ch
Feedback
EvaSUE |ኢቫሱ

EvaSUE |ኢቫሱ

前往频道在 Telegram

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎችና ምሩቃን ማሕበር [ኢቫሱ] -ከ1950ዎቹ ጀምሮ #ተቀዳሚ_ዐላማ፤የምንኖርለት:- <<ተማሪዎችን በማገልገል የእግዚአብሔርን መንግስት ማስፋት>> ኢቫሱ፣ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ #176 የዩኒቨርሲቲና ኮሌጅ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ሕብረቶችን በማቀፍ ያገለግላል። #በዚህ_ቻናል:- ☞ለካምፓስ ሕብረቶች የሚጠቅሙ መልእክቶች ይተላለፉበታል!

显示更多

📈 Telegram 频道 EvaSUE |ኢቫሱ 的分析概览

频道 EvaSUE |ኢቫሱ (@evasue58) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 836 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 436,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 125

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 836 名订阅者。

根据 10 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 364,过去 24 小时变化为 23,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 42.92%。内容发布后 24 小时内通常能获得 18.71% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 6 795 次浏览,首日通常累积 2 962 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 65

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎችና ምሩቃን ማሕበር [ኢቫሱ] -ከ1950ዎቹ ጀምሮ #ተቀዳሚ_ዐላማ፤የምንኖርለት:- <<ተማሪዎችን በማገልገል የእግዚአብሔርን መንግስት ማስፋት>> ኢቫሱ፣ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ #176 የዩኒቨርሲቲና ኮሌጅ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ሕብረቶችን በማቀፍ ያገለግላል። #በዚህ_ቻናል:- ☞ለካምፓስ ሕብረቶች የሚጠቅሙ መልእክቶች ይተላለፉበ...

凭借高频更新(最新数据采集于 11 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

15 836
订阅者
+2324 小时
+1147
+36430
帖子存档
ድካሜን አውቃለሁ ። በጥቂት ነገር ልቤ በፍረኃት ተሸብቦ ሲንገላወድ የምኖር ልልዘሊል ነኝ ። ብርታቴ ሆይ ያላንተ እግሮቼ ጸንተው መቆም ይሳናቸዋል ። የቆምኹ እየመሰለኝ ልወድቅ ምንተፋተፍ ተሰባሪ ነ
ድካሜን አውቃለሁ ። በጥቂት ነገር ልቤ በፍረኃት ተሸብቦ ሲንገላወድ የምኖር ልልዘሊል ነኝ ። ብርታቴ ሆይ ያላንተ  እግሮቼ ጸንተው መቆም ይሳናቸዋል ። የቆምኹ እየመሰለኝ ልወድቅ ምንተፋተፍ ተሰባሪ ነኝና ብርታቴ ሆይ አንተን ተስፋ አደርጋለሁ ። በምኞት ማዕበል ዐይኖቼ ሲናጡ ፣ ልቡናዬም ክፋትን ሲያወጠንጥን ፣ እጆቼ ለነውር ሲዘረጉ ፣ መላአካሌ መሪ እንደሌለው መርከብ እማያውቅበት አገር ሲነጉድ መመለሻ መንገዴ አንተው ነህና ፤ በዚህ ኹሉ አንተን እጠብቃለሁ ። " ሰው እንዴት በዚህ ይወድቃል? "ብዬ ባልኹት ጉዳይ ራሴን አገኛለሁና አቤቱ እጆቼን ይዘኽ ትመራኝ ዘንድ ረድኤትህን እሻለሁ ።  ምትታመን ታማኝ ወዳጅ አምላኬ እግዚአብሔር ሆይ ካንተ በቀር በጎነት የለኝም ።  ትናንትና ዛሬም እስከዘላለም ያው ኾነህ በምትኖር ባንተ እንጂ ዛሬ ባለኝ አቋም ፣ ትላንት ባሳለፍኹት ትጋት ታምኜ ነገን ተስፋ አላደርግም ። ባሳልፍኸው ትናንት ፣ ባሳየኸኝ ዛሬ ፣ በእጅህ ባለው ነገ አለመናወጽ ጸንተህ የምትኖር አንተ ነህና ጉልበቴ ሆይ አንተን እጠበቃለሁ ። ብርታቴ ሆይ ፤ አምላኬም ነህና አንተን እጠብቃለሁ ። በእጆችህ አበጃጅተህ ያቆምከኝ ያንተው ፍጥረት ነኝና ሠሪዬም ነህ ። በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ የመስቀል ላይ ጣር  ልጅህ አድርገህ የተቀበልኸኝ አባቴም ነህና ፤ ምስጋና ላንተ ይሁን ።  ተጠግቼ "እፎዬ "ምለው ። እውነተኛውን ርጋታም ማገኘው ፤ ባንተው ነውና መጠጊያዬ ሆይ ክብር እና ውዳሴ ላንተ ይሁን!! ለዘላለሙ አሜን!

