fa
Feedback
AASTU Muslims union

AASTU Muslims union

رفتن به کانال در Telegram

ይህ የቴሌግራም ቻናል ሁሉንም የ አአሳቴዩ ሙስሊም ተማሪዎች የሚመለከት ቻናል ነው። በዚህ ቻናል ኢስላማዊ ትምህርቶች፣ የተለያዩ ዳእዋና ሙሃደራዎች እንዲሁም ጀመዓውን የሚመለከቱ መልእክቶች ይለቀቁበታል። ከዚህ ውጪ ሌላ ቻናል የሌለን መሆኑን እና የትኛውም ከዚህ ቻናል ውጪ የሚለቀቅ ነገር እኛን እንደማይወክል እናሳስባለን። ለማንኛውም አስተያየት @abdua00 @abduw99

نمایش بیشتر
1 649
مشترکین
+124 ساعت
+37 روز
-330 روز
آرشیو پست ها
﴿إِنَّ ٱللَّهَ وَمَلَٰٓئِكَتَهُۥ يُصَلُّونَ عَلَى ٱلنَّبِىِّ ۚ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ صَلُّواْ عَلَيْهِ وَسَلِّمُواْ تَسْلِيمًا ۝﴾ قَالَ ﷺ: «مَنْ صَلَّ عَلَيَّ صَلاةً صَلَّ اللهُ عَلَيْهِ بِهَا عَشَراً» በኔ ላይ አንድ ጊዜ ሶላዋት ያወረደ አላህ በርሱ ላይ አስር ጊዜ ሶለዋት ያወርድለታል اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ وَبَارِكْ عَلَى نَبِيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ 🍃🍂 ሱረቱል ካህፋንም መቅራት አንርሳ መልካም ጁምኣ ‼

~ከ ሁለት ዓመት በፊት በ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ(AASTU) ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች የተደረገ ምክር ቢጤ! ወንድም አቡ ሱፍያን t.me/AbuSufiyan_Albenan t.me/Sle_qelbachn1

~ከ ሁለት ዓመት በፊት በ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ(AASTU) ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች የተደረገ ምክር ቢጤ! ወንድም አቡ ሱፍያን t.me/AbuSufiyan_Albenan t.me/Sle_qelbachn1

ታላቁ የቲክቶክ መድረክ ደረሰ _ ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ! ! ! ስለኒቃብ መጠየቅ በምርቃት ቀን እስከ ማሳሰር ከመድረሱ በፊት ጀምሮ ስላለው የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ
ታላቁ የቲክቶክ መድረክ ደረሰ _ ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ! ! ! ስለኒቃብ መጠየቅ በምርቃት ቀን እስከ ማሳሰር ከመድረሱ በፊት ጀምሮ ስላለው የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ በሰፊው ይዳሰሳል። ሕገ- መንግስቱን ጥሰው ስለሚጥሱት መብት ሕጋዊ ቦታ በሰፊው ይተነተናል። ከእኛ ስለሚጠበቀው ነገርም በደንቡን ውይይት ይደረጋል። ሙባረክ አደም፦ በድምፃችን ይሰማ የመብት ትግል እንቅስቃሴ ፈርቀዳጅ ታጋይ፤ አክቲቪስት፤ ቲክቶከር፤ ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብዕና፤ የሂባ ፋውንዴሽን መስራች ነው። ፕሮግራማችንን በመድረክ መሪነት የሚያስተናብርልን ይሆናል። ሙስጠፋ ሺፋ፦በድምፃችን ይሰማ የመብት ትግል እንቅስቃሴ ወቅት ለታሰሩት ጠበቃ ሆኖ አገልግሏል፤ አሁንም በጥብቃና ሙያው አንቱታን ካተረፉ ባለሙያዎች መካከል ነው። ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ሕጋዊ መሠረት ያብራራልናል። የሕያ ኢብኑ ኑሕ፦የንፅፅር ትምህርት መምህር፤ የሒዳያ ኢስላማዊ ማህበር መስራች እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብዕና ነው። ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ ያብራራልናል። ሁሴን ዩሱፍ፦የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፀሐፊ ሲሆን ከማን ምን ይጠበቃል የሚለውን በዝርዝር ያስቀምጣል። መቅረት አይታሰብም። ጀመዓዎች በቻናሎቻችሁ ላይ አሰራጩት። ሁሉም ለሁሉም ያድርስ። በአንድነት በአንድ መድረክ ተሰባስበን ስለመብቶቻችን እውቀትን እንጨብጥ። 🗓 ቀን፡ ሰኞ፣ ሰኔ 22 (Monday, 29 June) ⏰ ሰዓት፡ ከምሽቱ 03፡00 ሰዓት እውቀትን መፈለግ መብት ነው፤ እምነትንም በክብር መተግበር እንዲሁ! የቲክቶክ ገፃችንን Follow በማድረግ ዝግጅቱን ይጠብቁ፦ https://www.tiktok.com/@aaumsu ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu

