ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
This channel is not operated by Deacon Yaregal Abegaz- ይህ ገጽ የሚንቀሳቀሰው በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ አይደለም https://youtube.com/@yaregalabegaz?si=1f5NHTaQ2l2LbxWQ “ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።” — 2ኛ ቆሮ 11፥28
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
کانال ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ (@yaregalabegaz) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 38 754 مشترک است و جایگاه 1 652 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 855 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 38 754 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 21 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 885 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 21 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 25.95% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 8.97% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 10 050 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 3 475 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 112 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“This channel is not operated by Deacon Yaregal Abegaz- ይህ ገጽ የሚንቀሳቀሰው በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ አይደለም
https://youtube.com/@yaregalabegaz?si=1f5NHTaQ2l2LbxWQ
“ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።”
— 2ኛ ቆሮ 11፥28”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 22 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 22 ژوئیه | +23 | |||
| 21 ژوئیه | +27 | |||
| 20 ژوئیه | +22 | |||
| 19 ژوئیه | +29 | |||
| 18 ژوئیه | +21 | |||
| 17 ژوئیه | +37 | |||
| 16 ژوئیه | +37 | |||
| 15 ژوئیه | +18 | |||
| 14 ژوئیه | +40 | |||
| 13 ژوئیه | +20 | |||
| 12 ژوئیه | +28 | |||
| 11 ژوئیه | +20 | |||
| 10 ژوئیه | +18 | |||
| 09 ژوئیه | +11 | |||
| 08 ژوئیه | +31 | |||
| 07 ژوئیه | +15 | |||