በራልን እግዜሩ ጋር ንክኪ ያለው ሰው አቤት መታደሉ። ከክንፉ ጥላ ስር ተሸሽጎ በጥበቃው ልቡ አርፎ ይኖራል። ከመረጃ ባለፈ በተጨባጭ ሁኔታ በሒወቱ እውን ለሆነለት አምላክ ፈቃዱን አስገዝቶ ይኖራል።
በራልን እግዜሩ ጋር ንክኪ ያለው ሰው አቤት መታደሉ። ከክንፉ ጥላ ስር ተሸሽጎ በጥበቃው ልቡ አርፎ ይኖራል። ከመረጃ ባለፈ በተጨባጭ ሁኔታ በሒወቱ እውን ለሆነለት አምላክ ፈቃዱን አስገዝቶ ይኖራል። እግዚአብሔር ራሱን ካልገለጠልን በስተቀር በራሳችን ጥረት ልንደርስበት አንችልም ፤ በሰው ቀመር እና ስሌት አይገኝም ፤ በሰው የአዕምሮ ልህቀት ታስሶ አይደረስበትም። ታዲያ ይህ ረቂቅ እና ምጡቅ አምላክ ራሱን ለሰው ልጆች መግለጥ በጎ ፈቃዱ ሆኖ በልጁ በክርስቶስ በኩል መልኩን፣ ባህሪውን እና ማንነቱን አሳየን። እግዚአብሔር ተገለጠልን በራልን። እርሱን ማወቅ የዘላለም ህይወት ነው። ከእርሱ ጋር ተጣብቆ መኖር የህይወት ትርጉም ነው። ከእርሱ ጋር መወዳጀት የእረፍት አለም ነው። እርሱን ማመን ልብን የሚያረጋ መልህቅ ነው። ታዲያ እግዜሩን ከመረጃ ባለፈ በህይወታችን እውን ይሆንልን ዘንድ ይበራልን ዘንድ የግድ ያስፈልጋል። እንዲበራልን ይበልጡን እንድናውቀው እና እንድንረዳው ደግሞ ወደእርሱ ቀርበን ልንለምነው በፀሎት እንማፀነው ዘንድ ይገባል፤ እንዲሁ በአዕምሮ የምናውቃቸውን የእግዚአብሔር ቃል እውነቶች መተግበር ይገባናል ። ከትላንቱ ዛሬ ፤ ከዛሬ ደግሞ ነገ እግዚአብሔርን በማወቅ ህይወት እንዲሁም በእውነተኛ መረዳት እና ግንዛቤ እያወቅነው እንኖር ዘንድ ፀጋ ይብዛልን ✍️ ካሌብ ካሳሁን

ቃል ጸሎት እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ፤ በክንፎችህም ጥላ ሰውረኝ፤ መዝሙር 17፥8 አቤቱ ጠብቀኝ ! ትድግናህ የሚያሻኝ ድኩም ፣ ጠብቆትህ የሚያስፈልገኝ ፣ ለአውሬ ለሌባ ተጋላጫ የሆንኹ በግ ፣ ከለ
ቃል ጸሎት እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ፤ በክንፎችህም ጥላ ሰውረኝ፤ መዝሙር 17፥8
አቤቱ ጠብቀኝ ! ትድግናህ የሚያሻኝ ድኩም ፣ ጠብቆትህ የሚያስፈልገኝ ፣ ለአውሬ ለሌባ ተጋላጫ የሆንኹ በግ ፣ ከለላህ የሚያኖረኝ ልል ፣ ማዳናህ ሚፈውሰኝ ሕማም ፣ እጅህ የሚመራኝ ተጓዝ ፣ ቃልህ የሚያጸናኝ ወላዋይ ነኝና እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ ። የዐይንን ብሌን ከራስ በታች ከሌላው የሰውነት ክፍል ሁሉ ከፍ አድርገህ ፥ በማበጀት ከብዙ ጥፋት እንዲጠበቅ እንዳደረግህ ፤ ከዚህ ዓለም ክፋት እና ነውር በላይ  በጽድቅህ ከፍታ እግሮቼን እንድታጸና እማጸንሃለሁ ። የዐይንን ብሌን በተከለለ ሥፍራ እንዳኖርከው አቤቱ ባርያህንም በእቅፍህ እንድታኖረኝ አሻለሁ ። ንስር ጫጩቶቿን በክንፎቿ ሰውራ ከውጩ ብርድ ሙቀትን እንደምትቸር ፣ ከፀሓዩም ከልላ ጥላ እንድምትሆነው ፣ ከዝናብ ከውርጭ ሸሽጋ በጉያዋ እንደምታሳርፍ አቤቱ  ልጅህ ነኝና ከዚህ ዓለም ዐመጽ እና ነውር እንዲሁም ክፋት ሁሉ በክንፎችህ ሰውረኝ ። አምላክ ሆይ፤ ስለምትመልስልኝ ስምህን በመጥራት ልመናዬን አቅርቤያለሁና ስማኝ ። በእረኝነትህ እስከፍጻሜው አኑረኝ ፣ ለዘላለሙ አሜን !! ✍️ጌታሁን አያኖ