በዛሬው ቀን ከአዲስ አባባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለምትመረቁ ጓደኞቼ እንዲሁም ወንድምና እህቶቼ እንኳን ደስ አላችሁ! 🎓🎉 ለኣ.ሳ.ቴ.ዩ ጀማዓ መቼም የማይረሳ አሻራን በመጣል ከናንተ በታች ላሉ ታናናሽ እህትና ወንድሞቻችሁ አርአያ መሆን ችላቿልና አሏህ መልካም ተግባራችሁን ዘውታሪ ያድርግላችሁ! ✨ ብዙ ለፍታቿልና ከእንግዲህ በሗላ ያለውንም ረበና አግርቶላችሁ ሀገርና ወገንን የምትጠቅሙ ያድርጋችሁ 🇪🇹🚀 مبارك التخرج! 🎓🎉 أسأل الله العظيم أن يفتح لكم أبواب الرزق والتوفيق في حياتكم المهنية القادمة، وجعل الله كل جهد بذلتموه في ميزان حسناتكم وأنار دربكم، ونفع بعلمكم وابتكاراتكم البلاد والعباد. 🤲✨ اخوكم عبد الوكيل

ሰሞኑን ዛሬን ጨምሮ ከተለያዪ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂ ለሆናችሁ ሙስሊም ወንድምና እህቶቼ እንኳንም ለዚህ የልፋታችሁን ውጤትና ደስታ በከፊል ለምታዩበት ቀን በሰላም አደረሳችሁ! 🎓✨ እንኳንም ደስ አላችሁ! 🎉 ባገኛችሁት እውቀትና ተሞክሮ ሙስሊሙን ኡማ የምትጠቅሙ፣ ዳግማዊ ነፃነቱና ልእልናውንም የምታውጁ አሏህ ያድርጋችሁ! 🤲🌟 Abdulwekil gezu

