EvaSUE |ኢቫሱ
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎችና ምሩቃን ማሕበር [ኢቫሱ] -ከ1950ዎቹ ጀምሮ #ተቀዳሚ_ዐላማ፤የምንኖርለት:- <<ተማሪዎችን በማገልገል የእግዚአብሔርን መንግስት ማስፋት>> ኢቫሱ፣ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ #176 የዩኒቨርሲቲና ኮሌጅ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ሕብረቶችን በማቀፍ ያገለግላል። #በዚህ_ቻናል:- ☞ለካምፓስ ሕብረቶች የሚጠቅሙ መልእክቶች ይተላለፉበታል!
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام EvaSUE |ኢቫሱ
کانال EvaSUE |ኢቫሱ (@evasue58) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 16 057 مشترک است و جایگاه 5 329 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 104 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 16 057 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 01 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 342 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 5 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 18.01% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.55% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 2 890 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 533 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 33 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎችና ምሩቃን ማሕበር [ኢቫሱ] -ከ1950ዎቹ ጀምሮ
#ተቀዳሚ_ዐላማ፤የምንኖርለት:-
<<ተማሪዎችን በማገልገል የእግዚአብሔርን መንግስት ማስፋት>>
ኢቫሱ፣ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ #176 የዩኒቨርሲቲና ኮሌጅ ወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ሕብረቶችን በማቀፍ ያገለግላል።
#በዚህ_ቻናል:-
☞ለካምፓስ ሕብረቶች የሚጠቅሙ መልእክቶች ይተላለፉበ...”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 02 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 02 ژوئیه | +7 | |||
| 01 ژوئیه | +5 |
ሉኪዮስ ቅምሻዐይኖቼን ወደ ተራሮች አነሣሁ፤ ረድኤቴ ከወዴት ይመጣል? ረድኤቴ ሰማይንና ምድርን ከፈጠረ፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ይመጣል። መዝሙር 121፥1-2 ልብ በብዙ ዝለት ስታልፍ ዐይኖች ረድኤት ፍለጋ ማይንከራተቱበት የለም ። የጠብቅነው ሳይሆን ሲቀር ፣ የፈለግነው ፤ከደጅ ቢርቅ ፣ የወደድነው የከዳን ለት ፣ የሰበሰብነው ተበትኖ ውጥንቅጡ ሲጠፋብን ፣ የታመነው ጉልበታችን ዝልፍልፍ ሲል ፤ ነፍስያችን ዙሪያ ገባውን ተመልክቶ በፍርኃት ሲሸበብ ረድኤት ፍለጋ ዐይኖቻችን ወዲህ ወዲያ ይንገላወዳሉ ። ዐይን የሰውነት መብራት ነው ። ዐይን ያረፈበት ልብ ያመነበት ነው ። መላ አካል የት አለህ ቢሉት ልብ ያለበት እንዲል ። የዐይን መንከራተት እንዲሁም መራኮት የልብን መታወክ ያሳብቃል ። ልብ የታወከ እንደሆነ ረፍት ለጋሽ ረድኤት ፍለጋ መኳተን የሚጠበቅ እንጂ ቅንጦት አይደለም ። ዐይኖቻችን ረድኤት ፈለጋ ቸኩለው ሚያርፉት ከፊት ተደግኖ ባለው ተራራ እንጂ ተራራውን ከፈጠረው አይደለም ። ክርስቲያን ከተደገነው ተራራ የሚልቀውን አምላከ እግዚአብሔርን ማየት ሚችልበት የእምነት ጋሻ የተላበሰ ካለሆነ በቀር ተራራውን ከለላ ፣ ጠባቂ እና አኗሪ በማድረግ መዛሉ አይቀርምና ዘማሪው የረድኤቱን ምንጭ ሲገልጥ " ረድኤቴ ሰማይንና ምድርን ከፈጠረ፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ይመጣል።" ብሎ መግለጡ ምነኛ ግሩም ነው ። ፊታችን ከተደገነው ተራራ ይልቅ ሰማይንና ምድርን የፈጠረውን አምላክ እግዚአብሔር ማየትስ ምነኛ መታደል ነው ። ✍️ጌታሁን አያኖ
| 2 | #EvaSUE|ኢቫሱ
#Graduation #2026
#Congratulations | 3 822 |
| 3 | #EvaSUE|ኢቫሱ
#Graduation #2026
#Congratulations | 3 657 |
| 4 | #EvaSUE|ኢቫሱ
#Graduation #2026
#Congratulations | 2 786 |
| 5 | #EvaSUE|ኢቫሱ
#Graduation #2026
#Congratulations | 2 572 |
| 6 | #EvaSUE|ኢቫሱ
#Graduation #2026
#Congratulations | 2 332 |
| 7 | #EvaSUE|ኢቫሱ
#Graduation #2026
#Congratulations | 2 480 |
| 8 | #EvaSUE|ኢቫሱ
#Graduation #2026
#Congratulations | 2 387 |
| 9 | #EvaSUE|ኢቫሱ
#Graduation #2026
#Congratulations | 2 858 |
| 10 | እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ ! አንተ የርስቴ ድርሻዬ ነህ ። ካንተ የምሻው ሌላ ድርሻ የለም ። ለሌዊ ድርሻው አንተ እንደሆንኸው ፤ ለኔም ድርሻዬ አንተ ነህ ። የማታልፍ ዘላለማዊ ፤ የማትጠፋ ሕያው እና አርጅተህ ማትታደስ ሕያው ርስቴ ፤ ምስጋና ላንተ ይኹን ። የተወለድኹብህ ፣ የኖርኹብህ እና የምኖርብህ የዘላለም ቤቴ ሆይ ተገኔ ነህና አልናወጽም ። አቤቱ አንተ የርስት ድርሻዬ ብቻ ሳትሆን ጽዋዬም ነህ ።
እረኛዬ ነህና ፣ መጋቢዬም ጠባቂዬም እልሃለሁ ። አኗሪዬም ነህና ፣ ዕጣዬ እንኳን ካንተ የተሰወረ ዐይደለም ። ለኔ እጅግ ሩቅ ቢሆንብኝ ፣ ስለራሴ ዕጣ እንኳን የማወቅ ብቃቱ ባይኖረኝ "ነገ ምን እኾን ?"ብዬ ማልሰጋው ዕጣዬ በእጅህ ስለሆነች ነው ። ሁሉዬ ነኽና ፣ ልቤ ያለስጋት ዘላለም ባንተ ያርፋል ። ባንተ እንድኖር ፤ ለራስህ ክብር ሠራኸኝ ። ከአእምሮ በላይ ስለሆነው ማንነትህ ፤ ከልቤ እስከ አርያም ፣ ከዛሬ እስከ ዘላለም ክብር ይሁንልህ !!
✍️ጌታሁን አያኖ | 8 345 |
| 11 | ድካሜን አውቃለሁ ። በጥቂት ነገር ልቤ በፍረኃት ተሸብቦ ሲንገላወድ የምኖር ልልዘሊል ነኝ ። ብርታቴ ሆይ ያላንተ እግሮቼ ጸንተው መቆም ይሳናቸዋል ። የቆምኹ እየመሰለኝ ልወድቅ ምንተፋተፍ ተሰባሪ ነኝና ብርታቴ ሆይ አንተን ተስፋ አደርጋለሁ ። በምኞት ማዕበል ዐይኖቼ ሲናጡ ፣ ልቡናዬም ክፋትን ሲያወጠንጥን ፣ እጆቼ ለነውር ሲዘረጉ ፣ መላአካሌ መሪ እንደሌለው መርከብ እማያውቅበት አገር ሲነጉድ መመለሻ መንገዴ አንተው ነህና ፤ በዚህ ኹሉ አንተን እጠብቃለሁ ። " ሰው እንዴት በዚህ ይወድቃል? "ብዬ ባልኹት ጉዳይ ራሴን አገኛለሁና አቤቱ እጆቼን ይዘኽ ትመራኝ ዘንድ ረድኤትህን እሻለሁ ።
ምትታመን ታማኝ ወዳጅ አምላኬ እግዚአብሔር ሆይ ካንተ በቀር በጎነት የለኝም ። ትናንትና ዛሬም እስከዘላለም ያው ኾነህ በምትኖር ባንተ እንጂ ዛሬ ባለኝ አቋም ፣ ትላንት ባሳለፍኹት ትጋት ታምኜ ነገን ተስፋ አላደርግም ። ባሳልፍኸው ትናንት ፣ ባሳየኸኝ ዛሬ ፣ በእጅህ ባለው ነገ አለመናወጽ ጸንተህ የምትኖር አንተ ነህና ጉልበቴ ሆይ አንተን እጠበቃለሁ ።