በመታመን በየዕለት ህይወታችን ላይ እምነት (መታመን) የሚባለው ነገር የዘወትር ተግባራችንን የያዘ ነው። ለምሳሌ የተቀመጥንበት ወንበር እንደማይጥለን ስለምናምን ያለሀሳብ ዘና ብለን እንቀመጥበታለን።
በመታመን በየዕለት ህይወታችን ላይ እምነት (መታመን) የሚባለው ነገር የዘወትር ተግባራችንን የያዘ ነው። ለምሳሌ የተቀመጥንበት ወንበር እንደማይጥለን ስለምናምን ያለሀሳብ ዘና ብለን እንቀመጥበታለን። እግዚአብሔር በማንነቱ ታማኝ ስለሆነ በሙሉ ልባችን በእርሱ ላይ እንድንታመን ይፈልጋል። እግዚአብሔርን አምነዋለሁ( መታመኛየ ነው)  ማለት ሒወቴን እንድመራበት የሰጠኝ መመሪያ በሰው አይን የሚያዋጣ ባይመስልም ነገር ግን እሱ ለእኔ መልካም የሆነውን ስለሚያስብ ያንን ጎዳና ልጓዝበት ወስኛለሁ ማለት ነው። እግዚአብሔር የመረጠልኝን መንገድ በመከተሌ እንደከሰርኩ ያህል እንዲሰማኝ የሚያደርጉ ድምፆች በዙሪያየ ቢያንባርቁም መንገዱን መጓዝ ግን እቀጥላለሁ ማለት ነው። እሱን በመጠበቄ ጊዜየ እንዳረፈደብኝ ቢሰማኝም በራሴ አካሄድ ቅልጥፍጥፍ ብል ከማገኘው እስማኤል በላይ ጊዜው ያለፈ በሚመስል ወቅት የሚሰጠኝን ይስሀቅን እጠብቃለሁ ማለት ነው። በእግዚአብሔር እታመናለሁ ማለት በራሴ ማስተዋል አልደገፍም ፤ ያገኘሁትን መልካም የሚመስል አጋጣሚ በጠቅላላ ፈቃዱን ሳላረጋግጥ አልጠቀምም ማለት ነው ። ለእግዜሩ ወገንተኛ ሆኜ ከማጣቸው እድሎች በላይ እሱ በራሱ ጊዜ የእሱ ፈቃድ ያለበትን በር ይከፍትልኛል ማለት ነው ባይከፍትልኝም እንኳ እሱ የታመነ  አምላክ ነው ብሎ ልብን በእግዚአብሔር ሀሳብ ማፅናት ነው። ቢታመኑት የሚያስታምን ፤ አደራ የማይበላ ፤ ባለመታመን ተከሶ የማያውቅ የፀና ታማኝ አምላክ የሚያደላድል አለት ኢየሱስ ክርስቶስ አለ። ይሄ ጌታ ለላቀው ለዘላለም ሒወት በመስቀል ላይ እስከመሞት የታመነልን አምላክ ነውና ለምድሩ  አይጠረጠርም። ለሰማይ ወፎች የሚያስብ ጌታ ለልጆቹማ እንዴት የበለጠ አያስብም? ልባችን በእርሱ እንዲታመንልን ጌታ ፀጋውን ያብዛልን ✍️ ካሌብ ካሳሁን

