es
Feedback
EvaSUE |ኢቫሱ

EvaSUE |ኢቫሱ

Ir al canal en Telegram

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎችና ምሩቃን ማሕበር [ኢቫሱ] -ከ1950ዎቹ ጀምሮ #ተቀዳሚ_ዐላማ፤የምንኖርለት:- <<ተማሪዎችን በማገልገል የእግዚአብሔርን መንግስት ማስፋት>> ኢቫሱ፣ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ #176 የዩኒቨርሲቲና ኮሌጅ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ሕብረቶችን በማቀፍ ያገለግላል። #በዚህ_ቻናል:- ☞ለካምፓስ ሕብረቶች የሚጠቅሙ መልእክቶች ይተላለፉበታል!

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EvaSUE |ኢቫሱ

El canal EvaSUE |ኢቫሱ (@evasue58) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 849 suscriptores, ocupando la posición 5 421 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 120 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 849 suscriptores.

Según los últimos datos del 11 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 342, y en las últimas 24 horas de 16, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 43.56%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 18.69% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 6 904 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 962 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 65.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎችና ምሩቃን ማሕበር [ኢቫሱ] -ከ1950ዎቹ ጀምሮ #ተቀዳሚ_ዐላማ፤የምንኖርለት:- <<ተማሪዎችን በማገልገል የእግዚአብሔርን መንግስት ማስፋት>> ኢቫሱ፣ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ #176 የዩኒቨርሲቲና ኮሌጅ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ሕብረቶችን በማቀፍ ያገለግላል። #በዚህ_ቻናል:- ☞ለካምፓስ ሕብረቶች የሚጠቅሙ መልእክቶች ይተላለፉበ...

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 12 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 849
Suscriptores
+1624 horas
+1087 días
+34230 días
Archivo de publicaciones
ድካሜን አውቃለሁ ። በጥቂት ነገር ልቤ በፍረኃት ተሸብቦ ሲንገላወድ የምኖር ልልዘሊል ነኝ ። ብርታቴ ሆይ ያላንተ እግሮቼ ጸንተው መቆም ይሳናቸዋል ። የቆምኹ እየመሰለኝ ልወድቅ ምንተፋተፍ ተሰባሪ ነ
ድካሜን አውቃለሁ ። በጥቂት ነገር ልቤ በፍረኃት ተሸብቦ ሲንገላወድ የምኖር ልልዘሊል ነኝ ። ብርታቴ ሆይ ያላንተ  እግሮቼ ጸንተው መቆም ይሳናቸዋል ። የቆምኹ እየመሰለኝ ልወድቅ ምንተፋተፍ ተሰባሪ ነኝና ብርታቴ ሆይ አንተን ተስፋ አደርጋለሁ ። በምኞት ማዕበል ዐይኖቼ ሲናጡ ፣ ልቡናዬም ክፋትን ሲያወጠንጥን ፣ እጆቼ ለነውር ሲዘረጉ ፣ መላአካሌ መሪ እንደሌለው መርከብ እማያውቅበት አገር ሲነጉድ መመለሻ መንገዴ አንተው ነህና ፤ በዚህ ኹሉ አንተን እጠብቃለሁ ። " ሰው እንዴት በዚህ ይወድቃል? "ብዬ ባልኹት ጉዳይ ራሴን አገኛለሁና አቤቱ እጆቼን ይዘኽ ትመራኝ ዘንድ ረድኤትህን እሻለሁ ።  ምትታመን ታማኝ ወዳጅ አምላኬ እግዚአብሔር ሆይ ካንተ በቀር በጎነት የለኝም ።  ትናንትና ዛሬም እስከዘላለም ያው ኾነህ በምትኖር ባንተ እንጂ ዛሬ ባለኝ አቋም ፣ ትላንት ባሳለፍኹት ትጋት ታምኜ ነገን ተስፋ አላደርግም ። ባሳልፍኸው ትናንት ፣ ባሳየኸኝ ዛሬ ፣ በእጅህ ባለው ነገ አለመናወጽ ጸንተህ የምትኖር አንተ ነህና ጉልበቴ ሆይ አንተን እጠበቃለሁ ። ብርታቴ ሆይ ፤ አምላኬም ነህና አንተን እጠብቃለሁ ። በእጆችህ አበጃጅተህ ያቆምከኝ ያንተው ፍጥረት ነኝና ሠሪዬም ነህ ። በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ የመስቀል ላይ ጣር  ልጅህ አድርገህ የተቀበልኸኝ አባቴም ነህና ፤ ምስጋና ላንተ ይሁን ።  ተጠግቼ "እፎዬ "ምለው ። እውነተኛውን ርጋታም ማገኘው ፤ ባንተው ነውና መጠጊያዬ ሆይ ክብር እና ውዳሴ ላንተ ይሁን!! ለዘላለሙ አሜን!

