cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Ahmedin Jebel - አሕመዲን ጀበል

ይህ ይፋዊ የአሕመዲን ጀበል የቴሌግራም ገፅ ነው!

نمایش بیشتر
Advertising posts
60 252مشترکین
-1524 ساعت
+1397 روز
+3 77530 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

የሐጅ ምዝገባ በዛሬውእለት በድጋሚ እንደሚጀምር መጅሊስ አስታወቀ 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ) ተቋርጦ የነበረው የሐጅ ሥነ ሥርዐት ምዝገባ ከዛሬ ቅዳሜ ሚያዝያ 12/2016 ጀምሮ በድጋሚ ይካሄዳል ሲል ያስታወቀው ዛሬ ነው። ምክር ቤቱ ተመዝጋቢዎች ሁጃጆች ለምዝገባ ሲመጡ የታደሰ ፓስፖርት፣ መታወቂያና ጉርድ ፎቶ ግራፍ ይዘው እንዲመጡ አሳስቧል። መጅሊስ ፓስፖርት የሌላቸውና እድሚያቸው ከ50 በታች የሆነ ተመዝጋቢዎች የልደት ሰርተፊኬት እንዲያቀርቡ የጠየቀ ሲሆን፣ እድሜያቸው ከ50 ዓመት በላይ ለሆናቸው ደግሞ መታወቂያና ጉርድ ፎቶ ግራፍ ብቻ ይዛችሁ መገኘት አለባቸው ብሏል። ጥቂት ተመዝጋቢዎችን እንደሚቀበል ያስታወቀው ምክር ቤቱ፣ ከነገ ጀምሮ የሐጅ ምዝገባ እንደሚቀጥል ቢያሳውቅም የሚጠናቀቅበትን ቀን አልገለፀም።
نمایش همه...
42👍 22
ም ቅዳሜ በ 3 ሰዓት ከመስጂደል አንዋር ይጀምራል። ኢትዮጵያዉያን እስላሞች! (የኢትዮጵያ የጥናትና ምርምር ተቋም፣ ማኑስክሪፕት ክፍል፣ ማኅደር ቁጥር 2396/02/5) ይህ ሁሉ ሲሆን የመንግሥት የደህንነት አካላት ሰልፉን ለማሰናከል አስተባባሪዎችን፣ በተለይም ወጣቱን ክፍል ያሳድዱ ነበር። ከወጣቱ መካከልም በዋናነት በእነ ዶ/ር አሕመድ ቀሎ እና ጉልህ ሚና ባላቸው ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ በተጋጋሚ ይፈጸም ነበር። ሰፈር በመቀያየር፣ ራሳቸውን በመለዋወጥ እና ከደህንነት ለሚደርስባቸው ዛቻና ማስፈራሪያ ‹‹የፈለጉትን ያምጡ›› ሲሉ ራሳቸውን አሳምነው በተግባራቸው ገፉበት። ስለ ሰልፍ የሰማ ሙስሊም ሁሉ ‹‹አንዳች ይነገር ይሆን?›› እያለ አንዋር መስጂድን ማዘወተሩን ቀጠለ። ሰልፉ ፈቃድ ባይኖረውም ‹‹የመጣው ይምጣ›› በሚል ሁሉም ተረባረበ። አቶ ዐብዱ አደም የተባሉ የዩኒቨርሲቲ ምሩቅ ባለሐብት ወደ ሰልፉ አቀናባሪ ዶ/ር አሕመድ ቀሎ በመምጣት የሰልፉን ሙሉ ወጪ ለመሸፈን እንደሚፈልጉ እንዲህ ሲሉ ገለጹ፡- ‹‹አሕመድ! እኔ ሕዝቡ ጋር ሄደህ ገንዘብ እንድትሰበስብ አልፈልግም። አትቸገር፤ እኔ አለሁ! ለሰልፉ የሚያስፈልገውን የፈለግከውን ያህል ገንዘብ ይኸው ባዶ ቼክ። ከባንክ አውጥታችሁ ተጠቀሙበት። እኔ በምን አወጣኸው ብዬ አልጠይቅህም። እኔ አለሁ! የፈለጋችሁትን ገንዘብ ተጠቀሙበት! ይህ በእኔና ባንተ መሐል ይሁን።››(ከዶ/ር አሕመድ ቀሎ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ) አቶ ዐብዱ አደም እንዳሉትም የሰልፉን ሙሉ ወጪ ሸፈኑ። ገንዘባቸውንም ለሙስሊሙ መብት መከበር ትግል አዋሉ! ይቀጥላል……….
نمایش همه...
