ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
This channel is not operated by Deacon Yaregal Abegaz- ይህ ገጽ የሚንቀሳቀሰው በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ አይደለም https://youtube.com/@yaregalabegaz?si=1f5NHTaQ2l2LbxWQ “ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።” — 2ኛ ቆሮ 11፥28
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
کانال ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ (@yaregalabegaz) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 39 863 مشترک است و جایگاه 1 548 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 862 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 39 863 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 04 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 721 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 14 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 20.14% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 8.26% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 8 028 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 3 292 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 57 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“This channel is not operated by Deacon Yaregal Abegaz- ይህ ገጽ የሚንቀሳቀሰው በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ አይደለም
https://youtube.com/@yaregalabegaz?si=1f5NHTaQ2l2LbxWQ
“ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።”
— 2ኛ ቆሮ 11፥28”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 05 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 05 سپتامبر | 0 | |||
| 04 سپتامبر | +17 | |||
| 03 سپتامبر | +37 | |||
| 02 سپتامبر | +19 | |||
| 01 سپتامبر | +13 |
| 2 | ወርኃ ጳጉሜን
ዕለተ ምርያ
ወርኃ ጳጉሜን በዓመቱ መጨረሻ የምትገኝ በአገራችን ኢትዮጵያ እንደ ዐሥራ ሦስተኛው ወር የምትቆጠር ናት፤ ወርኃ ጳጉሜን አምስት ቀናት ያሏት ስትሆን በአራት ዓመት አንድ ጊዜ በዘመነ ሉቃስ መውጫ በዘመነ ዮሐንስ መግቢያ ያለው ስድስት ቀን ይሆናል፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላታቸው ጳጉሜን እንዲህ ይተረጉሟታል፤ ጳጉሜን ማለት ጭማሪ ተውሳክ፣ አምስት ቀን፣ ከሩብ፣ ከዐውደ ወር ተርፎ በዓመቱ መጨረሻ የተጨመረ ስለሆነ ትርፍ ተጨማሪ ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት፣ ገጽ ፱፻፭)
በወርኃ ጳጉሜን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ተከብረው (ታስበው የሚውሉ በዓላት አሉ፤ በሌላ ስያሜም ዕለተ ምርያ (የመዳን ወር ) ትባላለች፤ ምርያ ማለት ከቀን ወደ ቀን የሚያሻግር፣ አንድም ዕለተ ኅሪት ዕለተ መድኃኒት ማለት ነው፤ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት፣ ገጽ ፮፻፰) ምእመናን በዚህች ወቅት ጸበል ይጠበሉባታል (ይጠመቁበታል)፡፡
ሊቀ መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል
ጳጉሜን ሦስት ቀን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከምታከብራቸው በዓላት አንዱ የሊቀ መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል በዓል ነው፤ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል በዚህች ዕለት ዓመታዊ ክብረ በዓሉ ይከበራል፡፡ በድርሳነ ቅዱስ ሩፋኤል እና በወርኃ ጳጉሜን ሦስት ቀን የሚነበበው ስንክሳርና የተጻፉት ድርሳናት እንዲህ ያስተምሩናል፤ አንዲት ክርስቲያን ሴት በቅዱስ ሩፋኤል ሰም በባሕር መካከል ባለች ደሴት ቤተ ክርስቲያን አሳነጸች፤ ሊቀ ጳጳሱ አባ ቴዎፍሎስ በዚህች ዕለት ቅዳሴ ቤቱን አከበረ፤ ከደሴቲቱ ሥር የነበረ ግዙፍ ዓሣአንበሪም ባሕሩን ባናወጠው ጊዜ በደሴቲቱ የታነጸቸውን ቤተ ክርስቲያኗን ሊያፈርስ ደረሰ፤ በውስጧም ለበዓል ተሰብስበው የነበሩ ምእመናን በጸሎት ወደ ቅዱስ ሩፋኤል ተማጸኑ፡፡
