ የሆንኹ በግ ፣ ከለላህ የሚያኖረኝ ልል ፣ ማዳናህ ሚፈውሰኝ ሕማም ፣ እጅህ የሚመራኝ ተጓዝ ፣ ቃልህ የሚያጸናኝ ወላዋይ ነኝና እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ ። የዐይንን ብሌን ከራስ በታች ከሌላው የሰውነት ክፍል ሁሉ ከፍ አድርገህ ፥ በማበጀት ከብዙ ጥፋት እንዲጠበቅ እንዳደረግህ ፤ ከዚህ ዓለም ክፋት እና ነውር በላይ በጽድቅህ ከፍታ እግሮቼን እንድታጸና እማጸንሃለሁ ። የዐይንን ብሌን በተከለለ ሥፍራ እንዳኖርከው አቤቱ ባርያህንም በእቅፍህ እንድታኖረኝ አሻለሁ ። ንስር ጫጩቶቿን በክንፎቿ ሰውራ ከውጩ ብርድ ሙቀትን እንደምትቸር ፣ ከፀሓዩም ከልላ ጥላ እንድምትሆነው ፣ ከዝናብ ከውርጭ ሸሽጋ በጉያዋ እንደምታሳርፍ አቤቱ ልጅህ ነኝና ከዚህ ዓለም ዐመጽ እና ነውር እንዲሁም ክፋት ሁሉ በክንፎችህ ሰውረኝ ። አምላክ ሆይ፤ ስለምትመልስልኝ ስምህን በመጥራት ልመናዬን አቅርቤያለሁና ስማኝ ። በእረኝነትህ እስከፍጻሜው አኑረኝ ፣ ለዘላለሙ አሜን !! ✍️ጌታሁን አያኖ
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