35👍 25
የዛሬ 50 አመት በዛሬው እለት ነበር ይህ ክስተት የተፈፀመው 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 ‹‹አትነሳም ወይ አትነሳም ወይ! ይህ ጥያቄ ያንተ አይደለም ወይ?" ክፍል 3 📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌 ጥያቄዎቹ ለመንግሥት ከቀረቡ በኋላ ምላሹን ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ለማሳወቅ በአባድር ኢንስቲትዩት (ት/ቤት) ሰብሰባ ተጠርቷል። በአንድ የመማሪያ ክፍል ውስጥ ከሐምሳ ያልበለጡ ሙስሊም ግለሰቦች ተቀምጠዋል። ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የተሰጠውን ምላሽ ተወካዮቹ አብራሩ። ተወካዮቹ ሐጂ ሙሐመድ ሳኒ ሐቢብ፣ ዶ/ር አሕመድ ቀሎ፣ አሕመድ ሰዒድ ዐሊ፣ጧሃ፣ ዐብዱልዋሲዕ መንዲዳ፣ ዐብዱ አደም፣ወዘተ…፤ ሪፖርት ሲያቀርቡ ሁሉም በጥሞና ያደምጣል። የምላሹ ድምዳሜ ‹‹ጉዳያችሁ ይታይላችኋል ጠብቁ›› የሚል ነበር። በሥፍራው ከተገኙት መካከል ወጣቶቹ ምላሹ እጅግ አበሳጫቸው። ይበልጥ ደግሞ የአንዳንድ ተወካዮች ‹‹ብንጠብቅ ይሻላል›› የሚለው አስተያየት አናደዳቸው፤ አዘኑ፤ ቁጭት ገባቸው። አንዳንዶቹ ‹‹አይሆንም! የሆነ ነገር መደረግ አለበት›› ሲሉ በምሬት ተናገሩ። ‹‹በጠቅላይ ሚኒስትሩ ‹ፋታ ስጡኝ! ጠብቁ!› ምላሽ ልንቀር ነው?›› በማለት አሳሰቡ። ከፊሎቹ ‹‹‹ችግራችሁ ይታይላችኋል፤ ጊዜ ስጡኝ!› መባሉ በራሱ አዎንታዊ ምላሽ ነውና እንጠብቅ›› ሲሉ አስተያየታቸውን ሰነዘሩ። በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉ የ30 ዓመቱ ወጣት አሕመድ ቀሎ (ዛሬ ዶ/ር ናቸው) እጅ አወጡ። እንዲናገሩ እድል ተሰጣቸው። እንዲህ ሲሉም ሀሳባቸውን ገለጹ፡- ‹‹እንዲህማ አይሆንም! ማንም ገዢ የሆነ ሰው ይህንኑ ነው የሚለው። የሙስሊሞችን ጉዳይ ቀላል አድርገን ‹ጊዜ ስጡኝ› ስላለ ጊዜ አንሰጠውም! እስካሁን ሲጨቁነን የቆየ መንግሥት አሁን አንድ ደብዳቤ ስለጻፍንለት ብቻ ለውጥ ይመጣል ብለን መጠበቅ የለብንም። ወደሚቀጥለው እርምጃ መሄድ አለብን፡፡›› (በ2001 ከዶ/ር አሕመድ ቀሎ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ - በደራሲው) ሞራላቸው ተነክቶ የነበሩት ወጣቶች ከምሁራኑ ዶ/ር አሕመድ ቀሎ ስለደገፏቸው ደስ አላቸው። ክፍሏን በጭብጨባ አሞቋት። ከዚያ በኋላ ‹‹እንጠብቅ›› በሚሉትና ‹‹ወደሚቀጥለው እርምጃ እንሂድ›› በሚሉት መካከል ጠንካራ ክርክር ተደረገ።ሆኖም ስብሰባው ያለስምምነት ተቋጨ። በማግስቱ በምሽት በዚያው ሥፍራ ‹‹ያስታርቁን›› በማለት እነፊታውራሪ አመዴ ለማና ሌሎች ተጨማሪ ግለሰቦችን ‹‹እንጠብቅ›› በሚሉት ወገን ጥሪ ተደርጎላቸው በሥፍራው ተገኙ። ሁለቱም ወገኖች ሐሳባቸውን አቀረቡ። ክርክሩ ጦፈ። ሽምጋዮቹ የሁለቱንም ወገኖች ሀሳብ አደመጡ። ፊት አውራሪ አመዴ ለማ የወጣቶችን ሐሳብ ደግፈው ‹‹ፈራ ፈራ እያሉ አብዮት አይካሄድም! መጠበቅ የለብንም!››› ሲሉ ተናገሩ። ወጣቶቹ በጭብጨባ ተቀበሏቸው። ልክ ከምሽቱ አምስት ሰዓት ገደማ ላይ ‹‹ጊዜ ይሰጠው፣ እንጠብቅ›› የሚለው ሐሳብ ውድቅ ሆነ። በአሜሪካን አገር ተምሮ የመጣው አሕመድ ቀሎ በዚያ በተማሪዎች እንቅስቃሴ ውስጥ ያገኘውን ልምድ ተጠቅሞ በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች እንቅስቃሴ ላይ በራሪ ወረቀት በመበተን ይሳተፍ የነበረው በሙስሊሙ እንቅስቃሴ የመሪነቱን ሥፍራ ያዘ። በሙስሊሙ እንቅስቃሴ ውስጥ ከዚያ በፊት ጉልህ ሚና ባይኖረውም ከተቀመጠበት በመነሳት ‹‹ከአሁን በኋላ እዚህ አባድር ኢንስቲትዩት የተዘጋ ቤት ውስጥ ሳይሆን የምንሰበሰበው በግልፅ መስጂድ መሆን አለበት። ነገ በአንዋር መስጂድ ስብሰባ ጠርተናል›› ሲል ተናገረ። በማግሥቱ ጠዋት ከ 