በራልን እግዜሩ ጋር ንክኪ ያለው ሰው አቤት መታደሉ። ከክንፉ ጥላ ስር ተሸሽጎ በጥበቃው ልቡ አርፎ ይኖራል። ከመረጃ ባለፈ በተጨባጭ ሁኔታ በሒወቱ እውን ለሆነለት አምላክ ፈቃዱን አስገዝቶ ይኖራል።
በራልን እግዜሩ ጋር ንክኪ ያለው ሰው አቤት መታደሉ። ከክንፉ ጥላ ስር ተሸሽጎ በጥበቃው ልቡ አርፎ ይኖራል። ከመረጃ ባለፈ በተጨባጭ ሁኔታ በሒወቱ እውን ለሆነለት አምላክ ፈቃዱን አስገዝቶ ይኖራል። እግዚአብሔር ራሱን ካልገለጠልን በስተቀር በራሳችን ጥረት ልንደርስበት አንችልም ፤ በሰው ቀመር እና ስሌት አይገኝም ፤ በሰው የአዕምሮ ልህቀት ታስሶ አይደረስበትም። ታዲያ ይህ ረቂቅ እና ምጡቅ አምላክ ራሱን ለሰው ልጆች መግለጥ በጎ ፈቃዱ ሆኖ በልጁ በክርስቶስ በኩል መልኩን፣ ባህሪውን እና ማንነቱን አሳየን። እግዚአብሔር ተገለጠልን በራልን። እርሱን ማወቅ የዘላለም ህይወት ነው። ከእርሱ ጋር ተጣብቆ መኖር የህይወት ትርጉም ነው። ከእርሱ ጋር መወዳጀት የእረፍት አለም ነው። እርሱን ማመን ልብን የሚያረጋ መልህቅ ነው። ታዲያ እግዜሩን ከመረጃ ባለፈ በህይወታችን እውን ይሆንልን ዘንድ ይበራልን ዘንድ የግድ ያስፈልጋል። እንዲበራልን ይበልጡን እንድናውቀው እና እንድንረዳው ደግሞ ወደእርሱ ቀርበን ልንለምነው በፀሎት እንማፀነው ዘንድ ይገባል፤ እንዲሁ በአዕምሮ የምናውቃቸውን የእግዚአብሔር ቃል እውነቶች መተግበር ይገባናል ። ከትላንቱ ዛሬ ፤ ከዛሬ ደግሞ ነገ እግዚአብሔርን በማወቅ ህይወት እንዲሁም በእውነተኛ መረዳት እና ግንዛቤ እያወቅነው እንኖር ዘንድ ፀጋ ይብዛልን ✍️ ካሌብ ካሳሁን

ቃል ጸሎት እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ፤ በክንፎችህም ጥላ ሰውረኝ፤ መዝሙር 17፥8 አቤቱ ጠብቀኝ ! ትድግናህ የሚያሻኝ ድኩም ፣ ጠብቆትህ የሚያስፈልገኝ ፣ ለአውሬ ለሌባ ተጋላጫ የሆንኹ በግ ፣ ከለ
ቃል ጸሎት እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ፤ በክንፎችህም ጥላ ሰውረኝ፤ መዝሙር 17፥8
አቤቱ ጠብቀኝ ! ትድግናህ የሚያሻኝ ድኩም ፣ ጠብቆትህ የሚያስፈልገኝ ፣ ለአውሬ ለሌባ ተጋላጫ የሆንኹ በግ ፣ ከለላህ የሚያኖረኝ ልል ፣ ማዳናህ ሚፈውሰኝ ሕማም ፣ እጅህ የሚመራኝ ተጓዝ ፣ ቃልህ የሚያጸናኝ ወላዋይ ነኝና እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ ። የዐይንን ብሌን ከራስ በታች ከሌላው የሰውነት ክፍል ሁሉ ከፍ አድርገህ ፥ በማበጀት ከብዙ ጥፋት እንዲጠበቅ እንዳደረግህ ፤ ከዚህ ዓለም ክፋት እና ነውር በላይ  በጽድቅህ ከፍታ እግሮቼን እንድታጸና እማጸንሃለሁ ። የዐይንን ብሌን በተከለለ ሥፍራ እንዳኖርከው አቤቱ ባርያህንም በእቅፍህ እንድታኖረኝ አሻለሁ ። ንስር ጫጩቶቿን በክንፎቿ ሰውራ ከውጩ ብርድ ሙቀትን እንደምትቸር ፣ ከፀሓዩም ከልላ ጥላ እንድምትሆነው ፣ ከዝናብ ከውርጭ ሸሽጋ በጉያዋ እንደምታሳርፍ አቤቱ  ልጅህ ነኝና ከዚህ ዓለም ዐመጽ እና ነውር እንዲሁም ክፋት ሁሉ በክንፎችህ ሰውረኝ ። አምላክ ሆይ፤ ስለምትመልስልኝ ስምህን በመጥራት ልመናዬን አቅርቤያለሁና ስማኝ ። በእረኝነትህ እስከፍጻሜው አኑረኝ ፣ ለዘላለሙ አሜን !! ✍️ጌታሁን አያኖ