| 06 ژوئیه | +30 | |||
| 05 ژوئیه | +38 | |||
| 04 ژوئیه | +59 | |||
| 03 ژوئیه | +45 | |||
| 02 ژوئیه | +45 | |||
| 01 ژوئیه | +41 |
| 2 | ብሒለ አበው
"በፈተናዎች ባልተፈተንን ጊዜ ራሳችንን የበለጠ ማዋረድ ይኖርብናል ምክንያቱም እግዚአብሔር ደካማነታችንን አይቶ እየጠበቀንና ፈተናውን እያስቀረልን ነውና፤ ራሳችንን ከፍ ካደረግን ግን ጥበቃውን ከእኛ ያርቅብንና እንጠፋለን፡፡"
አረጋውያን
" መርከብ ያለ ምስማር ሊሠራ እንደማይችል ሁሉ ድኀነትም ያለ ትሕትና ሊገኝ አይችልም፡፡"
ቅድስት ስንቀሌጢቃ
" የትሕትና ከፍታ እጅግ ታላቅ ነው፤ የመታበይ ጥልቀት ደግሞ እጅግ ጥልቅ ነው፤ የመጀመሪያውን እንድት ከተል ወደዚህኛው ደግሞ እንዳትወድቅ እመክራለሁ፡፡"
አባ ኤስድሮስ
"ሰውን ሊያድነው የሚችለው ብሕትውና ወይም ትጋሃ ሌሊት ወይም ማንኛውንም ዓይነት መከራ መቀበል ሳይሆን እውነተኛ ትሕትና ብቻ ነው፡፡"
አረጋውያን አበው
"ምድር ከሁሉም በታች ስለሆነ ካለባት ወደ ታች አይወርድም፣ ራሱን ዝቅ የሚያደርግም እንዲሁ አይጣልም፡፡ ዝቅተኛ የሆነች ምድር ውኃን ትቀበላለች፣ ራሱን በትሕትና ዝቅ የሚያደርግም እንዲሁ ከሁሉም በላይ ይጠቀማል፣ በክርስ ቶስ ቀኝም ያለ ነቀፋ ሆኖ ይቆማል፡፡"
አባ ጴሜን | 2 254 |
| 3 | https://youtu.be/WH_vMW6aTK4?si=OQK_7w5asZIvqeiJ | 3 162 |
| 4 | https://youtu.be/WH_vMW6aTK4?si=OQK_7w5asZIvqeiJ | 1 |
| 5 | የምክር ቃል
ቅዱስ፣ ጥንቁቅ፣ ግልጽና ብልህ ሁን፡፡ እርጋታን የተላበሰ ሰብእና ይኑርህ፡፡ ደስተኛ ሁን፤ ሰላምታህ በፈገግታ የታጀበ ንጹህ ይሁን፡፡ ንግግርህ የታረመ አጭርና በጨው እንደተቀመመ ጣፋጭ ይሁን፡፡ ቃላቶችህ የተመጠኑ እና ጤናሞች ሁሉም የሚረዳቸው ይሁኑ፡፡
የጓደኛህን ምስጢር አትግለጥ፤ ለሚወዱህ ሁሉ የታመንክ ሁን፡፡ ወደ ጭቅጭቅ እና ንትርክ ከመግባት ራህን ጠብቅ፡፡ የሚሰሙህ ሁሉ እንዳይጠሉህ ወደ ጠብ አትግባ፡፡ ከሰይጣን በቀር ምንም ጠላት አይኑርህ፡፡
የሰዎችን ስህተት አትመራመር፤ የባልንጀራህ ኃጢአት አትግለጥ፡፡ የባልጀራህ ውድቀት ደጋግመህ አታውራ፡፡ በራስህ ኃጢአት ላይ ፍረድ እንጂ በሌሎች ላይ አትፍረድ ገዢያቸው አይደለህምና፡፡
ኃጢአትን በፈጸመ ሰው ላይ ወቀሳ አታብዛ አንተም ትበድላለህና፡፡ ነገር ግን ከኃጢአቱ ይመለስ ዘንድ ረዳትና መካሪ ሁነው፡፡ ከወደቀበትም የስህተት ሥራ እንዲወጣ አበርታው፡፡ ተስፋውን በእግዚአብሔር ላይ ቢያደርግ ኃጢአቱን ልክ በእሳት ፊት እንደወደቀ ገለባ ፈጥኖ እንደሚወገድለት ንገረው፡፡
ተፈጥሮ እንደ መጽሐፍ ፍጥረታት እንደ ጽላት ይሁኑህ፡፡ ከእነሱ ሕግጋትን ተማር፤ በተመስጦ ሆነህ በመጽሐፍ ያልሰፈሩትን ምስጢራት ተረዳ፡፡
እግዚአብሔርን ከሚፈራ በቀር ባለጸጋ የሆነ ሰው ማነው? የእውነት እውቀት ከጎደለው ሰው በላይ ፍጹም ደሃ የሆነ ማን ነው? ሁል ጊዜም እውነተኛ ፍቅራችን ጸንቶ ይቀጥል ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸልይ፡፡ እርሱን ለምነው፡፡ ስለ ቸርነቱ ምስጋና አቅርብ፤ ምክሬን ፈጽሞ ቸል አትበል፡፡
#ቅዱስ_ኤፍሬም_ሶርያዊ | 4 593 |
| 6 | "አንተ ራስህ ለገዛ ወንድምህ ጨካኝና ይቅር የማትል ኾነህ ሳለስ እግዚአብሔር እንዲራራልህና እንዲምርህ እንዴት መለመን ይቻልሃል?