ዘፍጥረት መግቢያ ዘለለው አርጋው https://youtu.be/jKXOQcQVFlc

በፅድቅ ኑሮ የሰው ልጅ በዚህ ምድር ሲኖር ሒወትን ቀለል አድርጎ ለመኖር ይፈልጋል። ከዚህም የተነሳ ሊደርስ ካሰበበት ቦታ ለመድረስ ትክክለኛውን ረጅሙን እና ዋጋ የሚያስከፍለውን መንገድ ትቶ አቋራጭ
በፅድቅ ኑሮ የሰው ልጅ በዚህ ምድር ሲኖር ሒወትን ቀለል አድርጎ ለመኖር ይፈልጋል። ከዚህም የተነሳ ሊደርስ ካሰበበት ቦታ ለመድረስ ትክክለኛውን ረጅሙን እና ዋጋ የሚያስከፍለውን መንገድ ትቶ አቋራጭ መንገዶችን ፤ የእጥፍ ጥልጥፍ አካሄዶችን በመምረጥ ይጓዛል። እግዜሩ ያስቀመጠው የአኗኗር መርህን ለመከተል ትግል ይሆንበታል ምክንያቱስ ቢባል "በፍየል ዘመን በግ አትሁን" የሚለው የዚህች ምድር ብሒል ውስጥ ውስጡን ሰርስሮት ገብቷል። ከዚህም የተነሳ መጓዝ በሚገባው የሒወት መንገድ ላይ የማይገባ አካሄድን መንገድ ቀይሶ ለመንጎድ ሲታትር ይስተዋላል። እግዜሩ ደግሞ ፆድቅ አምላክ ነውና ከእኛ የፅድቅን ኑሮ ይፈልጋል። እግዚአብሔር ነገሮቻችንን በእጃችን እንዳስገባን ብቻ ሳይሆን እነዚያን ስኬቶቻችንን ለማግኘት የሄድንባቸውን መንገዶችም ጭምር ይመዝናቸዋል። እግዚአብሔር የውጤት ብቻ ሳይሆን የሒደትም አምላክ ነው። እግዚአብሔርን በማያከብር መንገድ ሄደን ከምናገኘው ትርፍ ይልቅ በእግዚአብሔር መንገድ ተጉዘን የምናገኘው ጥቂት ነገር ዋጋ አለው። አጠገባችን የሚገኙ ሰዎች ሳያጠኑ ከሌላ ተማሪ ኮርጀው ጥሩ ውጤት  ቢያመጡ ፤ ጉቦ ተቀብለው ኑሮአቸውን ቢያስተካክሉ ፤ ዝምድናን ተጠቅመው ስልጣንን ቢይዙ ፤ ውጭ ሀገር ለመሄድ የሀሰት ትዳር ቢመሠርቱ... እግዚአብሔር የፃድቃንን መንገድ  ስለሚያውቅ የክፋዎችን ለሚያውቅ የክፋዎች መንገድ መጥፋቱ አይቀርም። እግዚአብሔር ሊያጠፋው እና ነፋስ ጠርጎ እንዲወስደው በወሰነው ከክፋ መንገድ መመለስ ሁነኛ መፍትሄ ነው። እግዚአብሔር ፃድቅ አምላክ ስለሆነ ከእኛም የፅድቅን ኑሮ(የእሱን መርህ እየተከተሉ እንድንኖር) ይፈልጋል ዋጋ ቢያስከፍልም ምክንያቱም መስቀልን መሸከም ይሄ ስለሆነ። ጌታ ፀጋውን ያብዛልን ✍️ ካሌብ ካሳሁን

መመለስ እግዜሩ እንደልቤ ያለው ንጉስ ዳዊት ሀጢያትን ሰራ፤ ሳተ ተሳሳተ ። ሚስቱ ያልሆነች ሴት ጋር ተኛ። አዳም ሀጢያትን ከሰራ በኃላ እርቃኑን መሆኑን ሲያውቅ ቅጠል በማገልደም የራሱን ችግር ከእግ
መመለስ እግዜሩ እንደልቤ ያለው ንጉስ ዳዊት ሀጢያትን ሰራ፤ ሳተ ተሳሳተ ። ሚስቱ ያልሆነች ሴት ጋር ተኛ። አዳም ሀጢያትን ከሰራ በኃላ እርቃኑን መሆኑን ሲያውቅ ቅጠል በማገልደም የራሱን ችግር ከእግዜሩ ሸሽቶ በራሱ ለመቅረፍ እንደተጣጣረ ሁሉ ንጉስ ዳዊትም ይህ ሀጢያቱን ለመሸፈን ሌላ ሀጢያትን አደረገ። አብሯት የተኛትን ሴት ባል አስገደለ። እግዚአብሔርም ነብዩን ናታንን ልኮ ዳዊትን ገሰፀው በዚህ ጊዜ ዳዊት አላስተባበለም ፤ ለመካድ አልሞከረም፤ "ንጉስ ነኝኮ እንዴት እንደዚህ ትናገረኛለህ" አላለም ፤ ጥቅስ ጠቅሶ ስህተቱን ለማፅደቅ አልፈለገም ይልቁንስ ልቡን ለእግዜሩ አጋለጠ ፤ ያደረገውን እያንዳንዷን ሀጢያት በአንደበቱ እየተናዘዘ ምህረትን ለመነ ፤ ራሱን ለእግዚአብሔር ምህረት አሳልፎ ሰጠ። እኛም ከእግዚአብሔር ጋር ተወዳጅተን ለመቀጠል ካስፈለገን በመንገዳችን ላይ ላጋጠመን ሀጢያት እና ጥፋት በንሰሀ የመመለስ አለብን እንጂ "ካፈርኩ አይመልሰኝ" በማለት በጥፋት መንገድ መጓዝ ትልቅ ክስረት ነው።መንገዳችንን ማስተካከል ፤ ከጠፋንበት መመለስ ፤ ልባችንን ለቃሉ ተግሳፅ ማጋለጥ ፤ በትህትና እና በተዋረደ መንፈስ እውነትን እየተናዘዙ በጌታ ፊት ግልፅ ሆኖ መቅረብ ሁነኛ መድሀኒት ነው። እኛም ለሀጢያታችን እና ለጥፋቶቻችን አቃቂር ከማውጣት ይልቅ እንፈወስ ዘንድ ፊታችንን ወደ እግዜሩ መመለስ ይሁንልን ✍️ ካሌብ ካሳሁን