500 እስከ 1000 ሙስሊሞች በአንዋር ቅጥር ግቢ ተገኙ። ከሐጂ ሙሐመድ ሳኒ ሐቢብ ቢሮ ፊት ለፊት ሙስሊሙ ሊያደምጥ ታደመ። የእስከ ዛሬው ሂደት ተብራራ። ሙስሊሙ በተክቢራ ግቢውን አቀለጠው። ለቀጣዩ ትግል ሀምሳ ተወካዮች ተመረጡ። ተወካዮቹም በተራቸው አመራራቸውን መረጡ። የዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎችን፣ ምሁራንን፣ መሻኢኾችን፣ ነጋዴዎችን እና ሌሎች ግለሰቦችን ያቀፈው ኮሚቴ ሥራውን ጀመረ። የኮሚቴው ውክልና እንዴት መስፋት እንደሚችል መምከር ያዙ። እንቅስቃሴያቸውን ሕዝባዊ መሠረት ማስያዝ እንዳለባቸውም ወሰኑ። በሐጂ ሙሐመድ ሳኒ ሐቢብ ቢሮ እየተገናኙ ውይይታቸውን ቀጠሉ። ‹‹መንግሥት ባይፈቅድም ሰልፍ መወጣት አለበት›› የሚል ሐሳብ ተነሳ። ‹‹ልታስጨርሱን ነው?›› ሲሉ የተደመጡም ነበሩ። ‹‹እንዴት ሙስሊሙን ማስወጣት ይቻላል? ከባድ እኮ ነው›› ወዘተ. የሚሉ ሐሳቦችም ተንሸራሸሩ። ሥጋት ለገባቸው ወገኖች ዶ/ር አሕመድ ቀሎ ‹‹መቶ ሺህ ሰው አስወጣለሁ!›› ሲሉ ገለጹ። የማይሆን ነው ከማለት በመነጨ ስሜት ‹‹መቶ ሰውም ከወጣ ትልቅ ነገር ነው›› ያሉም ነበሩ። ውይይቱ ጦፈ። ‹‹ሰልፍ ይወጣ›› የሚለው ሐሳብ ረታ። ውይይቱም ‹‹እንዴት ሰልፍ እናካሂድ?›› ወደሚለው ተሸጋገረ። ግና ‹‹እንዴት ያን ያህል ሕዝብ ማሰባሰብ ይቻላል?›› የሚለው ጥያቄ ፈታኝ ሆነ። የኮሚቴው አባላት፣ ምሁራኑ፣ ዑለማው፣ ነጋዴው፣ የመስጂድ ኮሚቴው… ሁሉም ያስባል። የመፍትሄው ሀሳብ ግን ጠብ አልል አለ። ግና ባልተጠበቀ ሁኔታ መላ ጠፍቶት የነበረውን ኮሚቴ ከጭንቀት የሚገላግል አንድ ግሩም ሐሳብ ቀረበ። ሐሳቡ የቀረበው ከምሁራኑ አልያም ከዓሊሞቹ አልነበረም፤ ከአንድ ተራ የቀን ሠራተኛ ሚስኪን ሙስሊም እንጂ። ግለሰቡ ‹‹አዲስ አበባ ውስጥ ያሉትን የእስላም እድሮች ዝርዝር ተዟዙረን እንለይ። ከዚያም የየእድሩን ሊቃነ መናብርት ስብሰባ ጠርተን እናወያያቸው። እነሱ ሕዝቡን ሁላ ሊጠሩልን ይችላሉ›› ሲል ሐሳቡን ገለጸ። ሁሉም የኮሚቴው አባላት በሐሳቡ ተደመሙ። ወዲያውኑ ስብሰባውን አቋርጠው የሙስሊሞችን ዕድር ለመመዝገብ በየአቅጣጫው ተበተኑ። ሀምሳ የሙስሊም እድሮችን ሥም ዝርዝር ይዘው ተመለሱ። ሊቃነ መናብርቱም ስብሰባ ተጠሩ። መጡም። ጉዳዩም ተብራራላቸው። ሐሳቡን ደገፉ። ሕዝቡንም ለመጥራት ቃል ገቡ። ከወጣቱ አካባቢ የመነጨው ሰልፍ የመውጣት ሐሳብ (አጀንዳ) የሁሉም ሆነ። የተቃወሙት ራሳቸው ይቅርታ ጠይቀው ከዝግጅቱ ተቀላቀሉ። ሰልፉን ለመጥራትና ለእንቅስቃሴው ሕዝባዊ መሠረት ለማስገኘት የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ማማከሩ ቀጠለ። ከሽማግሌዎቹ አካባቢ ‹‹በፍፁም ሴቶች ሰልፍ ላይ መሳተፍ የለባቸውም!›› የሚል ሐሳብ ቀረበ። ሐሳቡ አጨቃጨቀ። ወጣቶቹ ተሳክቶላቸው የአዛውንቶቹን ሐሳብ አስቀለበሱ። የሰልፉ የአወጣጥ ስትራቴጂ ተነደፈ። ሕዝቡም በቀኑ እንዲገኝ የሚገልጽ የሰልፍ ጥሪ ወረቀት ተበተነ። በወረቀቱ ላይ የሰፈረው የጥሪ መልዕክት የሚከተለው ነበር፡- ‹‹በአዲስ አበባ ከተማ ለምትገኙ ኢትዮጵያዉያን እስላሞች! ሰሞኑን በሕዝቡ መራጭነት የተቋቋመው ኮሚቴ በሕዝቡ ፍላጎት መሠረት ትዕይንተ ሕዝብ (ሰላማዊ ሰልፍ) የሚያደርግበትን መንገድ ካጠና በኋላ የሚከተለውን ውሳኔ አስተላልፏል። ይኸውም፤ ምንም እንኳን እናት አገራችን በአሁኑ ጊዜ በኢኮኖሚና በሶሻል ችግር ላይ ያለች መሆኗ ቢታወቅም በኛ ኢትዮጵያዉያን እስላሞችና በአገሪቱም ላይ ያለውን ችግር የጋራ መፍትሄ ያስገኛል ብለን ያመንበትን ጥያቄ ለማቅረብ ጊዜውና ሁኔታው አስገድዶናል። ስለዚህ በአዲስ አበባ ከተማ የምትገኙ ነጋዴዎች፣ የመንግሥትና የግል ድርጅቶች ሠራተኞች፣ ተማሪዎችና በልዩ ልዩ የሥራ መስክ ላይ ያላችሁ ሁሉ ፆታን ሳይለይ ለዚሁ ለተቀደሰ ዓላማ እንድትሰለፉ ይሁን። ትዕይንተ ሕዝቡ ሚያዝያ 12 ቀን 1966 ዓ.
نمایش همه...
