cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Tikivia Official channel

Tikivia Official channel

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
2 547
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Repost from ETHIO-MEREJA®
አሸባሪው ሕወሓት ዳግም የከፈተውን ጦርነት የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ ነው!! ሰልፉ “በአገር ሕልውናና አንድነት አንደራደርም!” በሚል መሪ ሀሳብ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ፊት ለፊት እየተከናወነ ይገኛል። ሰልፉ አሸባሪው ሕወሓት ዳግም የከፈተውን ጦርነት ለማውገዝና የአገርን ሕልውና ለማስጠበቅ እየተሳተፉ ላሉ የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የጸጥታ ኃይሎችና ዜጎች ድጋፍና አጋርነትን የመግለጽ አላማ እንዳለው የሰላምና አንድነት ለኢትዮጵያ ዲሲ ግብረ ኃይል ገልጿል። የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያና ኤርትራ ላይ ያለውን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ በመከባበርና በሁለትዮሽ የጋራ ጥቅም ላይ ያተኮረ እንዲሆን የሚያሳስቡ መልዕክቶች በሰልፈኞቹ ተላልፈዋል። በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ትውልደ-ኢትዮጵያውያንና ሌሎች የኢትዮጵያ ወዳጆች መሳተፋቸውን ኢዜአ ዘግቧል። የሰላምና አንድነት ለኢትዮጵያ ግብረ ኃይል ሰልፉን ከአገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ጋር በትብብር እንዳዘጋጀውም ተገልጿል።
نمایش همه...
Repost from ETHIO-MEREJA®
በመከላከያ ሠራዊቱ የደረሰብን ምት መቋቋም አልቻልንም - ምርኮኞች "በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የደረሰብን ምት ፈፅሞ የምንቋቋመው አልሆነም ሲሉ በሰቆጣ ግምባር እጃቸውን የሠጡ የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂዎች ገለጹ፡፡ ምርኮኞቹ አያይዘውም ብዙዎች ከአጠገባችን ተደምስሰውብናል፣ አመራሮቻችንም ሞተዋል የተረፉትም ሸሽተዋል በማለት ተናግረዋል፡፡ ጉዕዲ ገ/ኪዳን በሠቆጣ ግምባር እጃቸውን ለመከለከያ ሠራዊት ከሰጡ የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂዎች መካከል አንዷ ስትሆን አማራን መደምሰስ አለብን የሚል ተልዕኮ እንደተሰጣቸውም ተናግራለች። በትግራይ ክልል ውስጥ ከፍተኛ አፈና እና የመብት ጥሰት በአሸባሪ ቡድኑ ታጣቂዎች እየተደረገ መሆኑን የገለጸችው ጉዕዲ ምንም እንኳን የጦርነት ፍላጎት ባይኖራትም በቤተሰቦቿ ላይ የሚደርሰውን ወከባ እና እንግልት ላለማየት አሸባሪውን ቡድን መቀላቀሏን ገልፃለች። ሌላኛው ምርኮኛ ኤልያስ ገብረፃዲቅ የሦስት ወንድ እና የአንድ ሴት ልጅ አባት ሲሆን ከሚሰራበት ቦታ በሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች ተገዶ ወደ ማሰልጠኛ እንደተወሰደ መናገሩን የመከላከያ ሰራዊት መረጃ አመልክቷል።     T.me/ethio_mereja        @ethio_mereja
نمایش همه...