ብርታቴ ሆይ ፤ አምላኬም ነህና አንተን እጠብቃለሁ ። በእጆችህ አበጃጅተህ ያቆምከኝ ያንተው ፍጥረት ነኝና ሠሪዬም ነህ ። በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ የመስቀል ላይ ጣር ልጅህ አድርገህ የተቀበልኸኝ አባቴም ነህና ፤ ምስጋና ላንተ ይሁን ። ተጠግቼ "እፎዬ "ምለው ። እውነተኛውን ርጋታም ማገኘው ፤ ባንተው ነውና መጠጊያዬ ሆይ ክብር እና ውዳሴ ላንተ ይሁን!! ለዘላለሙ አሜን! | 10 211 |
| 12 | https://telegra.ph/%E1%8A%A0%E1%8B%B3%E1%8A%9D-%E1%8A%A8%E1%8C%BD%E1%8B%AE%E1%8A%95-05-29 | 7 879 |
| 13 | https://www.youtube.com/watch?v=OKi8379ru_k&t=541s&pp=ygUSIDUga2lsbyBmZWxsb3dzaGlw | 7 377 |
| 14 | በራልን
እግዜሩ ጋር ንክኪ ያለው ሰው አቤት መታደሉ። ከክንፉ ጥላ ስር ተሸሽጎ በጥበቃው ልቡ አርፎ ይኖራል። ከመረጃ ባለፈ በተጨባጭ ሁኔታ በሒወቱ እውን ለሆነለት አምላክ ፈቃዱን አስገዝቶ ይኖራል። እግዚአብሔር ራሱን ካልገለጠልን በስተቀር በራሳችን ጥረት ልንደርስበት አንችልም ፤ በሰው ቀመር እና ስሌት አይገኝም ፤ በሰው የአዕምሮ ልህቀት ታስሶ አይደረስበትም። ታዲያ ይህ ረቂቅ እና ምጡቅ አምላክ ራሱን ለሰው ልጆች መግለጥ በጎ ፈቃዱ ሆኖ በልጁ በክርስቶስ በኩል መልኩን፣ ባህሪውን እና ማንነቱን አሳየን። እግዚአብሔር ተገለጠልን በራልን። እርሱን ማወቅ የዘላለም ህይወት ነው። ከእርሱ ጋር ተጣብቆ መኖር የህይወት ትርጉም ነው። ከእርሱ ጋር መወዳጀት የእረፍት አለም ነው። እርሱን ማመን ልብን የሚያረጋ መልህቅ ነው። ታዲያ እግዜሩን ከመረጃ ባለፈ በህይወታችን እውን ይሆንልን ዘንድ ይበራልን ዘንድ የግድ ያስፈልጋል። እንዲበራልን ይበልጡን እንድናውቀው እና እንድንረዳው ደግሞ ወደእርሱ ቀርበን ልንለምነው በፀሎት እንማፀነው ዘንድ ይገባል፤ እንዲሁ በአዕምሮ የምናውቃቸውን የእግዚአብሔር ቃል እውነቶች መተግበር ይገባናል ። ከትላንቱ ዛሬ ፤ ከዛሬ ደግሞ ነገ እግዚአብሔርን በማወቅ ህይወት እንዲሁም በእውነተኛ መረዳት እና ግንዛቤ እያወቅነው እንኖር ዘንድ ፀጋ ይብዛልን
✍️ ካሌብ ካሳሁን | 10 136 |
| 15 | ቃል ጸሎት
እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ፤
በክንፎችህም ጥላ ሰውረኝ፤
መዝሙር 17፥8
አቤቱ ጠብቀኝ ! ትድግናህ የሚያሻኝ ድኩም ፣ ጠብቆትህ የሚያስፈልገኝ ፣ ለአውሬ ለሌባ ተጋላጫ የሆንኹ በግ ፣ ከለላህ የሚያኖረኝ ልል ፣ ማዳናህ ሚፈውሰኝ ሕማም ፣ እጅህ የሚመራኝ ተጓዝ ፣ ቃልህ የሚያጸናኝ ወላዋይ ነኝና እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ ።
የዐይንን ብሌን ከራስ በታች ከሌላው የሰውነት ክፍል ሁሉ ከፍ አድርገህ ፥ በማበጀት ከብዙ ጥፋት እንዲጠበቅ እንዳደረግህ ፤ ከዚህ ዓለም ክፋት እና ነውር በላይ በጽድቅህ ከፍታ እግሮቼን እንድታጸና እማጸንሃለሁ ። የዐይንን ብሌን በተከለለ ሥፍራ እንዳኖርከው አቤቱ ባርያህንም በእቅፍህ እንድታኖረኝ አሻለሁ ።
ንስር ጫጩቶቿን በክንፎቿ ሰውራ ከውጩ ብርድ ሙቀትን እንደምትቸር ፣ ከፀሓዩም ከልላ ጥላ እንድምትሆነው ፣ ከዝናብ ከውርጭ ሸሽጋ በጉያዋ እንደምታሳርፍ አቤቱ ልጅህ ነኝና ከዚህ ዓለም ዐመጽ እና ነውር እንዲሁም ክፋት ሁሉ በክንፎችህ ሰውረኝ ።
አምላክ ሆይ፤ ስለምትመልስልኝ ስምህን በመጥራት ልመናዬን አቅርቤያለሁና ስማኝ ። በእረኝነትህ እስከፍጻሜው አኑረኝ ፣ ለዘላለሙ አሜን !!