ወጣት ወንዶች እስላም ማኅበር (ወ.ወ.እ.ማ) እና ወጣት ሴቶች እስላም ማኅበር (ወ.ሴ.እ.ማ.)፣ ሌሎችም የመሳሰሉትን ማኅበሮች ለማቋቋም እንድንችል በነጋሪት ጋዜጣ እንዲታወጁልን። 6. በጠቅላላው የመሬት ሥሪት መሻሻል አለበት ብለን እናምናለን። አሁን እንደተያዘው የመሬት ይዞታው በሚሻሻልበት ደረጃ ሥሪቱም አብሮ መሻሻል ይኖርበታል። እዚህ ላይ እንደምሳሌ አድርገን ልንጠቅስ የምንፈልገው ኢትዮጵያዉያን እስላሞች በአንዳንድ ሥፍራዎች ላይ ባለርስት መሆን ቀርቶ ከሌላ ባዕድ አገር የመጡ ይመስል ለመኖሪያቸው ያህል እንኳን በግል ሐብታቸው ገዝተው ለመሥራት አይፈቀድላቸውም። ስለዚህ እንደዚህ ያለውን ሥሪት ፈጽሞ መቅረት አለበት። 7. ይህ ከዚህ በላይ የተጠቀሰው የመሬት ሥሪት መኖር የሚያመራን ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት ምን ጊዜም ከልሳናቸው የማይለዩትን ‹‹አገር የጋራ ነው፤ ሃይማኖት የግል ነው›› የሚለው አነጋገር ትርጉም እንደሌለው አባባልና በሥራም እንደማይገለጽ ስለሚያደርገው የንጉሠ ነገሥታችንን መሪ ቃልና ጥቅስ በሥራ የመገለጹ ጉዳይ ጊዜው አሁን ስለሆነ አዲሱ ካቢኔ በተለይ በዚሁ አባባል ተመርቶ እግብር (ተግባር) ላይ እንዲያውለው እንጠይቃለን። 8. በብዛት በንግድ፣ በእርሻና በመሳሰሉት የሥራ ዘርፎች ተወስነን የምንገኝ ኢትዮጵያዉያን እስላሞች በመንግሥቱ ሥራ በመሳተፍ ለውዲቱ አገራችን ያለንን የሥራ ድርሻ እንድናበረክት፡- ሀ) በአገር አገዛዝ ለ) በፍርድ ሐ) በዲፕሎማቲክ መ) በወታደርና በጠቅላላው በመንግሥቱ የሥራ መስኮች ሁሉ በይበልጥ እንድንካፈል እንቅፋት የሚሆኑት ነገሮች እንዲወገዱልን፣ አዲሱ ካቢኔ ጥብቅ እርምጃ እንዲወስድልን እንጠይቃለን። 9. ለእስልምና ሃይማኖት መስፋፋት መንግሥት ድጋፍ እንዲያደርግልን እንጠይቃለን። ከሚደረጉልን ድጋፎችም አንዱን ለመጥቀስ ያህል የእስላም ሚሲዮን እንዲገባ ሙሉ ፈቃድ እንዲሰጥልን ነው። (እንደ ክርስቲያኑ ማለት) የሰበካም ባጀት እንዲመደብልንና ለስብከቱ የሚሠማሩ ሰዎች የሚሠለጥኑበት የኮርስ ዝግጅት እንዲደራጅልን። 10. በማንኛውም የመገናኛ ዘዴዎች ለምሳሌ እንደሬዲዮ፣ ቴሌቪዥንና በመሳሰሉት መገናኛዎች ሁሉ /እንደ ክርስትያኑ/ የእስልምና ሃይማኖት ስብከት ለማሠራጨት እንዲፈቀድልን። 11. ‹‹በኢትዮጵያ የሚገኙ እስላሞች›› እየተባለ በሬዲዮም ሆነ በቴሌቪዥን፣ ወይም በማንኛውም የመገናኛ ዘዴዎች የሚነገረውን አነጋገር በኛ በኢትዮጵያዉያን እስላሞች ላይ እንደውጭ አገር ኮሚኒቲዎች በገዛ አገራችን የባዕድነትን ስሜት ስለሚፈጥርብን ይህ ዓይነቱ አነጋገር ፈፅሞ እንዲቀርና ምናልባትም ስለኛ የሚነገር ነገር ቢኖር በነዚሁ የመገናኛ ዘዴዎች ‹‹ኢትዮጵያዉያን እስላሞች›› ተብሎ እንዲነገር እንፈልጋለን። ይህም ለማለት ካሰኙን ምክንያቶች አንዱ ኢትዮጵያ ማንኛውም ሃይማኖት ከመግባቱ በፊት ኑራ፣ ዜጎችም ‹‹ኢትዮጵያዉያን›› ተብለው ሲጠሩ የቆዩባት አገር እንደመሆኗ መጠን የተለያዩ እምነቶች ስለገቡ ብቻ በኢትዮጵያዉያን መካከል ልዩነት ማድረግ ስለማይገባ የልዩነት መንፈስ ሊያሳድሩ የሚችሉትን የቃልም ሆነ የሥራ ድርጊቶች እንዲቀሩ ጨምረን ለመጠየቅ ነው። 12. በየትምህርት ቤቶቹ ሁሉ የሃይማኖት ትምህርት በፕሮግራም ውስጥ ገብቶ ይሰጣል። የሚሰጠውም ትምህርት የአንድ ወገን የሃይማኖት ትምህርት ብቻ ስለሆነ የእስልምና ሃይማኖት ትምህርቱም በካሪኩለም ውስጥ ገብቶ ከሌሎች የትምህርት ፕሮግራሞች ጋር ተያይዞ እንዲሰጥልን እንፈልጋለን። 13. /እንደ ክርስትናው ሁሉ/ መንግሥት በመላ የኢትዮጵያ ክፍለ ግዛቶች መስጊዶች ሊሠሩባቸው ከሚገቡ ሥፍራዎች ላይ መስጊዶችን እየሠራ ከነመተዳደሪያቸው እንዲያደራጅልን ስንለምን፣ እስከ አሁን በነበረው የመስጊዶች ይዞታ ሲሠራባቸው እንደቆየው ሁሉ በጠቅላላው መስጊዶች የሚተዳደሩት ከእምነቱ ተከታዮች ከሚገኘው መዋጮና ስጦታ ስለሆነ አገልግሎታቸውም ለምእመናኑ ከመሆኑም በቀር ሌላ የገቢ ምንጭ ስለሌላቸው ንብረታቸው ሁሉ ከማናቸውም ግብር ነጻ እንዲሆኑና ከውጭ ለሚያስመጡትም እቃ ከቀረጥ ነጻ እንዲገባ እንዲደረግልን እንጠይቃለን። (የኢትዮጵያ የጥናትና ምርምር ተቋም፣ ማኑስክሪፕት ክፍል፣ ማኅደር ቁጥር 2400/01/4) ይቀጥላል……..
نمایش همه...