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤልም ከእግዚአብሔር ተልኮ መጣ፤ ሕዝቡን ታደገ፤ ከደሴቲቱ ሥር ያለውንም ግዙፍ ዓሣአንበሪው እንዳይንቀሳቀስ በጦር ወጋው፤ ‹‹እግዚአብሔር አዞሃልና ከቦታህ ሳትናወጽ ጸጥ ብለህ ቁም!›› አለው፤ ጸጥ ብሎም ቆመ፡፡ ሕዝቡም ከባሕሩ ከመስጠም፣ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኒቱም ከመፍረስ ተረፉ፤ ቅዱስ ሩፋኤል ይህን ድንቅ ተአምር አድርጎ፣ ከፈጣሪው አማልዶ፣ ለጠሩት ፈጥኖ የደረሰበትን ይህን በዓል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዓመቱ መጨረሻ ባለችው ወርኃ ጳጉሜን በሦስተኛ ቀን በድምቀት ታከብሯለች፡፡ (ስንክሳር ዘወርኃ ጳጉሜን ሦስት ቀን)
በዚህች ዕለት ከሚከበሩ በዓላት ሌላኛው በመጽሐፍ ቅዱስ በመጽሐፈ ጦቢት እንደተጻፈው ቅዱስ ሩፋኤል በመልካም ምግባሩ፣ በምጽዋት ሥራው ለሚታወቀው ለጦቢት በችግሩ ጊዜ በሰው አምሳል ተገልጦ፣ እንደ ሠራተኛ ተቀጥሮ በማገልገለል ልጁ ጦቢያን ከዓሣአንባሪ ፣ ሣራ የተባለችን ሴት ያሠቃያት ከነበረው ርኩስ መንፈስ፣ ጦቢትን ከዓይን ሕመሙ የፈወሰበት የቅዱስ ሩፋኤል ተራዳኢነት፣ የጦቢት መልካም ምግባር፣ የእግዚአብሔር ቸርነት የተገለጠበት መታሰቢያም በዓል ነው፡፡ (መጽሐፈ ጦቢት አንድምታው መግቢያ) ይህች ዕለት ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል የተሾመበት መታሰቢያውም ነው፤ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ጸሎት ይጠብቀን፤ አሜን!!!
ዕለተ ምጽአት
ወርኃ ጳጉሜን የዕለተ ምጽአት መታሰቢያም ናት፤ እግዚአብሔር ለፍርድ ወደዚህ ምድር የሚመጣበት ወቅት መታሰቢያ ነው፤ ነቢየ እግዚአብሔር ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹የአማልክት አምላክ እግዚአብሔር ተናገረ፤ ከፀሐይም መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያዋ ድረስ ምድርን ጠራት፤ ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል፤ ዝምም አይልም ….›› በማለት እንደተናገረው ጌታችንም በደብረ ዘይት ተራራ ለደቀ መዛሙርቱ ዳግመኛ ለፍርድ እንደሚመጣ በገለጸው መሠረት ወደዚህ ምድር ለጻድቃን ሊፈርድላቸው፣ በኃጥአን ሊፈርድባቸው ይመጣል፤ (መዝ. ፵፱፥፩-፫) ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መቼ እንደሚመጣ ዓመቱንና ዕለቲቱን በግልጽ ባይነግረንም ዳግመኛ ግን እንደሚመጣ ነግሮናል፤ ‹‹…ስለዚህ እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፤ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና፡፡›› (ማቴ.፳፬፥፵፬)
ቅዱስት ቤተ ክርስቲያንም የዕለተ ምጽአቱን መታሰቢያ በዐቢይ ጾም እኩለ ሳምንት ላይና በወርኃ ጳጉሜን ሦስተኛው ቀን ታከብራለች፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በሰዓታት ጸሎት ላይ ‹‹ለምጽአትከ ከዋላ እስከነ ዘመን ወዕድሜ፣ ለመለኮትከ ዘአልቦ ፍጻሜ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ አምላከ ሱላሜ፤ አመጣጥህ በኋለኛው ዘመን የሆነ ለአገዛዝህ ፍጻሜ የሌለህ ኢየሱስ ክርስቶስ የፍቅር አምላክ ነህ›› በማለት እንደተናገረው ለዘመኑ ፍጻሜ የሌለው የፍቅር አምላክ ፈጣሪያችን ዳግመኛ ይመጣል፡፡ (ስብሐተ ፍቁር)
ሐዋርው ቅዱስ ጴጥሮስ በመልእክቱ ‹‹ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋው ቃል አይዘገይም፤ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል›› ብሎናልና፡፡ (፪ኛ ጴጥ.፫፥፱) ጌታ ስለ ተስፋው ቃል አይዘገይምና ሕይወታችንን በንስሐ አንጽተን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ተቀብለን ተዘጋጅተን ልንጠብቀው ይገባል፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር ‹‹…ኑ እናንተ የአባቴ ቡሩካን…›› ከሚላቸው ወገን ይደምረን! ምስጋና ለእርሱ ይሁን፤ አሜን!!!