Repost from ETHIO-MEREJA®
"ዓለም ጸንታ የቆመችው ለሌሎች በሚደረግ መልካም ነገር ነው። ገንዘባችንን፣ ዕውቀታችንንና ጉልበታችንን እጅግ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ከማዋል በላይ ሀገርን የመውደድ መገለጫ የለም። ከለውጡ ወዲህ ከተከተልናቸው መርሖች አንዱ በማኅበራዊ ኃላፊነት ማኅበራዊ ችግሮችን መፍታት ነው። ማዕድ ማጋራት፣ የድኾችን ቤት መሥራት፣ ትምህርት ቤቶችንና የጤና ተቋማትን መገንባት፣ የችግረኛ ገበሬዎችን እርሻ ማረስ፣ አካባቢን አረንጓዴ ማድረግ፣ ባህል እንዲሆኑ ሠርተናል። ሚልዮኖችም የዚህ ተሳታፊ ሆነዋል። ከሕጻናት እስከ አረጋውያን ባህላቸው አድርገውታል። በዚህ ዓመት በተደረጉት እነዚህ ማኅበራዊ አገልግሎቶች የተሳተፋችሁትን ሁሉ በራሴና በመንግሥት ስም አመሰግናችኋለሁ። አገልግሎቱን ያገኙት ወገኖች እንደሚመርቁንና እንደሚጸልዩለን አምናለሁ። ኢትዮጵያችን በእነዚህ ወገኖች ምርቃትና ጸሎት ፈተናዎቿን አሸንፋ እንደምትጓዝ ርግጠኛ ነኝ።" ዶ/ር አብይ አህመድ ፣ የኢፌድሪ ጠ/ሚንስትር     T.me/ethio_mereja        @ethio_mereja
نمایش همه...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#UpdateAU #ETHIOPIA የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት ፤ የትግራይ ክልል መንግስት ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ያለውን ቁርጠኝነት እንዲሁም በአፍሪካ ህብረት መሪነት በሚካሄደው የሰላም ሂደት ውስጥ ለመሳተፍ ፍቃደኝነቱን መግለፁን በደስታ እንደሚቀበሉት ገልፀዋል። ይህን የገለፁት የትግራይ ክልልን እያስተዳደረ ያለው ህወሓት በአፍሪካ ህብረት መሪነት ከፌዴራል መንግስት ጋር እደራደራለሁ ካለ በኃላ ባወጡት መግለጫ ነው። ሊቀመንበሩ ይህ አዎንታዊ የሆነ እድገት በኢትዮጵያ ውስጥ ሰላምን ወደነበረበት ለመመለስ ልዩ አጋጣሚ ነው ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል። የትግራይ ክልል መንግስት ለድርድር ዝግጁ መሆኑን በመግለፁም ሊቀመንበሩ አመስግነዋል። ከዚህ ባለፈ ሁለቱም ወገኖች (የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት እና የትግራይ ክልል መንግስት) በአስቸኳይ የተኩስ አቁም ለማድረግ እንዲሰሩ እና የፊት ለፊት ንግግር እንዲያደርጉ አሳስበዋል። ሊቀመንበሩ በአፍሪካ ህብረት በሚመራው የሰላም ሂደት ላይ ሁለቱም ወገኖች የሚስማሙባቸው ዓለም አቀፍ አጋሮች እንደሚካተቱ ጠቁመዋል። ሙሳ ፋኪ መሀመት በመግለጫቸው ላይ በዚህ ወሳኝ ወቅት የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በአፍሪካ ኅብረት ለሚመራው የሰላም ሂደት ድጋፉን እንዲያጠናክር ጠይቀዋል። @tikvahethiopia
نمایش همه...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#USA #ETHIOPIA " አሜሪካ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ትቆማለች ፤ የአፍሪካ ህብረትን (AU) ዲፕሎማሲያዊ ጥረትን ትደግፋለች " - አንቶኒ ብሊንከን የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ሀገራቸው አሜሪካ #ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር እንደምትቆም እና በአፍሪካ ህብረት እየተመራ ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት #እንደምትደግፍ ገልፀዋል። ይህን የገለፁት ለሊት ባወጡት መግለጫ ነው። ብሊንከን ፤ የአፍሪካ ህብረት እየተካሄደ ላለው ግጭት ሰላማዊ መፍትሄ ለማበጀት የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት (TPLF) በተቻለ ፍጥነት ወደ ውይይት እንዲመጡ ለማድረግ እየሰራ ላለው ስራ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ለሰላም ሲባል ከህወሓት ጋር " በየትኛውም ስፍራ፣ በማንኛውም ጊዜ "  ለመነጋገር ዝግጁ መሆኑን እንደገለፀ ያስታወሱት ብሊንከን ለዚህ የመንግስት ዝግጁነት የሚሰጥ ምላሽን እናበረታታለን ብለዋል። ህወሓት (TPLF) ግጭት ለማቆም እና ችግሮችን በውይይት ለመፍታት ያወጣውን መግለጫ እናበረታታለን ሲሉም አክለዋል። ዓለም አቀፍ አጋሮች የሰላም ሂደቱን ለማገዝ ዝግጁ ናቸውም ብለዋል። ኤርትራ እና ሌሎችም ግጭቱን ማቀጣጠል ማቆም አለባቸውም ሲሉ ገልፀዋል። አሜሪካ የኢትዮጵያን #አንድነት፣ #ሉዓላዊነት እና #የግዛት_አንድነት እንደምትደግፍ የገለፁት አንቶኒ ብሊንከን አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር ወደ #ጠንካራ_አጋርነት መመለስ ትፈልጋለች ሲሉ ገልፀዋል። " የአዲስ ዓመት መንፈስን ታሳቢ በማድረግ የአገሪቱ መሪዎች አገሪቱ መከራዋ ወደሚያበቃበት እና ዘላቂ ሰላም ሊያስገኝ ወደሚያስችል መንገድ እንደሚሯት ጥሪ እናቀርባለን " ብለዋል። @tikvahethiopia
نمایش همه...