161👍 84
‹‹አትነሳም ወይ አትነሳም ወይ!የግፍ አገዛዝ አይበቃህም ወይ?›› ክፍል ሁለት 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 የዛሬ 50 አመት በ1966ዓል ልክ በዚህ ሳምንት እንዲህ ሆነ! 📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌 13ቱ ጥያቄዎችና የሰልፉ መታሰብ 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ‹‹ኢትዮጵያ ምን አደረገች? እንዲያውም ከሥር መሠረቱ በነብዩ ሙሐመድ ጊዜ የእስልምና ስደተኞችን ተቀብላ ለእስልምና ሃይማኖት መስፋፋት ምክንያት የሆነችው ኢትዮጵያ ናት፡፡ ምን አድርጊ ብለው ነው የሚጨቀጭቋት?›› (ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ) ******************************************* የአፄ ኃይለሥላሴ መንግሥት ክርስትናን በግልጽም በሥውርም በየዘርፉ ሲደጉም እስልምናን መግፋቱ ሙስሊሙን አሳርሮታል። የአገሪቱ ሐብት ሢሶው ለቤተ ክህነት ሲታወጅ ሙስሊሙ ባይተዋር መደረጉ ከንክኖታል። ክርስትና በመገናኛ ብዙኃን ሲሰበክ ሙስሊሙ ሰብዓዊ መብቱ መነፈጉ ቆጭቶታል። ክርስትና በየ ት/ቤቱ በትምህርት መልክ ሲሰጥ ኢስላም መናቁ አሳዝኖታል። ከሁሉ በላይ በሕገ-መንግሥቱ የመንግሥት ሃይማኖት ኦርቶዶክስ ክርስትና ሆኖ መደንገጉ የእግር ውስጥ እሳት ሆኖበታል። ሙስሊሞች እትብታቸው በተቀበረበት አገራቸው የርስት ባለቤት መሆን መነፈጋቸው ብግን አድርጓቸዋል። ክርስቲያን ሚሺነሪዎች ሙስሊሙን እምነት ያስለውጡ ዘንድ ከየአቅጣጫው ሲጎርፉ ሙስሊም ሚስዮናዉያን ላይ መግቢያው ተከርችሞባቸዋል። ይህን ሁሉ በደል ሙስሊሙ ላይ እያደረሰ የአፄው መንግሥት ‹‹የሃይማኖት ነጻነት አከበርኩ፤ ኢትዮጵያዉያን ያለ ልዩነት ተቻችለን የምንኖር ነን፤ ኢትዮጵያ የነጻነትና የዲሞክራሲ አገር ናት›› ወዘተ ሲል ያፌዝ ነበር። መንግሥት የሃይማኖት ነጻነት እንዳከበረ የሚገልጽ “Religious Freedom in Ethiopia” የተሰኘ መጽሐፍም በእንግሊዝኛና በዐረብኛ አሳትሞ ለዓለም አሰራጨ። ይህን በሚያደርግበት ጊዜ ሁሉ በሥውር ሕዝባዊ ኑሮ ዕድገት ሚኒስቴር እና ደህንነት መሥሪያ ቤት ከጸረ-ሙስሊም ሤራቸው አልተቆጠቡም ነበር። ሙስሊሙ ላይ በሚሆነው ነገር የተቆጩትና ከተለያዩ ት/ቤቶች የተውጣጡት ወጣቶች በአ/አበባ በአባድር ኢንስቲትዩት መዋለ ሕፃናት በአንድ ክፍል ውስጥ ተቀምጠዋል፤ የሙስሊሙ መብት የሚከበርበትን ዘዴ ለመማከር ስብሰባ የተቀመጡት በሕቡዕ (በምስጢር) ነበር። (ከዶ/ር አሕመድ ቀሎ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ፣ 2001፣ አ/አ፣ ኢትዮጵያ) የሙስሊሙን መብት ለማስከበር ምን ማድረግ እንደሚችሉ ይመክራሉ። የተለያዩ ሙስሊም ግለሰቦች እየተጨመሩበት ለተከታታይ ቀናት ስብሰባው ቀጠለ። በወቅቱ ‹‹ለጠቅላይ ሚኒስትር እንዳልካቸው ደብዳቤ እንጻፍ›› በሚል ሐሳብ ላይ ከስምምነት ይደርሳሉ። ይህ የመብት ትግል በአንዋር መስጂድ በወጣት ክበቡ በተዘጋጀው ዝግጅት ላይ ይፋ ሆነ። ‹‹ችግሮቻችንን ለመቅረፍ ለመንግሥት አቤቱታ እንጻፍ እና ትግል እንጀምር›› የሚለውን ሐሳብ ያደመጠው የዝግጅቱ ታዳሚ ‹‹አላሁ አክበር!›› እያለ ብሶቱን አስተጋባ። ‹‹የግድ አንድ ነገር አሁኑኑ መደረግ አለበት›› ተባለ። በቁጣና በወኔ የተነሳውን ሙስሊም ወጣት አሕመድ ቀሎ እና ሐጂ ሙሐመድ ሳኒ ሐቢብ አረጋጉ። ሐጂ ሙሐመድ ኢብራሒም ዐብዱሰላምም በመምከር ሙስሊሙ ተረጋግቶ ጉዳዩ ፈር እንዲይዝ አደረጉ። ጉዳዩን የሚያስተባብር አንድ ኮሚቴ ተዋቀረ። ኮሚቴውም ‹‹የሙስሊሙን ችግሮች አጥንቶ በጽሑፍ ከነመፍትሄ ሀሳብ እንዲያቀርብ›› ተብሎ ተወሰነ። ኮሚቴው የሚከተሉትን ግለሰቦች ያቀፈ ነበር፡- 1. አቶ ሙሐመድ አወል ከቴሌ ኮሚውኒኬሽን 2. አቶ አሕመድ ቀሎ (ዶ/ር) ከአውራ ጎዳና መሥሪያ ቤት 3. አቶ ዐብዱ አደም - የግል ኩባንያ ባለቤት 4. አቶ ዩሱፍ አሕመድ ዐሊ - የኢንዶ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ሀላፊ 5. አባቢያ አባጆቢር አባዱላ አባጂፋር - የሕግ ጠበቃ 6. ወጣት ኸሊል ዐብዱ - ከወጣቶች ክበብ 7. ወጣት ሙሐመድ ሐሰን - ከወጣቶች ክበብ የኮሚቴው አባላት በተለያዩ ግለሰቦች ቤት ውስጥ በድብቅ ስብሰባ ጀመሩ፤ በተደጋጋሚ በመገናኘት ከአሥር ጊዜያት በላይ ተሰበሰቡ። ‹‹የሙስሊሙ አበይት ችግሮች ናቸው›› የሚሏቸውን ጥያቄዎች የያዘ ረቂቅ አዘጋጁ። ረቂቁም ከአባት ኮሚቴዎች ዘንድ ቀርቦ ውይይት ተካሄደበት። የመጨረሻው ረቂቅም ተዘጋጀ። ጠቅላይ ሚኒስትር እንዳልካቸው ቢሮም ቀጠሮ ተያዘ። አሥራ ሦስት ጥያቄዎች የሠፈረበት ባለ አራት ገጽ ጽሑፍ ሚያዚያ 1 ቀን 1966 ዓ.