ርኆተ ሰማይ
ይህች ዕለት ርኆተ ሰማይ (የሰማይ መስኮቶች የሚከፈቱባት)፣ ሊቃውንቱ የሰማይ ደጆች ተከፍተው የምእመናን ጸሎት የሚያርጉበት በዓመት አራት ጊዜያት እንዳሉ ይገልጻል፤ ታዲያ የመጀመሪያው ዕለት ጳጉሜን ሦስት ቀን በመሆኑ ይህች ዕለት ርኆተ ሰማይ ትባላለች፡፡ የሰማይ መስኮቶች ተከፍተው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል የምእመናንን ጸሎት ለእግዚአብሔር የሚያሳርግበት ዕለትም መታሰቢያ ነው፡፡ የእግዚአብሔር የምሕረት ደጆች የሚከፈቱባት ዕለት መታሰቢያ ናት ርኆተ ሰማይ ! አባቶችና እናቶች በትውፊት በዚህች ዕለት ዝናም ሲዘንብ በእምነት የቤታቸውን ዕቃ (ሌማቱን፣የቡሆዕቃ…) ከሰማይ በሚወርደው ዝናመ ምሕረት እንዲባረክላቸው ከውጭ አውጥተው ያስመቱታል፤ ምእመናን በዚህች ዕለት በሚዘንብ ዝናብ ይጠመቁበታል፤ በርኆተ ሰማይም በጳጉሜን ሦስት ቀን!!!
የኦሪቱ ሊቀ ካህን የመልከጼዴቅ መታሰቢያ
በዚህች ዕለት የጌታችን ምሳሌ የሆነው የኦሪቱ ሊቀ ካህን የመልከጼዴቅ መታሰቢያ ነው፤ መልከ ጼዲቅ ማለት ንጉሠ ጽድቅ ንጉሠ ሰላም ማለት ነው፡፡ ከተማዋም በእርሱ ኢየሩሳሌም/የሰላም ከተማ /ተብላለች፡፡ መልከ ጼዲቅ የእስራኤል እምብርት /ዋና ከተማ/ ኢየሩሳሌምን ያቀና ከካም ወገን የሆኑት የኖኅ የልጅ ልጅ ነው፡፡ እግዚአብሔር አስቀድሞ ለኖኅና ለልጁ ለሴም ከካም ወገን የተለየ የተባረከ ልጅ እንደሚወለድና አጽመ አዳምን ይጠብቅ ዘንድ የተመረጠ መሆኑን ነግሮት ስለነበር ሴም በታዘዘው መሠረት ወደ ማዕከለ ምድር ቀራንዮ ወስዶ አጽመ አዳምን እንዲጠብቅ በእግዚአብሔር የተመረጠ መሆኑን ነግሮት በክህነቱ መፈጸም ስለሚገባው/በኑሮው ስለሚገልጠው/ ሥርዐት ሠርቶለታል፡፡ በክህነቱ እግዚአብሔርን ሁል ጊዜ እንዲያመሰግን የእንስሳት መሥዋዕት እንዳይሠዋ መሥዋዕቱ ንጹሕ ስንዴና ወይን እንዲሆን በእጁም ደም እንዳያፈስ ነግሮታል፡፡ | 3 198 |
| 3 | ቅዳሜ ይጠብቁን
https://youtu.be/En5-U3WVxlE?si=pQLHC2P_Yk3HMqEq | 163 |
| 4 | "የተጠራነው እንድንቀደስ ነው"
#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ | 4 013 |
| 5 | መታገል
#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ | 6 775 |
| 6 | بدون متن... | 8 056 |
| 7 | ጌታን ሲከተሉት የነበሩ አይሁድ "ከሰማይ የወረደ እውነተኛ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ" የሚለውን የጌታ ቃል በሁለት ምክንያት ለመቀበል ተቸግረው ነበር። ለጊዜው ፍላጎታቸው ምድራዊውን ምግብ አበርክቶ የሚያበላቸው ሰው ነው፡፡ ሁለተኛው እንዴት ሥጋውን ለመብልነት ሊሰጣቸው እንደሚችል ማሰብ አልቻሉም። በዚህ ትምህርቱ " እንዴት ልንከተው እንችላለን" ብለውም ጥለውት ሄዱ። ይኼንን የወንጌል ክፍል ለማየት ሞክረናል። አድምጡት
https://youtu.be/Dt2XogkyzFk?si=m15uIes48_xP5kNO | 8 238 |
| 8 | የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው:: ሙት አንስተዋል፤ ድውያንን ፈውሰዋል፤ አጋንንትን አሳደዋል፤ እሳትን ጨብጠዋል፤ በክንፍ በረዋል፤
ደመናን ዙፋን አድርገዋል፤ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መስርተዋል፤ በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕፃናት አብረው ኑረዋል፤ በዘመናቸው ሰይጣን ታስሯልና::
ዕረፍት
ጻድቅ፣ ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው፣ መከራን በብዙ ተቀብለው፣ እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው በተወለዱ በ፺፱ ዓመት: ከስምንት ወር ከ አንድ ቀናቸው ነሐሴ ፳፬ ቀን በ፲፻፫፻፮ ዓ.ም ዐርፈዋል:: ጌታችን፣ ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል፤ ፲ ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል::