በድጋጋሚ የተለቀቀ ♻️ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለምትመረቁ ውድ ጓደኞቼ ፣መላው የአስቱ ሙስሊም ተማሪዎች ፣ በተለይም   ትልቅ አሻራ እሳርፋቹ ጀመአውን ተረክባቹ፣ የምችሉትን ሁሉ ሰጥታቹት (ቀን ለሊት ስለ ጀመአው እያሰባቹ) ፣ ከበታቹ ላላቹት አስረክባቹ በመሄድ ላይ ትልቅ አሻራ የአሳረፋቹ ወንድሞች እና እህቶች እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለው። ቀጣይ ህይወታችሁ ያማረ ለኢስላምም የምትሰሩበት አሏህ ያድርጋችሁ!አሚን🤲🤲 ♻️ماشاء الله تبارك الله مبارك عليكم أيها الخريجون جميعا سعدنا بفرحتكم، جَعَلَ اللهُ حَيَاتَكُمْ حياة طيبة وَجَعَلَكُمْ مِمَّنْ يَعْمَلُونَ لِخِدْمَةِ الْإِسْلَامِ،والمسلمين ✅ይህች ግጥም ለናንተ ናት👇👇👇 አራት አምስት አመት ስንሰራ ስንለፋ፣ ስንቱን ችግር አየን ህይወትን ልንገፋ ፣ አልፎ ከራሳችን ቤተሰብ ሊደሳ ፣ እንዴት ልብ ይነካል ያ ታሪክ ሲነሳ ። ግባችን ደረሰ ዓላማችን ቀና ያመታት ልፋቱ ተተካ በፋና ለዚህ ላደረሠን ላለማቱ ጌታ ሃምድን አድርሰናል ለቸረን ፈገግታ ማብቂያው ዛሬ መሠል ቢመርጠን ጀሊሉ ፣ ለመመረቅ በቁ ደስ ይላል መባሉ፣ ቀናችን በርቶልን መድመቁ መኳሉ፣ ደስታችን ዛሬ ነው ሹክረን ሊላህ በሉ ። በካምፓስ ህይወት ላይ… አንዱ ሆኖ ከንቱ፣ ሌላው ቀድሞ ነቅቶ… ሸሽቶ ከጠላቱ፣ ከፊሉ ለነፍሱ የቀረው ሲል ኡማ፣ ይሰቅላል ከፍ አርጎ… የኢስላምን አርማ ፣ ሞልተዋል ብርቱዎች የታገሉ ብዙ ፣ በአላህ መንገድ ላይ ኢብሊስ ያፈዘዙ፣ ሰዎችን አመስጋኝ እኔን የሃመደ፣ ይለናል ጌታችን በኔ ተወደደ፣ እህት ወንድሞቼ ቀናችን ነው ዛሬ ፣ በግዜው ሲቀምሱት ይጣፍጣል ፍሬ ፣ ምንም ብንለያይ ቀናችን ተቆርጦ፣ መገናኘት አለ ለጀነት ተመርጦ ። አላህ ያገናኘን !!!! ✍️ወንድማቹ አቡ ሀሪስ (አይመን ሁሰይን)

🎉 Congratulations to the AASTU Muslim Graduates! 🎉 To all the AASTU Muslim students graduating today, we extend our heartfelt congratulations on your remarkable success and achievements. Your hard work, dedication, and resilience have brought you to this beautiful milestone. As you step into the next chapter of your lives, we pray that Allah (SWT) blesses your journey ahead, grants you barakah in your knowledge, and opens doors to endless opportunities. May He make you a source of pride and benefit to your families, your community, and the Ummah. 🎓 Barakallahu Lakum! 🎓 — AASTU Muslim Students Union @aastumuslims

﴿إِنَّ ٱللَّهَ وَمَلَٰٓئِكَتَهُۥ يُصَلُّونَ عَلَى ٱلنَّبِىِّ ۚ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ صَلُّواْ عَلَيْهِ وَسَلِّمُواْ تَسْلِيمًا ۝﴾ قَالَ ﷺ: «مَنْ صَلَّ عَلَيَّ صَلاةً صَلَّ اللهُ عَلَيْهِ بِهَا عَشَراً» በኔ ላይ አንድ ጊዜ ሶላዋት ያወረደ አላህ በርሱ ላይ አስር ጊዜ ሶለዋት ያወርድለታል اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ وَبَارِكْ عَلَى نَبِيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ 🍃🍂 ሱረቱል ካህፋንም መቅራት አንርሳ መልካም ጁምኣ ‼

✅ ለHabesha Tech Full Stack Web Development Course Scholarship የመወዳደሪያ መስፈርቶች 📌 10 top scoring and skilled students will be granted scholarships 👉 Full Name 👉 Email 👉 Department 👉 Year 👉 CGPA 👉 Programming languagea you know: ‼️ (አንድ ላንጉጅ አውቀዋለሁ ለማለት ቢያንስ በዛ ላንጉጅ የተፃፈ ቀለል ያለ ኮድ ምን እንደሚሰራ መረዳት ምትችሉ ከሆነ ነው) 👉 Choose those which you know from the following: ✅ React.js ✅ Node.js ✅ Express.js ✅ PostgreSQL ✅ MySQL ‼️ If you don't know all of them, it is okay. 👉 Latest grade report (Take photo and send it as evidence) 🎤 Send all of the above required fields, and becareful not to miss any detail. 💥 Send to: @Zuzenith Join our channel and get the website: https://t.me/habesha_tech_lessons