ል ቀረበ። ውይይትም ተካሄደበት። በወቅቱ አንገብጋቢ የነበሩት 13ቱ የሕዝበ ሙስሊሙ ጥያቄዎች የሚከተሉት ነበሩ፡- 1. በየትምህርት ቤቱ የሚሰጠው የሃይማኖትና የሞራል ትምህርት የአንዱን ክፍል ሃይማኖት የተከተለ እንደመሆኑ እስላሞች ልጆቻቸው ሃይማኖታቸውን እንዳይለውጡ በመፍራት ወደየት/ቤቶች ሳይልኳቸው በመቅረቱ በዘመናዊ ትምህርት ያለንን ተካፋይነት አዳክሞታል። 2. በአንዳንድ የኢትዮጵያ ክፍለ አገሮች የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ የሆነ ሰው የማይንቀሳቀስ ንብረት እንዲኖረው ስለማይፈቀድለት ኢትዮጵያዉያን በሕግ ፊት እንዲኖራቸው የተወሰነው በእኩልነት የንብረት ማፍራት መብት በከፊል ተነፍገዋል። 3. በሕገ መንግሥቱ ማናቸውም ኢትዮጵያዊ ‹‹ማኅበር የማቋቋም መብቱ የተጠበቀ ነው›› ቢባልም በእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች የተቋቋመው ማኅበር ባለመፈቀዱና ከዚህም የተነሣ ኢትዮጵያዉያን እስላሞች በኢንተርናሽናል ደረጃ በሚካሄዱ የእስላም ሃይማኖት ተከታዮች በስብሰባዎች እንዳንካፈልና ከጊዜው አስተሳሰብ ጋር እንዳንራመድ አድርጎናል። 4. እንግዲህ የመንግሥቱ አመራር መሠረቱ ከሃይማኖት የታበለ እንዲሆን ይህ ሁሉ ችግራችንና ቅሬታችን መፍትሄ እንደሚገኝለት እናምናለን። (መንግሥት እና ሃይማኖት እንዲለይ) 5. ምናልባት የመንግሥቱ አመራር ሃይማኖትን መሠረት ከማድረግ የማይታበል የሆነ እንደሆነ ከላይ እንደተጠቀሰው ጉዳዩ የሚመለከተው የሕገ-መንግሥቱ አንቀፆችና ሌሎችም ከዚሁ ጋር የተያያዙ ድንጋጌዎች የማይለወጡ ከሆነ በኢትዮጵያ ዜጎች መካከል ልዩነት በማይፈጥር ሁኔታ የኛም ሃይማኖት የመንግሥቱን ድጋፍ የሚያገኝ ለመሆኑ በሕጉ ይረጋገጥልን ዘንድ የሚከተሉትን ጥያቄዎች እንዲፈጸሙልን እንጠይቃለን፡- 1. የእስልምና ሃይማኖት የመንግሥቱ ድጋፍ እንዲኖረው በሕገ-መንግሥቱ ውስጥ በጽሑፍ ሠፍሮ በሥራም ተገልፆ እንድናይ እንዲደረግልን። 2. ኢትዮጵያዉያን እስላሞች በእስልምና ሃይማኖት የሊቃውንት ጉባዔ በጠቅላላውም የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች መራጭነት የእስልምና መሪዎች ሙፍቲዎቹና ረዳቶቹ የመንፈሳዊውን ጉዳዮች እንዲመሩ በንጉሠ ነገሥቱ እንዲፀድቅልንና የአስተዳደሩም ድርጅት በሕግ እንዲመራልን፣ ለዚሁም መተዳደሪያ መንግሥት በጀት እንዲመድብልን። 3. የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች በ 1936 ዓ.ም በቁጥር 62 በወጣው አዋጅ ለብዙ ዘመናት ሲሠራበት ቆይቶ ባላወቅነው ምክንያት በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 33447 ንዑስ ቁጥር አንድ (1) በመለወጡና አሠራሩም የሕግ ድጋፍ የተነፈገው ስለሆነ አሁን የሸሪዓ ፍርድ ቤት ቅዱስ ቁርኣናችን በሚያዘው መሠረት አንድ ራሱን የቻለ አቋም ኖሮት በመንግሥት በጀት እየተዳደረ፣ ሕግጋት ተደንግገውለት፣ ወግና ሥርዓት ባለው አኳኋን በእምነቱ ተከታዮች እንዲመራ ተሻሽሎ በሕገ-መንግሥቱ ውስጥ ተጠቅሶ እንዲወጣልን። 4. የእስላም ሃይማኖት ተከታዮች በዓላት የሕዝብ በዓላት ሆነው እንዲከበሩ እንዲታወጅልን። 5.
نمایش همه...
👍 32 13
“ሌሊት መስገድን አስቦ ወደ ፍራሹ የሄደ ከዚያም እስከ ንጋት ዓይኑ ያሸነፈችው ያሰበውን አላህ ይፅፍለታል፤ እንቅልፉም ከጌታው ዘንድ ሶደቃ ይሆንለታል” ረሱል ﷺ
نمایش همه...
222👍 52
ታላቁ አሊም ሼህ አብድልለጢፍ ሸረፈዲን በጠና መታመማቸው ተገለፀ! 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 ሼህ አብድልለጢፍ ሸረፈዲን ፣በመዲና ዩንቨርስቲ በከፍተኛ ማዕረግ የተመረቁና በወሎ ከሚሴ እንዲሁም በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች በዳአዋ በርካቶችን በማስተማር እና በሀገር ሽማግሌነት ትልቅ ተሰሚነት ያላቸው ታላቅ አሊም ናቸው። ... ሼህ አብድልለጢፍ ሸረፈዲን በሰሜን ኢትዮጵያ ተከስቶ በነበረው ጦርነት ወቅት ህዝቡን በማሰተባበር ለተቸገሩ ወገኖች መሰረታዊ ቁሳቁሶችን በማቅረብ ህዝቡን በጦርነት ውስጥ ሲታደጉ የቆዩ ቢሆንም ለሁለት አመታት በአዋሽ አርባ እና በከሚሴ እስር ቤት ታስረው እንደነበር ይታወሳል። ... እስር ቤት ውስጥ በነበሩ ሰአት ህመሙ የጀመራቸው ሲሆን ከእስር ከተፈቱ በኋላ በሀገረ በቱርክዬ የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው የነበረ ሲሆን፣አሁን ላይ የህክምና ወጪው ከቤተሰብ አቅም በላይ በመሆኑ በአሊሞች እና የሀገር ሽማግሌዎች የተዊቀረ ኮሚቴ በተከፈተ አካውንት ድጋፍ እንድታደረግላቸው ጥሪ ቀርቧል። ... ድጋፍ ለማድረግ፦ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአካውንት :-1000392652788 የአካውንት ስም፦የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ኮምዩኒቲ ሰፖርት አካውንቱን የሚከታተሉ ኮሚቴዎች ሸኽ ጡሃ ሸኽ መሀመድ ሸኽ ሁሴን ሀሰን ሱሩር ሸኽ አህመድ አሊ ሃሰን ...