"ባልንጀራህ ምናልባት ንቆህ ሊኾን ይችላል፡፡ አዎ! አንተ ግን እግዚአብሔርን ኹልጊዜ እንደናቅኸው ነው፡፡ በባልንጀራና በእግዚአብሔር መካከልስ ምን ንጽጽር አለ? ባልንጀራህ ምናልባት ጉዳት ሲደርስበት ሰድቦህ ይኾናል፤ አንተም በዚህ ተበሳጭተህ ይኾናል፡፡ አንተ ግን ምንም ሳይጎዳህና በአንተ ላይ ክፉ ሳያስብ ይልቁንም ዕለት ዕለት በረከቱን እየተቀበልክ እያለ እግዚአብሔርን ሰድበኸዋል፡፡ እንግዲህ ተመልከት! ነቢዩ፡- “እመሰ ኃጢአተኑ ትትዐቀብ እግዚኦ መኑ ይቀውም - አቤቱ ኃጢአትንስ ብትጠባበቅ ማን ይቆማል?” ብሎ እንደ ተናገረ እግዚአብሔር በእርሱ ላይ የምንፈጽመውን በደል ቢመረምር ኖሮ አንዲት ቀንስ እንኳን በሕይወት መቆየት አንችልም ነበር (መዝ.129፡3)፡፡
እያንዳንዱ በደለኛ ሰው ለራሱ የሚያውቀውንና ሌላ ሰው የማይመሰክርበትን እግዚአብሔር ብቻዉን ግን የሚያውቀውንስ ይቅርና የተገለጠውና ሰው ኹሉ የሚያውቀው ኃጢአታችንን እንኳን እግዚአብሔር ቢቈጣጠር ኖሮ ከእነዚህ ኃጢአቶች በኋላ የምንጠብቀው ምንድን ነው? እግዚአብሔር ንዝህላልነታችንንና ጸሎት ስናደርስ የምናሳየው ግድየለሽነታችንን፣ ሠራተኞች ለአሠሪዎቻቸው ወታደሮችም ለአለቆቻቸው ጓደኛሞች ለጓደኞቻቸው የሚያሳዩትን ፍርሐትና ክብር ያህልስ እንኳን ለጸሎትና ለልመና በፊቱ በቆምን ጊዜ አለማሳየታችንን ቢቈጣጠር ኖሮ ምን ነበር የምንኾነው?
አንተ ከጓደኛህ ጋር ስትነጋገር ለምታደርገው ማንኛውም ነገር ትጠነቀቃለህ፡፡ ስለ በደሎችህ እግዚአብሔርን ስትጠብቀው፣ ለብዙ መተላለፎችህ ይቅርታን ስትጠይቀው፣ ሥርየትን ለማግኘት ስታሳስበው ግን [በፊቱ ላይ] ኹልጊዜ ግድየለሽ ትኾናለህ፡፡ ጉልበትህ በምድር ላይ ተንበርክኮ ሳለ ልቡናህ ግን እዚህም እዚያም፣ በገበያ ሥፍራም፣ በቤት ውስጥም ይዋልላል፤ ከንፈርህ በከንቱና እንዲሁ ያነበንባል፤ ይህን የምንፈጽመው ደግሞ አንዴ ወይም ኹለቴ ሳይኾን ኹልጊዜ ነው።
እንግዲህ እግዚአብሔር ይህን ብቻ እንኳን ቢመረምር ይቅርታን ወይም ምሕረትን እንደምናገኝ ታስባለህን? በእውነት አይመስለኝም!"
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
#ትምህርት_በእንተ_ሐውልታት_መጽሐፍ
ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው | 5 263 |
| 7 | "ዲያብሎስ ልጅነታችንን እናቆሽሽ ዘንድ በእኛ ላይ የሚተናኰለው ተንኰል በጣም ተደጋጋሚና ኃይለኛ ነው፡፡ ስለዚህ ይህን መንቻካ የዲያብሎስን ደባ ድል እንነሣ ዘንድ ዘወትር ንቁዎችና ጠንቃቆች ልንኾን ይገባናል፡፡ እኛ ይህን ማድረግ ሳንችል ቀርተን እጅግ #ጥቂት መግቢያ ቀዳዳ የምንተውለት ከኾነ ግን እርሱ #ጥቂቷን ቀዳዳ ሰፊ በር ያደርጋታል፡፡ እንዲህ አድርጎም ኃይሉን ኹሉ ተጠቅሞ ወደ እኛ ይገባል፡፡
ስለዚህ ስለ ድኅነታችን የሚገደን ከኾነ እንደዚህ #ጥቂትና ቀልድ በሚመስሉ ነገሮች እንኳን #አንዘናጋ፤ እርሱ የሚንቀውና #ጥቂት የሚለው ኃጢአት የለምና፡፡ እኛ #ጥቃቅን የምንላቸውን ነገሮች መነሻ አድርጎ ልጅነታችንን የምናቆሽሽበትን #ታላላቅ ኃጢአቶችን እንድንሠራ አድርጎ እጅግ ይተጋልና፡፡"