የጻደቁ አባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ በረከታቸው ይደርብን፤ አሜን፡፡
ምንጭ፡- ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት | 8 240 |
| 9 | በዓለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
አምላካችን እግዚአብሔር ለነቢዩ ኤርምያስ “በሆድ ሳልሰራህ አውቄሃለሁ፤ ከማኅፀን ሳትወጣ ቀድሸሃለሁ” በማለት እንደተናገረ የገናናው ጻድቅ የአባታችን ተክለ ሃይማኖት ዜና ሕይወቱን እንዘክራለን፡፡ (ኤር.፩፥፭)
ልደት
ደጋጎቹ ካህኑ ጸጋ ዘአብና እግዚእኃረያ የእግዚአብሔር ሰዎች ነበሩ፡፡ እነርሱም እንደሌሎች ቅዱሳን እናት እና አባቶቻቸው ልጅ አተው ኖረዋል፡፡ እንደነ አብረሃም እና ሣራ፣ እንደ እነ ዘካርያስ እና ኤልሳቤጥ ማለት ነው። እግዚኃርያም ሁል ጊዜም ወደ ቤተ እግዚአብሔር ታመለክት ነበር። ከዕለታት አንዲት ቀን መላኩ ተግልጾ ልጅ እንደሚወልዱ ነገራቸው። እርሱ በክህነቱ እርሷ በደግነቷ በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል::
አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት በመጋቢት ፳፬ ቀን ፲፻፪፻፮ ዓ.ም ተፀንሰው በሸዋ ክፍለ ሀገር በጽላለሽ ወይም በዞረሬ አካባቢ ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብ እና ከእናታቸው ከእግዚኃርያ በታኅሣሥ ፳፬ ቀን በታኅሣሥ ፳፬ ቀን በ፲፻፪፻፯ ዓ.ም ተወለዱ፡፡ ሲወለዱም ሥላሴን “ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ” ብለው አመስገነዋል። ጻድቁ በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጿል፤ ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል::
አባታችን ተክለ ሃይማኖት ክርስትና ወይም የሥላሴን ልጅነት ሲቀበሉ አባቱ ጸጋ ዘአብ ሲቀድስ ያመሰግን ነበር፡፡ እናቱም ደግሞ “አንተ ልጅ አሁን ጡጥ ጥባ እንጂ” እያለች ትሞግተው ነበር። የካህን ልጅ ካህን እንዲሉ ገና ሲወለድ ጀምሮ “ተክለ አብ ተክለ ወልድ ተክለ መንፈስ ቅዱስ” በማለት ምስጋና ስለጀመረ አባት እና እናቱ እጅግ ተደሰቱ፡፡
ዕድገት
ጻድቃኖች የቅዱሱ ወላጆች እግዚአብሔር ለሰጣቸው የተመረጠ ልጅ የመጀመሪያ ያወጡላቸው “ፍሥሃ ጽዮን” የሚል ስም ነው:: በዚህም ስያሜ አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይም ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያትና ሐዲሳትን) ተምረዋል:: ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁናም ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ ተቀብለዋል::
መጠራት
ከዕለታት በአንዱ ቀን ፍሥሃ ጽዮን ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ:: የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑት በቅዱስ ሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ::
በመቀጠልም የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ፤ “ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን:: ከአሁን በኋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ” ብሎትም በግርማ ዐረገ:: ጻድቁ ተክለ ሃይማኖትም ጊዜ አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ::
አገልግሎት
ጻድቁ አባት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ:: አባታችን በኢትዮጵያ በረሃዎች ወንዞች ሸንተረሮች እና አውራጃዎች እየተዘዋወሩ በልዩ ልዩ አምልኮ የነበረውን ሕዝብ የክርስቶስን ወንጌለ መንግሥት አስተምረው እና አጥምቀው የክርስቶስን መንግሥት እንዲወርሱ ያደረጉ ታልቅ ጻድቅ ናቸው። በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ፲ ሽህ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ:: ያን ጊዜ ኢትዮዽያ ሁለት መልክ ነበራት::