نمایش همه...
👍 138 62
“አምስቱ ሰላቶች፣ ከጁምዓ እስከ ጁምዓ፣ ከረመዳን እስከ ረመዳን በመካከላቸው ያሉትን ኃጢአቶች ያብሳሉ ታላላቅ ወንጀሎችን ሲቀር፡፡” ረሱል (ﷺ)
نمایش همه...
72👍 13
‹‹አትነሳም ወይ አትነሳም ወይ! የግፍ አገዛዝ አይበቃህም ወይ?›› 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 📌 የዛሬ 50 አመት በ1966 ዓል ልክ በዚህ ሳምንት እንዲህ ሆነ! 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ክፍል አንድ በእምነቱ ምክንያት መገፋቱ ሙስሊሙን አብግኖታል። የስውርና የግልጽ ሴራ ተጠቂነቱ ከንክኖታል። በገዛ አገሩ እንደ ሁለተኛ ዜጋ መቆጠሩ የእግር እሳት ሆኖበታል። ኢትዮጵያ ለሙስሊሙ ከክፉ ከእንጀራ እናት በላይ ከፋችበት። ‹‹አገር የጋራ ሃይማኖት የግል›› በሚል የሽንገላ ቃላት ሊያሞኙት እየሞከሩ በተግባር ግን የሃይማኖት ነጻነት መነፈጉ አብግኖታል። ከትምህርት አራቁት። ሙስሊም በመሆኑ ብቻ በአፄ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት ድርብ ጭቆና ቀመሰ። አንድነቱን በማሳጣት እርስ በርስ እየተጠራጠረ እንዲኖር መደረጉ ቆጭቶታል። የዘመናት ብሶትና ቁጭት ለመብቱ ሊታገል ሙስሊሙን ግድ አሉት። ከትግል ሥልቶቹ አንዱ ሕዝባዊና ሰላማዊ ሰልፍ ነበር። ቁጣውንና ብሶቱን በማሰማት የመብት ጥያቄውን ሊገፋበት ወሰነ፤ ይህም በዕለተ ቅዳሜ ሚያዚያ 12 ቀን 1966 ዓ.ል በመዲናችን አዲስ አበባ በዓይነቱና በስፋቱ ታይቶ የማይታወቅ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ነበር። ትዕይንተ-ሕዝቡ በኢትዮጵያም ሆነ በሙስሊሙ ታሪክ ጉልህ ሥፍራ ነበረው። ግና ተዘነጋ። በሰላማዊ መንገድ ለሚታገሉት ፈር ቀዳጅ ሆኖ ሳለ ቸል ተባለ። በሰልፉ ሙስሊሙ ብሶቱንና ቁጭቱን ገልጾ መብቱን ለማስከበር ነቅሎ ወጣ። መብቱንም መንግሥት ያረጋግጥለት ዘንድ አስገደደ። ‹‹የቅርብ ጊዜ ታሪካችን ነውና የግድ ልናውቀው ይገባል›› በሚል ታሪኩ ሰፋ ባለ መልኩ እንደሚከተለው ቀርቧል። የሰልፉ አቀነባባሪዎች እነማን ነበሩ? ለምን እና እንዴት ሊደረግ ቻለ? የወጣቱና የሙስሊሙ ተማሪ ሚና ምን ነበር? መነቃቃቱስ እንዴት ሊመጣ ቻለ? የሙስሊሙ ጥያቄዎችስ ምን ነበሩ? የወጣቶች ክበብ እና የዒድ ፓርቲ 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ‹‹እስላሞች ተጨቁነዋል እየተባለ በኢትዮጵያ ብጥብጥ እንዲነሳ ብዙ ጊዜ በመገናኛ ብዙሃን ወቀሳ ይነገራል፡፡›› (ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ) በአፄው ዘመን የመማር ዕድል ያገኙ ጥቂት ሙስሊም ተማሪዎች በአዲስ አበባ ከ 1950ዎቹ ጀምሮ ‹‹የዒድ ፓርቲ›› በሚል በዒድ ቀን ይገናኙ ነበር። በዚያው ዝግጅት ላይ ስለ ኢስላም የሚያስተምራቸው ግለሰብ እየፈለጉ፣ እየተማማሩና እየተዝናኑ ዒድን ያከብሩ ጀመር። በጥቂት ሙስሊሞች የተጀመረው ይህ ሂደት ቀስ በቀስ ስለሙስሊሙ ተጨባጭ ሁኔታ እና መብት ወደመወያየት ገባ። የእርስ በርስ ግንዛቤያቸውን ማዳበሪያ መድረክ ሆኖ ቀጠለ። ይህ በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ (የዛሬው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ) የተጀመረው የተማሪዎች የግንኙነት መድረክ ቀስ እያለ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎችን ቀልብ ሳበ። ዐብዱ መስዑድና ሙሐመድ ሐሰን ከመድኃኒዓለም ትምህርት ቤት፣ ሙሐመድ ዩሱፍ ከልዑል መኮንን ት/ቤት እና አበጋዝና ዐብዶ በሽር ከተግባረ-ዕድ ትምህርት ቤት በጋራ በመሆን በ1964 ዓ.