በመታመን በየዕለት ህይወታችን ላይ እምነት (መታመን) የሚባለው ነገር የዘወትር ተግባራችንን የያዘ ነው። ለምሳሌ የተቀመጥንበት ወንበር እንደማይጥለን ስለምናምን ያለሀሳብ ዘና ብለን እንቀመጥበታለን።
በመታመን በየዕለት ህይወታችን ላይ እምነት (መታመን) የሚባለው ነገር የዘወትር ተግባራችንን የያዘ ነው። ለምሳሌ የተቀመጥንበት ወንበር እንደማይጥለን ስለምናምን ያለሀሳብ ዘና ብለን እንቀመጥበታለን። እግዚአብሔር በማንነቱ ታማኝ ስለሆነ በሙሉ ልባችን በእርሱ ላይ እንድንታመን ይፈልጋል። እግዚአብሔርን አምነዋለሁ( መታመኛየ ነው)  ማለት ሒወቴን እንድመራበት የሰጠኝ መመሪያ በሰው አይን የሚያዋጣ ባይመስልም ነገር ግን እሱ ለእኔ መልካም የሆነውን ስለሚያስብ ያንን ጎዳና ልጓዝበት ወስኛለሁ ማለት ነው። እግዚአብሔር የመረጠልኝን መንገድ በመከተሌ እንደከሰርኩ ያህል እንዲሰማኝ የሚያደርጉ ድምፆች በዙሪያየ ቢያንባርቁም መንገዱን መጓዝ ግን እቀጥላለሁ ማለት ነው። እሱን በመጠበቄ ጊዜየ እንዳረፈደብኝ ቢሰማኝም በራሴ አካሄድ ቅልጥፍጥፍ ብል ከማገኘው እስማኤል በላይ ጊዜው ያለፈ በሚመስል ወቅት የሚሰጠኝን ይስሀቅን እጠብቃለሁ ማለት ነው። በእግዚአብሔር እታመናለሁ ማለት በራሴ ማስተዋል አልደገፍም ፤ ያገኘሁትን መልካም የሚመስል አጋጣሚ በጠቅላላ ፈቃዱን ሳላረጋግጥ አልጠቀምም ማለት ነው ። ለእግዜሩ ወገንተኛ ሆኜ ከማጣቸው እድሎች በላይ እሱ በራሱ ጊዜ የእሱ ፈቃድ ያለበትን በር ይከፍትልኛል ማለት ነው ባይከፍትልኝም እንኳ እሱ የታመነ  አምላክ ነው ብሎ ልብን በእግዚአብሔር ሀሳብ ማፅናት ነው። ቢታመኑት የሚያስታምን ፤ አደራ የማይበላ ፤ ባለመታመን ተከሶ የማያውቅ የፀና ታማኝ አምላክ የሚያደላድል አለት ኢየሱስ ክርስቶስ አለ። ይሄ ጌታ ለላቀው ለዘላለም ሒወት በመስቀል ላይ እስከመሞት የታመነልን አምላክ ነውና ለምድሩ  አይጠረጠርም። ለሰማይ ወፎች የሚያስብ ጌታ ለልጆቹማ እንዴት የበለጠ አያስብም? ልባችን በእርሱ እንዲታመንልን ጌታ ፀጋውን ያብዛልን ✍️ ካሌብ ካሳሁን