አንደኛ ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽእኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዶ እና በባዕድ አምልኮ ተጠምዶም ነበር::
ሁለተኛው ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር::
ግማሹ ሀገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ:: ሕዝቡን እንዲሁመ መሳፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው ማርያኖችን (ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል::
አባታችን ተክለ ሃይማኖት በዚህ ዓለም ላይ ወንጌልን መሰረት አድርገው የሐዋርያትን ሥራ ፈለግ በመከተል ብዙ ተጋድላዋል። ለሀገራችን ለኢትዮጵያ በዚህ ዓለም ብዙ ደክመዋል።፡ ለዚህም ነው በአንድ ወቅት አባታችን “ወለእመ ጠፋአ ማሕቶት አልቦ ዘየሐቱ ሎቱ ዘእንበለ ዘይከድኖ ጽልመት፤ መብራት ቢጠፋፋ የሚያበራለት የለም፤ ጨለማ ከሚወርሰው በቀር።” ለአቃቤ ሥርያኒ መኑ ይፌውስ ለአመኢያመረ ፈውሰ ለእረሱ ከማሁ ኮነት ነፍስዬ በላዕሌየ ቀሰምኩ ባዕዳነ ወለሳህዩኩ ለልየ ሰረይኩ፤ አሕዛበ ወደወይኩ ለልየ አብራይኩ ለዓለም ወጸለምኩ ለእርስየ፤ ባለ መድኃኒትንስ ማንን ይፈውሰዋል፤ ከእራሱ የሚድንበት ካላወቀ ነፍሴ በእኔ ላይ እንዲሁ ሆነች፤ ሌሎችን ግን አጣፈጥኩ፤ ለእራሴ ግን አልጫ ሆንኩ፤ ሕሙማንን ፈወስኩ፤ ለእራሴ ግን ድውይ ሆንኩኝ፤ ለዓለም አበራሁ፤ ለእራሴ ግን ጨለምኩ” በማለት እንደተናገሩ ገድላቸው ይጠቅሳል። ይህ የሚያመለክተው አባታችን ተክለ ሃይማኖት ረኃቡን፣ ጥሙን፣ መካራ ሥቃዩን ታግሠው በጾም እና በጸሎት እንዲሁም በስግደት ተጋድሎ በማድረግ በየተራረው እየዞሩ በዚህች በመራረው ዓለም ጣፋጭ ወንጌልን በማስማር ኢትዮጵያን ያጣፈጡ እንደሆኑ ነው፡፡ ሥራቸውም በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለዓለም እንዳበራ የተመሠከላቸው ነው፡፡
ገዳማዊ ሕይወት
ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በሦስት ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል:፡ እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ፲፪ ዓመታት፣ በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለሰባት ዓመታት፣ በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለሰባት ዓመታት፣ በአጠቃላይ ለ፳፮ ዓመታት አገልግለዋል::
በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ (ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ፳፪ ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም ስድስት ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለሰባት ዓመታት ጸልየዋል::
ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ እስራኤል የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ፣ እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር::
የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከፅንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር:: ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ፣ በቤተ መቅደስ ብሥራቱን፣ በቤተ ልሔም ልደቱን ፣በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን ፣በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን ፣በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር::
የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ::
በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን ወደ ሰማይ አሳረገቻቸው:: በዚያም የብርሃን ዐይን ተቀብለው ስድስት ክንፍ አብቅለው፣ የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው፣ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው፣ ከ፳፬ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው ፣ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው -“ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ” ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል::
ተአምራት | 7 822 |
| 10 | ታላቅ የምሥራች
የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ወደ ሮሜ ሰዎች በዮሐንስ አፈወርቅ በመምህር ሽመልስ መርጊያ ተተርጉሞ ጀምሮ ገበያ ላይ ውሏል።
በሰርዲኖን መጽሐፍ መደብር ታገኙታላችሁ። | 8 464 |
| 11 | https://youtu.be/5VGAbdNmosU?si=M31d3BkqFlTD-tiS | 7 040 |
| 12 | https://youtu.be/jCaa_Q-auC4?si=HUJmQ49Sqcmx5H9a | 6 883 |
| 13 | بدون متن... | 7 490 |
| 14 | 📖 መማር እንሻለን - የትምህርት ቁሳቁስ ማሰባሰቢያ ዘመቻ
ማኅበራዊ ቀውሶች የብዙ ሕፃናትን የትምህርት ጉዞ አግድመውታል። የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት እነዚህን ሕፃናት ለመደገፍ ሰፊ የንቅናቄ ዘመቻ ጀምሯል።
🔹 ዓላማ፦ ሕፃናቱ በትምህርት መሣሪያ እጥረት ሳይስተጓጎሉ ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ማድረግ።
🔹 መዋጮ፦ የአንድ ተማሪ ዓመታዊ ቁሳቁስ ወጪ 3,300 ብር ቢሆንም፣ ማንኛውም ሰው የቻለውን ያህል (አንድ ደብተርም ቢሆን) ማበርከት ይችላል።
🏦 የባንክ መረጃዎች፦
CBE: 1000309803648
Ahadu: 0025393810901
Abyssinia: 23375458
Wegagen: 083731610101
📍 የመቀበያ ቦታ፦ አምስት ኪሎ ማኅበረ ቅዱሳን ሕንፃ 1ኛ ወለል | 8 362 |
| 15 | بدون متن... | 8 938 |
| 16 | https://vt.tiktok.com/ZSVQxEynb/ | 93 |
| 17 | 📚#መድሎተ_ጽድቅ
እነኾ ቅጽ ፪ ለ6ኛ ጊዜ ታትሟል
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623 | 9 955 |
| 18 | ከክርስትና በፊት የነበረው አረማዊው ዓለም (pagan world) ድሆች ፣ ሕሙማን እና አካል ጉዳተኞች በአማልክቱ የተረገሙ እንደሆኑና ርኅራኄ እንደማይገባቸው ያምን ነበር። ለእነዚህ የተገለሉ የማኅበረሰብ ክፍሎች መራራት ለአረማዊው ዐለም እንግዳ የሆነ፣ የክርስትና ግን መሠረታዊ ተፈጥሮ ነበር። ክርስቲያኖችም ከአረማውያኑ የሚለዩበት ልዩ መታወቂያቸው ይህ ለተቸገሩትና ልዩ ልዩ ደዌ ለጸናባቸው ሰዎች የሚያሳዩት ፍቅር ርኅራኄና እንክብካቤ ነበር። በጥንታዊቷ ቤተክርስቲያን ለነበሩ ክርስቲያኖች ምጽዋት እንደ አማራጭ በጎ ስራ (virtue) የሚደረግ አልነበረም። ይልቁንም ክርስቲያን ያደረጋቸው መሠረታዊ ማንነታቸው እንጂ። በዛሬው ቆይታችን ይህንን የጥንቷ ቤተክርስቲያን ስለነዳያን የነበራትን አቢዮታዊ አቋም ፣ ዛሬ ካለው መረዳትና ልምምድ ጋር በስፋት ለማነጻጸር ሞክረናል። መልካም ቆይታ።
https://youtu.be/cy9mYo1cFw0?si=3FKQyHXn4yO_Nnvj | 9 195 |
| 19 | በቤተክርስቲያን ስም የሚቀርቡ ቤተክርስቲያንን የማይወክሉ ድምጾች
https://vt.tiktok.com/ZSV53oA5w/ | 8 126 |
| 20 | በመንፈስ ቅዱስ የተሸመነች አንድ የክርስቶስ አካል ቤተክርስቲያን
https://vt.tiktok.com/ZSV5ccJxQ/ | 9 601 |