ል ‹‹የሙስሊም ወጣቶች ክበብ››ን አቋቋሙ። ብዙም ሳይቆይ የክበቡን ዓላማ የተረዱ ወጣት ወንዶችና ሴቶች ከተለያዩ ት/ቤቶች ወደ ክበቡ በአባልነት ተቀላቀሉ። ክበቡም ከዒድ ፓርቲ ልምድ በመቅሰም በሙስሊም በዓል ቀናት ሙስሊሙ ተማሪ የሚገናኝበትንና የሚማማርበትን መድረክ ማዘጋጀቱን ተያያዘው። ከበዓል ቀናት ውጪም መገናኘትና መማማር እንዳለባቸው ተመካከሩ። ቋሚ የሚማሩበትንና ስለሙስሊሙ በደል፣ ስለመንግሥት ግልጽና ስውር ጸረ-ኢስላም ተግባራት፣ እንዲሁም የሙስሊሙ መብት የሚከበርበትን ቋሚ መንገድና አጠቃላይ መፍትሄ የሚገኝበትን ዘዴ ሊማከሩ ግድ ሆነ። ለመገናኘት የሚሆናቸው ስፍራ ሲታሰብ አንዋር መስጂድ ምቹ ሆኖ ታያቸው። የአንዋር መስጂድ አስተዳዳሪ የነበሩትን ሐጂ ዐብዱረሕማን ሸሪፍን ጠየቁ። እሳቸውም ወጣቶችን የሚያቀርቡ ነበሩና የመስጅዱን ቅጥር ግቢ ፈቀዱላቸው። ተማሪዎች በዚያ መገናኘት ጀመሩ። ሥፍራዋም ለክበቡ አባላት የስብሰባና የቤተ-መጽሐፍት አገልግሎትን መስጠት ጀመረች። የስፖርት፣ የሥነ-ጽሑፍ፣ የሴቶች፣ የደዕዋና መሰል ንዑስ ኮሚቴዎችን አዋቀሩ። በአጭር ጊዜ ውስጥ በርካታ ቁጥር ያለው ሙስሊም ወጣት አንዋርን አጥለቀለቀ። በኢስላማዊውም ሆነ በዓለማዊው ትምህርት እውቀት ያላቸውን ግለሰቦች በየሳምንቱ መጋበዙን ተያያዙት። ሸኽ ሐሚድ ዩሱፍ፣ ሐጂ ሙሐመድ ሳኒ ሐቢብ እና ሸኽ ሰይድ ሙሐመድ ሷዲቅ ዲናዊ ትምህርቶችን ለወጣቶች ያስተምሩ ጀመር። ሸኽ ሰይድ ሙሐመድ ሳዲቅ ከዲናዊ ትምህርት ጎን ለጎን ስለመብታቸውና ስለሙስሊሙ ጭቆና ወጣቶቹን ማስገንዘቡን ተያያዙት። አባቢያ አባጆቢር ስለ ሕግ ሲያስተምሩ ጋዜጠኛ ሐጂ በሽር ዳዉድና ሙሐመድ ኢድሪስ የተለያዩ አርእስቶችን እየመረጡ ወጣቱን ያነቃቁ ጀመር። ሐጂ ዐብዱልከሪም ኑር ሑሴን እና ሐጂ ዑመር ሑሴንም የየራሳቸው ፕሮግራሞች ነበሯቸው። በሂደት የወጣት ክበቡ ከአንዋር መስጂድ ወጣ እያለ መድረክ ለመፍጠር ሙከራ አደረገ። አባቶች ግን ሥጋት ነበራቸው። ምክንያቱም እነሱ ‹‹የሰላም ማኅበር›› በሚል ሥያሜ አቋቁመውት የነበረው ድርጅታቸው በኃይለ ሥላሴ ደህንነቶች በሐሰት ተወንጅሎ መዘጋቱ ይቆጫቸው ነበርና ነው። የወጣት ክበቡ ከቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ‹የዒድ ፓርቲ› አዘጋጅ ኮሚቴ ጋር በመተባበር አዳራሽ እየተከራየ ፕሮግራም በጋራ ማዘጋጀት ጀመሩ። መሰል የወጣት ክበቦች (ስብስቦች) በየአካባቢው ብቅ ብቅ አሉ። የወጣቱም ንቃተ-ሕሊና እየዳበረ ሄደ። የሕግ ባለሞያና ጠበቃ የነበሩት አባቢያ አባ ጆቢር (የጅማው አባጂፋር የልጅ ልጅ ልጅ ናቸው) በየቲያትር ቤቱ በሚዘጋጀው መድረክ በግልጽ ስለ ሙስሊሙ መብት መቀስቀሱን ተያያዙት። በዚህ ጊዜም ከደህንነት አባላት ዛቻና ማስፈራሪያ ይደርስባቸው ነበር። የሙስሊሙ መብት መጣሱ እጅግ ይቆጫቸው ነበርና የደህንነትን ዛቻና ማስፈራሪያ ከቁብ አልቆጠሩትም። በደህንነት አባላት እንዳይታፈኑ በመሥጋት ወጣቱ እያጀባቸው ቤት ድረስ ይሸኛቸው ነበር። በ1964 ዓ.ል በሲኒማ ራስ በተዘጋጀው መድረክ ‹‹የእስልምና ማኅበራዊ ግዴታዎች ምንድናቸው?›› በሚል ርዕስ ንግግር አድርገዋል። ‹‹ኢስላም ሕግም፣ ንግድም፣ ፖለቲካም፣ ባህልም፣ ሥልጣንም፣ ማኅበራዊ ኑሮም፣ ሳይንስም፣ ሁሉንም ነው። አንዱን ነገር ብቻ ነጥለን የምንመራበት ሳይሆን ሁለንተናዊ ነው›› ሲሉ አስተምረዋል። ወጣቱ ስለ መብቱና እምነቱ፣ ስለ ሕልውናው እና አገሩ ይጨነቅ ዘንድ፣ እንዲሁም ለሙስሊሞች መብት መከበር መታገል እንዳለበት ጥሪ አድርገዋል። ሌሎችም በተለያዩ አርእስቶች ሥር የየራሳቸውን ትምህርት ሰጥተዋል። በ1965 የዒድ ፓርቲና የወጣቶች ክበብ በጋራ በመሆን የአገር ፍቅር አዳራሽን ተከራይተው የትምህርት መድረክ አዘጋጁ። በመሰል መድረኮች ንቃተ-ሕሊናው የዳበረው ወጣት ስለሙስሊሙ መብት መጣስና አጠቃላይ ጭቆና ይማከር ያዘ። ዑለሞችንም ያማክር ቀጠለ።በመስጂድ መገናኘትና መወያየትን አዘወተረ። የመድኃኒዓለም፣ ተግባረ ዕድ፣ ኮሜርስ ት/ቤት እና የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች በይበልጥ ብርቱና ንቁ ተሳታፊ ነበሩ። ይቀጥላል……..
نمایش همه...
👍 340 132