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ | 6 653 |
| 8 | https://youtu.be/WH_vMW6aTK4?si=NmJK-vj6Ez9TLlup | 8 340 |
| 9 | ሐምሌ 7/2018
#ታሪክን_የኋሊት
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፣ ሁለተኛው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ ፣ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉት ፣በ1971 ዓ.ም በዛሬው ቀን ነበር፡፡
ፓርትርያክ ብፁዕ ወቅዱስ አባ ቴዎፍሎስ በግፍ የተገደሉት በኮሎኔል መንግስቱ ኃ/ማርያም በሚመራው ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ ትዕዛዝ ነው፡፡
ደርግ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፣ የንጉሱን አስተዳደር የምትደግፍና ፣ ለሶሻሊዝም ሥርዓት እንቅፋት ነች ብሎ ስላመነ ፣ ለማጥቃት የሚፈልግበትን መንገድ ሲያደራጅና የስም ማጥፋት ፕሮፓጋንዳ ሲያከናውን ቆየ፡፡
ከአንድ አመት በኋላም ፓትርያርኩንና ሊቃነ ጳጳሳትን አሰረ፡፡
ብጹዕ ወቅዱስ አባ ቴዎፍሎስ ፣ ሁለተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ሆነው የተሰየሙት፣ የመጀመሪያውን ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ ፣ ብጹዕ ወቅዱስ አባ ባሰልዮስን ተክተው ነው፡፡
ከዚያ በፊትም የሀረር ሊቀ ጳጳስና የፓትርያርኩ እንደራሴ ሆነው በጠቅላላው ለ20 አመታት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን በሀላፊነት አገልግለዋል፡፡
ብጹህ ወቅዱስ አባ ቴዎፍሎስ ፣ በፕትርክና ዘመናቸው ፣ ቤተ ክርስቲያኗ ራሷን ችላ ለመተዳደር የሚያበቃትን ፣ የሰበካ ጉባኤ አደረጃጀት አስጀምረዋል፡፡
የአለም ዐብያተ ቤተ ክርስቲያን ምክር ቤት አባል አድርገዋል፡፡
የቤተ ክርስቲያኗ ልማት እንዲስፋፋ የልማት ተራድኦ ኮሚሽንን አቋቁመዋል፡፡
ሃይማኖት የለሽ መሆንን መመሪያው ያደረገው ወታደራዊው መንግስት ፣ በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ እንደማይገባ ቢናገርም፣ ግን የሃይማኖት ተቋሞችን ለመቆጣጠር የሚያስችለውን አሰራር ዘርግቶ ነበር፡፡
ስለዚህ ፓትርያርኩንና ሌሎች ጳጳሳትን የሌሎች ሃይማኖት መሪዎችንም አሰራቸው፡፡
ከቤታቸው በወታደሮች ተወስደው የታሰሩት ብፅዕ ወቅዱስ አባ ቴዎፍሎስ ከታሰሩበት ቦታ ለማምለጥ ችለው ነበር፡፡
ወደ አሰቦት ገዳም ለመሄድ ስላሰቡ ፣ ለጉዟቸው ዝግጅት ለማድረግ ጎፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ተሸሸጉ፡፡