🔴 የጁምዐ መልዕክት የኢስላም ሊቃውንቶች በጁምዓ ቀን ዱዓ ተቀባይነት የሚገኝበት ሰአት ላይ የተወዛገቡ ሲሆን፤ -የመጀመሪያዎቹ የጁምዓ ቀን የመጨረሻዋ ሰዐት ናት ሲሉ፣ -ሁለተኞቹ ኹጥባ አድራጊው ሚንበር ላይ ከወጣበት ሰዐት አንስቶ እስከሚወርድበት ነው በማለት ይናገራሉ። ስለዚህ የትኛውም ሙስሊም ከውዝግቡ ለመውጣትና ሰዐቷን ለማግኘት እንዲያደርገው የሚመከረው በእነዚህ ሁለቱ ሰአታት ዱአ ማብዛትና እንደ አጠቃላይም በጁምዓ የቀን ክፍለ ጊዜ ላይ በዱዓ እንዲበራታ ነው። ወላሁ አዕለም
نمایش همه...
Repost from Mujib Amino Z islam
“የተለያየ አመለካከት ሲኖር የሀሳብ ጥራት እንዲገኝ ያስችላል” - የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ የተለያየ አመለካከት ሲኖር የሀሳብ ጥራት እንዲገኝ ያስችላል፤ አካታችነት የሚያስፈልገውም ለዚሁ ነው ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ተናገሩ። የሀሳብ ብዝሀነት እና በሀገር ግንባታ ላይ አብሮ መሥራት ዴሞክራሲያዊ ጠቀሜታው ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው በጋራ የሀገርን ሀብት ለማልማት ያስችላልም ብለዋል። ፈተና፣ ድል፣ ተስፋ የተሰኘው የ2014 ዐበይት የመንግሥት ክዋኔዎች የሚዳስስ የአዲስ ወግ የውይይት መርሐ-ግብር በመካሄድ ላይ ይገኛል። የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ የሆኑት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን፣ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ የሚያስችሉ የሰላምና ደህንነት ስራዎች ላይ ትኩረት መደረጉን አንስተዋል። ከተሠሩ የለውጥ እርምጃዎች የተነሳም የጸጥታ ተቋማት የሀገራችንን ሰላም ለማስከበርና የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ በሚያስችል አቋም ላይ ይገኛሉ ብለዋል። በሰው ሠራሽ እና ተፈጥሯዊ ተግዳሮቶች መካከል ኢኮኖሚያችን ዕድገት አሳይቷል፤ ከውጪ ምንዛሬ፣ ከማክሮ ኢኮኖሚ አመለካከቶች፣ ከገቢ፣ የብድር አቅርቦት እና አመላለስ፣ ከሥራ ዕድል መመቻቸት አኳያ ጥሩ አፈጻጸም ተመዝግቧል ያሉት ደግሞ የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ዶ/ር ፍጹም አሰፋ ናቸው። ግብርና፣ አረንጓዴ ዐሻራ፣ አምራች ኢንዱስትሪ፣ ዲጂታል ኢኮኖሚ ተጨባጭ ዕድገት ከታየባቸው መካከል መሆናቸውን መጥቀሳቸውን የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት መረጃ ያመለክታል። ▬▬▬▬▬▬▬▬▬ የቴሌግራም ቻናል-https://t.me/MujibbinISLAM
نمایش همه...
Repost from DW Amharic
https://p.dw.com/p/4GRZY?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
نمایش همه...
የነሐሴ 30 ቀን፣ 2014 ዓ.ም የስፖርት ዘገባ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለአልጄሪያው የቻን የአፍሪቃ ዋንጫ ማለፉን አረጋግጧል። ብሔራዊ ቡድናችን በቻን የአፍሪቃ ዋንጫ ሊኖረው የሚችለው የፉክክር ሚዛን ምን ይመስላል? ቃለ መጠይቅ አድርገናል። እጅግ አጓጊ እየሆነ በመጣው የእንግሊዝ ፕሬሚየር ሊግ በአሸናፊነት ሲገሰግስ የነበረው አርሰናል በማንቸስተር ዩናይትድ ብርቱ ሽንፈት ገጥሞታል።

Repost from Fana Tv/Fbc ™
አዲአርቃይ ላይ በወገን ጦር የተሰበሩ የዋሻ ምሽጎች!! ጠላት አንድ ዓመት ከሁለት ወር በላይ ተቆጣጥሮት የነበረውን አዲአርቃይ ከተማ የመከላከያ ሰራዊት እና ጥምር ጦሩ በትናንትናው ምሽት ነፃ ወጣለች። በአሁን ወቅት መከላከያ ሰራዊት ወደ ማይፀብሪ እየተጠጋ መሆኑ ታውቋል።   
نمایش همه...