◼️የአሹራ ቀን ፃም በተመለከተ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ አቢ ቀታዳ አል አንሷርይ አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና እንዲህ አለ። ✅ የአላህ መልእክተኛ ስለ አሹራ ቀን መፃም ተጠይቀው እንዲህም አሉ፦ 【ያለፈውን አንድ አመት ወንጀል ያብሳል】ብለዋል። 📚(ሙስሊም ዘግቦታል።) ◼️መቼ ነው የሚጀመረው⁉️ 〰〰〰〰〰〰〰〰〰 የአሹራ ቀን ፃም የሚጀመረው፦ አሁን ያለንበት የሙሀረም ወር አስረኛው ቀን ላይ ነው። ይህም ማለት የፊታችን ሐሙስ ሰኔ 18 / 2018 ይሆናል ። ◼️እንዴት ነው የሚፃመው⁉️ 〰〰〰〰〰〰〰〰〰 ↪️ አህለል ኪታቦችን ለመ ኻለፍ ዘጠነኛውን ቀን መፃም የፈለገ (በላጩም ይህ ነውና) የፊታችን እሮብ ሰኔ 17 / 2018 ላይ ይጀምርና እሮብ ና ሐሙስን በተከታታይ ይጾማል ። ↪️ ዘጠነኛው ቀን መጨመር ያልተመቸው አስረኛውና አስራ አንደኛው ቀን ማለትም ሀሙስና ጁማዓ መፃም ይችላል። አላህ ይውፍቀን... መረጃውን ለሌሎችም በማጋራት ከወዲሁ እናስታውስ

﴿إِنَّ ٱللَّهَ وَمَلَٰٓئِكَتَهُۥ يُصَلُّونَ عَلَى ٱلنَّبِىِّ ۚ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ صَلُّواْ عَلَيْهِ وَسَلِّمُواْ تَسْلِيمًا ۝﴾ قَالَ ﷺ: «مَنْ صَلَّ عَلَيَّ صَلاةً صَلَّ اللهُ عَلَيْهِ بِهَا عَشَراً» በኔ ላይ አንድ ጊዜ ሶላዋት ያወረደ አላህ በርሱ ላይ አስር ጊዜ ሶለዋት ያወርድለታል اللهم صل وسلم وبارك على نبينا محمدﷺ 🍃🍂 ሱረቱል ካህፋንም መቅራት አንርሳ መልካም ጁምኣ ‼