✍️ጌታሁን አያኖ | 9 254 |
| 16 | https://youtu.be/6osUqOArVtM?si=KRyvaXsRuVikR2tN | 4 802 |
| 17 | በመታመን
በየዕለት ህይወታችን ላይ እምነት (መታመን) የሚባለው ነገር የዘወትር ተግባራችንን የያዘ ነው። ለምሳሌ የተቀመጥንበት ወንበር እንደማይጥለን ስለምናምን ያለሀሳብ ዘና ብለን እንቀመጥበታለን። እግዚአብሔር በማንነቱ ታማኝ ስለሆነ በሙሉ ልባችን በእርሱ ላይ እንድንታመን ይፈልጋል። እግዚአብሔርን አምነዋለሁ( መታመኛየ ነው) ማለት ሒወቴን እንድመራበት የሰጠኝ መመሪያ በሰው አይን የሚያዋጣ ባይመስልም ነገር ግን እሱ ለእኔ መልካም የሆነውን ስለሚያስብ ያንን ጎዳና ልጓዝበት ወስኛለሁ ማለት ነው። እግዚአብሔር የመረጠልኝን መንገድ በመከተሌ እንደከሰርኩ ያህል እንዲሰማኝ የሚያደርጉ ድምፆች በዙሪያየ ቢያንባርቁም መንገዱን መጓዝ ግን እቀጥላለሁ ማለት ነው። እሱን በመጠበቄ ጊዜየ እንዳረፈደብኝ ቢሰማኝም በራሴ አካሄድ ቅልጥፍጥፍ ብል ከማገኘው እስማኤል በላይ ጊዜው ያለፈ በሚመስል ወቅት የሚሰጠኝን ይስሀቅን እጠብቃለሁ ማለት ነው። በእግዚአብሔር እታመናለሁ ማለት በራሴ ማስተዋል አልደገፍም ፤ ያገኘሁትን መልካም የሚመስል አጋጣሚ በጠቅላላ ፈቃዱን ሳላረጋግጥ አልጠቀምም ማለት ነው ። ለእግዜሩ ወገንተኛ ሆኜ ከማጣቸው እድሎች በላይ እሱ በራሱ ጊዜ የእሱ ፈቃድ ያለበትን በር ይከፍትልኛል ማለት ነው ባይከፍትልኝም እንኳ እሱ የታመነ አምላክ ነው ብሎ ልብን በእግዚአብሔር ሀሳብ ማፅናት ነው። ቢታመኑት የሚያስታምን ፤ አደራ የማይበላ ፤ ባለመታመን ተከሶ የማያውቅ የፀና ታማኝ አምላክ የሚያደላድል አለት ኢየሱስ ክርስቶስ አለ። ይሄ ጌታ ለላቀው ለዘላለም ሒወት በመስቀል ላይ እስከመሞት የታመነልን አምላክ ነውና ለምድሩ አይጠረጠርም። ለሰማይ ወፎች የሚያስብ ጌታ ለልጆቹማ እንዴት የበለጠ አያስብም?
ልባችን በእርሱ እንዲታመንልን ጌታ ፀጋውን ያብዛልን
✍️ ካሌብ ካሳሁን | 8 843 |
| 18 | https://youtu.be/3HRV2LeNLho?si=YEVdO9hChvlU-5_w | 5 529 |
| 19 | https://telegra.ph/%E1%89%83%E1%88%8D-%E1%89%85%E1%88%9D%E1%88%BB-04-29 | 7 805 |
| 20 | ዘፍጥረት መግቢያ ዘለለው አርጋው
https://youtu.be/jKXOQcQVFlc | 6 784 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