ዘፍጥረት መግቢያ ዘለለው አርጋው https://youtu.be/jKXOQcQVFlc

በፅድቅ ኑሮ የሰው ልጅ በዚህ ምድር ሲኖር ሒወትን ቀለል አድርጎ ለመኖር ይፈልጋል። ከዚህም የተነሳ ሊደርስ ካሰበበት ቦታ ለመድረስ ትክክለኛውን ረጅሙን እና ዋጋ የሚያስከፍለውን መንገድ ትቶ አቋራጭ
በፅድቅ ኑሮ የሰው ልጅ በዚህ ምድር ሲኖር ሒወትን ቀለል አድርጎ ለመኖር ይፈልጋል። ከዚህም የተነሳ ሊደርስ ካሰበበት ቦታ ለመድረስ ትክክለኛውን ረጅሙን እና ዋጋ የሚያስከፍለውን መንገድ ትቶ አቋራጭ መንገዶችን ፤ የእጥፍ ጥልጥፍ አካሄዶችን በመምረጥ ይጓዛል። እግዜሩ ያስቀመጠው የአኗኗር መርህን ለመከተል ትግል ይሆንበታል ምክንያቱስ ቢባል "በፍየል ዘመን በግ አትሁን" የሚለው የዚህች ምድር ብሒል ውስጥ ውስጡን ሰርስሮት ገብቷል። ከዚህም የተነሳ መጓዝ በሚገባው የሒወት መንገድ ላይ የማይገባ አካሄድን መንገድ ቀይሶ ለመንጎድ ሲታትር ይስተዋላል። እግዜሩ ደግሞ ፆድቅ አምላክ ነውና ከእኛ የፅድቅን ኑሮ ይፈልጋል። እግዚአብሔር ነገሮቻችንን በእጃችን እንዳስገባን ብቻ ሳይሆን እነዚያን ስኬቶቻችንን ለማግኘት የሄድንባቸውን መንገዶችም ጭምር ይመዝናቸዋል። እግዚአብሔር የውጤት ብቻ ሳይሆን የሒደትም አምላክ ነው። እግዚአብሔርን በማያከብር መንገድ ሄደን ከምናገኘው ትርፍ ይልቅ በእግዚአብሔር መንገድ ተጉዘን የምናገኘው ጥቂት ነገር ዋጋ አለው። አጠገባችን የሚገኙ ሰዎች ሳያጠኑ ከሌላ ተማሪ ኮርጀው ጥሩ ውጤት  ቢያመጡ ፤ ጉቦ ተቀብለው ኑሮአቸውን ቢያስተካክሉ ፤ ዝምድናን ተጠቅመው ስልጣንን ቢይዙ ፤ ውጭ ሀገር ለመሄድ የሀሰት ትዳር ቢመሠርቱ... እግዚአብሔር የፃድቃንን መንገድ  ስለሚያውቅ የክፋዎችን ለሚያውቅ የክፋዎች መንገድ መጥፋቱ አይቀርም። እግዚአብሔር ሊያጠፋው እና ነፋስ ጠርጎ እንዲወስደው በወሰነው ከክፋ መንገድ መመለስ ሁነኛ መፍትሄ ነው። እግዚአብሔር ፃድቅ አምላክ ስለሆነ ከእኛም የፅድቅን ኑሮ(የእሱን መርህ እየተከተሉ እንድንኖር) ይፈልጋል ዋጋ ቢያስከፍልም ምክንያቱም መስቀልን መሸከም ይሄ ስለሆነ። ጌታ ፀጋውን ያብዛልን ✍️ ካሌብ ካሳሁን

መመለስ እግዜሩ እንደልቤ ያለው ንጉስ ዳዊት ሀጢያትን ሰራ፤ ሳተ ተሳሳተ ። ሚስቱ ያልሆነች ሴት ጋር ተኛ። አዳም ሀጢያትን ከሰራ በኃላ እርቃኑን መሆኑን ሲያውቅ ቅጠል በማገልደም የራሱን ችግር ከእግ
መመለስ እግዜሩ እንደልቤ ያለው ንጉስ ዳዊት ሀጢያትን ሰራ፤ ሳተ ተሳሳተ ። ሚስቱ ያልሆነች ሴት ጋር ተኛ። አዳም ሀጢያትን ከሰራ በኃላ እርቃኑን መሆኑን ሲያውቅ ቅጠል በማገልደም የራሱን ችግር ከእግዜሩ ሸሽቶ በራሱ ለመቅረፍ እንደተጣጣረ ሁሉ ንጉስ ዳዊትም ይህ ሀጢያቱን ለመሸፈን ሌላ ሀጢያትን አደረገ። አብሯት የተኛትን ሴት ባል አስገደለ። እግዚአብሔርም ነብዩን ናታንን ልኮ ዳዊትን ገሰፀው በዚህ ጊዜ ዳዊት አላስተባበለም ፤ ለመካድ አልሞከረም፤ "ንጉስ ነኝኮ እንዴት እንደዚህ ትናገረኛለህ" አላለም ፤ ጥቅስ ጠቅሶ ስህተቱን ለማፅደቅ አልፈለገም ይልቁንስ ልቡን ለእግዜሩ አጋለጠ ፤ ያደረገውን እያንዳንዷን ሀጢያት በአንደበቱ እየተናዘዘ ምህረትን ለመነ ፤ ራሱን ለእግዚአብሔር ምህረት አሳልፎ ሰጠ። እኛም ከእግዚአብሔር ጋር ተወዳጅተን ለመቀጠል ካስፈለገን በመንገዳችን ላይ ላጋጠመን ሀጢያት እና ጥፋት በንሰሀ የመመለስ አለብን እንጂ "ካፈርኩ አይመልሰኝ" በማለት በጥፋት መንገድ መጓዝ ትልቅ ክስረት ነው።መንገዳችንን ማስተካከል ፤ ከጠፋንበት መመለስ ፤ ልባችንን ለቃሉ ተግሳፅ ማጋለጥ ፤ በትህትና እና በተዋረደ መንፈስ እውነትን እየተናዘዙ በጌታ ፊት ግልፅ ሆኖ መቅረብ ሁነኛ መድሀኒት ነው። እኛም ለሀጢያታችን እና ለጥፋቶቻችን አቃቂር ከማውጣት ይልቅ እንፈወስ ዘንድ ፊታችንን ወደ እግዜሩ መመለስ ይሁንልን ✍️ ካሌብ ካሳሁን