ለቸኮለ ማለዳ! ማክሰኞ ጳጉሜ 1/2014 ዓ.ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች 1፤ ኢሰመጉ በሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት ተሳታፊ የሆኑ አካላት ወደ ሰላማዊ ንግግር እንዲመለሱ ትናንት ባወጣው መግለጫ ጥሪ አድርጓል። ኢሰመጉ ትግራይ ክልልን በሚያዋስኑ የአማራ እና አፋር ክልሎች አንዳንድ አካባቢዎች በቀጠለው ጦርነት ሳቢያ ሴቶች፣ ሕጻናት እና አረጋዊያንን ጨምሮ በርካታ ሰላማዊ ነዋሪዎች ከቀያቸው እየተፈናቀሉና ለስቃይ እየተዳረጉ መሆኑን ገልጧል። ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ አዲስ ባገረሸው ግጭት ለጉዳት ለተዳረጉ ሰዎች ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲያ ደርግ ኢሰመጉ ጠይቋል። 2፤ የሱዳን መንግሥት የውጭ ረድዔት ድርጅቶች በኢትዮጵያ አዋሳኝ ከሚገኘው ሐምዳይት የኢትዮጵያዊያን ስደተኞች መቀበያ ጣቢያ እንዲወጡ ማዘዙን ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል። መንግሥት ትዕዛዙን ያስተላለፈው፣ በድንበር አቅራቢያ "በኢትዮጵያ መንግሥትና በሕወሃት ኃይሎች መካከል የሚደረገው ውጊያ መባባሱን" ተከትሎ እንደሆነ ዘገባው አመልክቷል። ሱዳን ተጨማሪ ጦር ወደ ድንበር ማስጠጋቷንም ዘገባው ወታደራዊ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል። በሐምዳይት የስደተኞች መቀበያ ጣቢያ ከሚሰሩት ዓለማቀፍ የዕርዳታ ድርጅቶች መካከል፣ ድንበር የለሹ የሐኪሞች ቡድንና የተመድ ስደተኞች ኮሚሽን ይገኙበታል። 3፤ የሱዳን ወታደራዊ መንግሥት ሲቪሉ የሽግግር መንግሥት ቀደም ሲል አፍርሷቸው የነበሩ 22 መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንደገና እንዲንቀሳቀሱ መፍቀዱን የሱዳን ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የሽግግር መንግሥቱ መንግሥታዊ ያልሆኑትን ድርጅቶች ያፈረሰው፣ ከቀድሞው የፕሬዝዳንት ሐሰን አልበሽር አገዛዝ ጋር ትስስር እንዳላቸው በመግለጽ ነበር። ሆኖም የኅዳሩን ወታደራዊ የመንግሥት ግልበጣ ተከትሎ፣ ወታደራዊው መንግሥት የቀድሞውን ሥርዓት ተቋማት ለማፍረስ የተቋቋመውን ኮሚቴ በመበተን የኮሚቴውን ውሳኔዎች መቀልበስ እንደጀመረ ሲዘገብ ቆይቷል። 4፤ የኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ከተመራጩ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋር ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር እንደሚያደርጉ ትናንት በቴሌቪዥን በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል። ሆኖም ፕሬዝዳንቱ ምክትላቸው ዊሊያም ሩቶ ምርጫውን በማሸነፋቸው እና ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የምርጫ ውጤታቸውን ማጽደቁን አስመልክተው የደስታ መግለጫ ሳያስተላልፉላቸው ቀርተዋል። ኬንያዊያን የአገሪቱን ተቋማት እንዲያከብሩ የጠየቁት ኬንያታ፣ ኬንያዊያን በምርጫውና በፍርድ ቤቱ ሂደት ወቅት የአገሪቱን ሰላም በመጠበቃቸው አድናቆታቸውን ገልጸዋል። 5፤ የዓለም ዓቀፍ ነዳጅ ዋጋ በሦስት በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን ዓለማቀፍ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የዓለም ነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ያሳየው፣ የነዳጅ አምራች እና ሻጭ አገሮች ድርጅት አባል አገራት በቀን ከሚያመርቱት ነዳጅ ላይ 100 ሺህ በርሜል ነዳጅ ለመቀነስ መወሰናቸውን ተከትሎ ነው። በውሳኔው መሠረት የአንድ በርሜል ነዳጅ ዋጋ ወደ 95.74 ዶላር አሻቅቧል። [ዋዜማ ራዲዮ]
نمایش همه...