⚠️ የጥንቃቄ መልእክት السلام عليكم ورحمة الله وبركاته، ውድና የተከበራችሁ ወንድም እህቶች፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዚህ የቴሌግራም ፕላትፎርም እግባብነት የሌላቸው ማስፈንጠሪያዎች (links) እየተዘዋወሩ እንደሆነ ግልጽ ነው። ሊንኮቹ የሚነክስቸውን ሰው አካውንት በመመንተፍ ለኮንታክቶቻቸው ራሳቸውን እንዲልኩ ኦቶሜት ተደርገው የተዘጋጁ ናቸው። ከላያቸው ላይ "ፕሪሚየም በነጻ" እና መሰል አጓጊ መልእክቶችን ያዘሉ ጽሑፎች (click baits) አሉባቸው። እኛ እነዚህን ማስፈንጠሪያዎች በምንነካበት ወቅት ትላልቅ ጥፋቶች እንዲከሰቱ ሰበብ እንሆናለን፦ 1. ያንኑ ተመሳሳይ ሊንክ በመበተን የሌሎች ሰዎች አካውንቶች እንዲጠለፉ እና እንዲመነተፉ እናደርጋለን። 2. እነኚህ ሊንኮች ባብዛኛው ነውር አዘል ይዘት ስለሚኖራቸው ሌሎችን ወንጀል ውስጥ እንከታለን፣ የራሳችንን ክብር በገዛ እጃችን እናጎድጋለን፣ ነገሩን ካልተረዱ ሰዎች ጋር እንድንጋጭ ይሆናል። 3. መንታፊዎቹ አካውንታችንን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ስለሚችሉ ልወዳጅ ዘመዶቻችን ውደነሱ የባንክ አካውንቶች ብር እንዲልኩ የሚጠይቁ መልእክቶችን በመላክ ሰውን የሚያሳስቱበት እድል እንዲኖር እናደርጋለን። እሁን ላይ ትዝ ያሉኝን ጉዳቶች ነው የጠቀስኩት። ከጠቀስኳቸውም ሌላ ከህግና ከሸሪዓ አንጻር መጥፎ የሆኑ መዘዞችን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ጥንቃቄ በማድረግ ራሳችንንም ሌሎች ወንድም እህቶቻችንንም እንጠብቅ። ይህን ሁሉ ለመከላከል የሚከተሉትን ነጥቦች ትኩረት ብንሰጣቸው ጥሩ ነው እላለሁ፦ 1. ቴሌግራም ላይ የምናገኛቸውን ማስፈንጠሪያዎች ከምናምነው አካል ያውም ለአስፈላጊ ቁም ነገር ካልሆነ በስተቀር አለመንካት። (እዚህጋ ማስተዋል የሚገባችሁ ነገር "ነጻ ገንዘብ" የሚባል ነገር አለመኖሩን ነው።) 2. የቴሌግራም መተግበሪያዎቻችን ላይ "Two-step Verification" የሚለውን የsecurity ማስተካከያ አማራጭ መጠቀም። ይህ የሚረዳን ሰዎች ወይም ኦቶማቲክ ቦቶች ዘው ብለው ወደ አካውንታች እንዳይገቡ ተጨማሪ የይለፍ ቃል በመጠየቅ ነው። 3. ይህ ነገር በማወቅም ሆነ ባለማወቅ በድንገት ከተከሰተብን 24 ሰዓት ሳይሞላው በፊት በፍጥነት "Terminate All Other Sessions" የሚለውን የማስተካከያ አማራጭ በመጠቀም ከኛ ዲቫይስ ውጪ ያሉ ሌሎች ዲቫይሶችን ከአካውንታችን ማገድ። (እዚህ ጋር መጠንቀቅ ያለብን በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ እኛ ቀድመን ካላቋረጥንባቸው እነሱ በተቃራኒው እኛን ከአካውንታችን በማስወጣት እድሜልክ የአካውንታችንን ባለቤትነት ይወርሱታል። ማለትም ዳግመኛ ያንን አካውንት መጠቀም የማንችልበት ሁኔታ ይፈጠራል።) መልእክቱን ለሌሎች በማስተላለፍ ግዴታችንን እንወጣ!

﴿إِنَّ ٱللَّهَ وَمَلَٰٓئِكَتَهُۥ يُصَلُّونَ عَلَى ٱلنَّبِىِّ ۚ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ صَلُّواْ عَلَيْهِ وَسَلِّمُواْ تَسْلِيمًا ۝﴾ قَالَ ﷺ: «مَنْ صَلَّ عَلَيَّ صَلاةً صَلَّ اللهُ عَلَيْهِ بِهَا عَشَراً» በኔ ላይ አንድ ጊዜ ሶላዋት ያወረደ አላህ በርሱ ላይ አስር ጊዜ ሶለዋት ያወርድለታል اللهم صل وسلم وبارك على نبينا محمدﷺ 🍃🍂 ሱረቱል ካህፋንም መቅራት አንርሳ መልካም ጁምኣ ‼

In addition to this, please be informed that a special holiday meal has been prepared by the university cafe and will be served after the Eid prayer at morning 3:30 Local Time (9:30 AM).