ሚገኝበት ቦታ የሰው ልጅ በህይወት ጎዳና ሲጓዝ መንገዱን የሚጀምረው በመወለድ ፤ የሚጨርሰው ደግሞ በሞት ነው። በሕይወቱ ውስጥ የተለያዩ ምዕራፎችን ቢያልፍም ድምድማቱ ሞት ፍፃሜው ከአፈር በታች መሆን
ሚገኝበት ቦታ የሰው ልጅ በህይወት ጎዳና ሲጓዝ መንገዱን የሚጀምረው በመወለድ ፤ የሚጨርሰው ደግሞ በሞት ነው። በሕይወቱ ውስጥ የተለያዩ ምዕራፎችን ቢያልፍም ድምድማቱ ሞት ፍፃሜው ከአፈር በታች መሆን ነው። ፍፁም አምላክ ፍፁም ሰው የሆነው የጌታ ኢየሱስ ህይወት ግን እንደዚህ አልነበረም። ጅማሬ የሌለው የዘላለም አምላክ የሆነው እርሱ ስጋን ለብሶ ወደ ምድር ወረደ። የአባቱን ፈቃድ እየፈፀመ ኖረ። ለሰው ልጆች ሀጢያት ሲል በመስቀል ላይ በመሞት ዋጋን ከፈለ። የአለም ቤዛ ፤ ለሰው ልጆች መድሀኒት ሆነ። ሞት ሊገታው መቃብር ውጦ ሊያቀረው አልቻለም ፤ በመቃብሩ የተከረቸመው ዲንጋይ እና በዙሪያው ያሉ መቃብሩን የሚጠብቁ ወታደሮች ሊያስቆሙት አልቻሉም። ተነስቷል ሞትን ድል ነስቷል። በማለዳ ወደመቃብሩ ሽቱ ይዘው ለሄዱ ሰዎች " ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።" እንዳሏቸው ሁሉ እኛስ ይህንን የትንሳኤውን ጌታ የት ነው እየፈለግነው ያለነው? በፆም በፀሎት በህብረት ውስጥ በቅዱስ ቃሉ ውስጥ ነው? ወይስ በአለማዊነት በመዋከብ ሰሞነኛ በመሆን? በሀጢያታዊ ሕይወት፤ በአመፃ ምልልስ ከሆነ "እሱ(ኢየሱስ) በዚያ የለም" ። በንሰሀ በመመለስ ፤ በፅድቅ ኑሮ በመኖር እና እሱን በመታመን ከሆነ ግን እርሱ(ኢየሱስ) በዚያ አለ። እርሱ በሚገኝበት ፍለጋችንን እናደርግ ዘንድ ፀጋው ይርዳን!

https://t.me/Easter_PostCard_bot Generate your fasika digital post cards
https://t.me/Easter_PostCard_bot Generate your fasika digital post cards

ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነቱን ትቶ ክብሩን ትቶ ዙፋኑን ትቶ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ ዋለ! #ድጋሚ_ይነበብ
ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነቱን ትቶ ክብሩን ትቶ ዙፋኑን ትቶ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ ዋለ! #ድጋሚ_ይነበብ

ከፍል — 2
+8
ከፍል — 2