ሚገኝበት ቦታ የሰው ልጅ በህይወት ጎዳና ሲጓዝ መንገዱን የሚጀምረው በመወለድ ፤ የሚጨርሰው ደግሞ በሞት ነው። በሕይወቱ ውስጥ የተለያዩ ምዕራፎችን ቢያልፍም ድምድማቱ ሞት ፍፃሜው ከአፈር በታች መሆን
ሚገኝበት ቦታ የሰው ልጅ በህይወት ጎዳና ሲጓዝ መንገዱን የሚጀምረው በመወለድ ፤ የሚጨርሰው ደግሞ በሞት ነው። በሕይወቱ ውስጥ የተለያዩ ምዕራፎችን ቢያልፍም ድምድማቱ ሞት ፍፃሜው ከአፈር በታች መሆን ነው። ፍፁም አምላክ ፍፁም ሰው የሆነው የጌታ ኢየሱስ ህይወት ግን እንደዚህ አልነበረም። ጅማሬ የሌለው የዘላለም አምላክ የሆነው እርሱ ስጋን ለብሶ ወደ ምድር ወረደ። የአባቱን ፈቃድ እየፈፀመ ኖረ። ለሰው ልጆች ሀጢያት ሲል በመስቀል ላይ በመሞት ዋጋን ከፈለ። የአለም ቤዛ ፤ ለሰው ልጆች መድሀኒት ሆነ። ሞት ሊገታው መቃብር ውጦ ሊያቀረው አልቻለም ፤ በመቃብሩ የተከረቸመው ዲንጋይ እና በዙሪያው ያሉ መቃብሩን የሚጠብቁ ወታደሮች ሊያስቆሙት አልቻሉም። ተነስቷል ሞትን ድል ነስቷል። በማለዳ ወደመቃብሩ ሽቱ ይዘው ለሄዱ ሰዎች " ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።" እንዳሏቸው ሁሉ እኛስ ይህንን የትንሳኤውን ጌታ የት ነው እየፈለግነው ያለነው? በፆም በፀሎት በህብረት ውስጥ በቅዱስ ቃሉ ውስጥ ነው? ወይስ በአለማዊነት በመዋከብ ሰሞነኛ በመሆን? በሀጢያታዊ ሕይወት፤ በአመፃ ምልልስ ከሆነ "እሱ(ኢየሱስ) በዚያ የለም" ። በንሰሀ በመመለስ ፤ በፅድቅ ኑሮ በመኖር እና እሱን በመታመን ከሆነ ግን እርሱ(ኢየሱስ) በዚያ አለ። እርሱ በሚገኝበት ፍለጋችንን እናደርግ ዘንድ ፀጋው ይርዳን!

https://t.me/Easter_PostCard_bot Generate your fasika digital post cards
https://t.me/Easter_PostCard_bot Generate your fasika digital post cards

ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነቱን ትቶ ክብሩን ትቶ ዙፋኑን ትቶ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ ዋለ! #ድጋሚ_ይነበብ
ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነቱን ትቶ ክብሩን ትቶ ዙፋኑን ትቶ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ ዋለ! #ድጋሚ_ይነበብ

ከፍል — 2
+8
ከፍል — 2