በአሁኑ ወቅት ባለው ወቅታዊ የነዳጅ እጥረት ምክንያት ዩኒቨርሲቲው የባስ (የአውቶቡስ) አገልግሎት ማቅረብ የማይችል መሆኑን እናሳውቃለን። በመሆኑም የዒድ ሰላት የሚሰገደው ኮዬ ንፋስ ስልክ በመሆኑ እና ሰላቱ በጧት 2:00 ሰዓት ስለሚጀምር፣ ከኮዬ አደባባይ የንፋስ ስልክ ታክሲዎችን በመያዝ መሄድ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ለመላው የአዲስ አበባ ሳይንስ ና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች፣ በዙሪያው ላላቹ ነዋሪዎች እና ለተከበራችሁ የቻናላችን ተከታዮች 🌙እንኳን ለ1446ኛው የዒድ አል_አድሀ 🐏🐏🐏 በዓል በሰ
ለመላው የአዲስ አበባ ሳይንስ ና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች፣ በዙሪያው ላላቹ ነዋሪዎች እና ለተከበራችሁ የቻናላችን ተከታዮች 🌙እንኳን ለ1446ኛው የዒድ አል_አድሀ 🐏🐏🐏 በዓል በሰላም አደረሳችሁ🌙                   ❤️ዒድ ሙባረክ❤️ تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال አላህ መልካም ሥራችንን ሁሉ ይቀበለን!  ጥፋታችንንም ይቅር ይበለን። የደስታ የሰላም እና የተባረከ ዒድ ይሁንልን!! @aastumuslims

[ዙል-ሒጃ 9](የአረፋ ቀን ፆም) ============================= 👉ይህን ቀን መፆም ያለውን ምንዳ አስመልክቶ የአላህ መልዕክተኛ(ﷺ) እንዲህ ብለዋል:- 👉"የዐረፋ እለት የፆመ ሰው ያለፈውን አንድ አመት እና የሚመጣውን የአንድ አመት ወንጀሉን ያስምረታል ብየ እከጅላለሁ"ማለታቸው ተዘግቧል። (ሙስሊም)📚 👉ዙልሂጃ 9 ወይም የአረፋ ቀን በዱንያ ላይ ካሉ ቀናቶች ሁሉ የበለጠች ቀን ናት። 👉ረሱል(ﷺ) "አላህ ባሪያውን ከእሳት ነፃ የሚያወጣበት ቀን ከአረፋ ቀን በላይ የለም"ማለታቸውም ተዘግቧል። (ሙሰሊም)📚 👉 ይህን ወድ ቀን ሁላችንም ልንጠቀምበት ይገባል። ለወንጀላችን ምህረት የምንጠይቅበት፣ከእሳት ነፃ እንዲያወጣን አልቅሰን የምንማፀንበት፣ላስጨነቀን ነገር ሁሉ መፍትሄ ለማግኝት አላህን የምንማፀንበት ቀን ነው። 👉የአላህ መልዕክተኛ(ﷺ)"በላጩ እና ምርጡ ዱዓ በአረፋ ቀን ውስጥ የተደረገ ዱዓ ነው"ብለዋል።በዚህ እለት እኔም ሆነ ሌሎች ነብያት ከተናገሩት ሁሉ በላጭ ደግሞ፤ላ ኢላሀ ኢለላህ፤ወህደሁ ላ ሸሪከ ለሁ፤ ለሁል ሙልክ ወለሁል ሀምዱ ወሁወ ዓላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር።የሚለው ነዉ። (ቲርሙዚ ዘግበውታል)📚 አላህን ከሚጠቀሙበት ያድርገን።

photo content

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته To All Graduating Students Starting Their Final Exams Today May Allah bless you all as you step into your final exams today! I am praying that He fills your hearts with peace, grants your minds clarity, and rewards all your hard work. Take a deep breath, put your full trust in Allah (Tawakkul), and walk into that exam room with confidence. 💡 A Beautiful Reminder: Before you open your exam booklet, take a moment to pause and recite this powerful Dua for ease:
"اللَّهُمَّ لَا سَهْلَ إِلَّا مَا جَعَلْتَهُ سَهْلاً، وَأَنْتَ تَجْعَلُ الْحَزْنَ إِذَا شِئْتَ سَهْلاً" “O Allah, nothing is easy except what You make easy, and You can make the difficult easy if It is Your will.”
May Allah make this exam season incredibly smooth for you and crown your years of dedication with the best results. Have a truly blessed exam! You've got this. @aastumuslims