ግን በጎፋ ገብርኤል ግቢ መሆናቸውን ፣ የሚያውቅ ሰው ከድቶ ፣ ለደርግ ጠቆመ ተያዙ፡፡ በወታደሮች ሲያዙ፣ ብዙ ግፍ ፈፀሙባቸው፡፡
ጫማቸውን አስወልቀው በእግራቸው አስኬዷቸው፡፡ለአንድ ወር ያህል በአንዲት ጠባብ ጨለማ ክፍል አስገብተው ፣ እጃቸውንና እግራቸውን ከአልጋ ጋር በሰንሰለት አሰሯቸው፡፡
የሚይዙትን የወርቅ መስቀል ወሰዱባቸው፡፡ ከአንድ ወር ቆይታ በኋላ፣ በታላቁ ቤተ መንግስት ቀዝቃዛ የምድር ቤት ፣ ቁጥር 1 እስር ቤት ለሶስት አመታት ፣ከሌሎቹ የንጉሱ ሹማምንት ጋር አስሯቸው፡፡
ሁሉንም በፀጋ እየተቀበሉ ፣ አብረዋቸው የታሰሩትን ያፅናኑና በፀሎት ይረዱ ነበር፡፡ በ1971 ዓ.ም ከሐምሌ አምስት ጀምሮ ፣ የንጉሱን ከፍተኛ ሹማማንት ለመግደል ከእስር ቤት ሲወስዳቸው፣ ቅዱስ ፓትሪያርኩ ሟቾቹን እያናዘዙ በፀሎት ሲሸኙ ሰነበቱ፡፡
ሐምሌ 7/1971 ደርግ ፣ ፓርትርያርኩንና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት የነበሩት ደጃ ካሳና ሌሎችንም ጨምሮ በምሽት ጠሯቸው፡፡
ቅዱስ ፓትርያርኩ ፣ ፀሎታቸውን አድርሰው ፣ ጥቁር ቀሚሳቸውንና ቆባቸውን ደፍተው ፣ የቀሩትን እስረኞች ባርከው ፣ ወደ አሳሪዎቻቸው ሄዱ፡፡
የደርግ ወታደሮች ፣ ቅዱስ ፓትርያርኩንና 15 የሚሆኑን ሹማምንት ፣ የራስ አሰራተ ካሳ መኖሪያ ወደነበረበት ገነተ ኢየሱስ አካባቢ ወስዷቸው፡፡
በግቢው ውስጥ በጨለማ እንዲያልፉ አስገደዱዋቸው በመሄድም ላይ እንዳሉ፣ በጨለማ የተደበቁ ገዳዮች ፣ አንገታቸውን በኤሌክትሪክ ሽቦ አንቀው ገደሏቸው፡፡
ከሌሎች ተገዳዮች ጋር ለምሽግ በተቆፈረው ጉድጓድ ጣሏቸው፡፡
የኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም መንግስት ተባሮ ፣ ኢሕአዴግ ሥልጣን ሲይዝ ፣ቅዱስ ፓትርያክ አባ ቴዎፍሎስ ከሌሎች ጋር የተቀበሩበት ቦታ በጥቆማ ተገኘ፡፡
ከአፅማቸው ጋር ጥቁር ቀሚሳቸውና የምንኩስና ቆባቸው ተገኘ፡፡ በተገደሉ 13 አመታት በኋላ አፅማቸው ፈልሶ፣ በሙሉ ክብር በአሰሩት በጎፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን እንዲያርፍ ተደርጓል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የሰማዕትነት ክብር ሰጥታቸው በጎፋ ገብርኤል ሐውልት ተቀርጾላቸው፣ ሙዚየምም፣ ተሰርቶላቸዋል፡፡
ሁለተኛው የኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ ፣ ብጹዕ ወቅዱስ አባ ቴዎፍሎስ ፣ በ69 አመታቸው ሰማዕትነት ከተቀበሉ ፣ 47 አመት ሆነ ፡፡
እሸቴ አሰፋ | 9 209 |
| 10 | ቅድስት ሥላሴ በአብርሃም ቤት
አባታችን አብርሃም እንግዳ ከመውደዱ የተነሣ በመስቀለኛ መንገድ ላይ ድንኳን ሠርቶ እንግዶች እየተቀበለ እግዚአብሔርን እያገለገለ ይኖር ነበር፡፡ ጥንተ ጠላታችን ዲያብሎስ ለተንኮል አያርፍምና ይህንን መልካም ግብሩን፣ ርኅራኄውን፣ ትሕትናውን አይቶ ሊፈትነው አሰበ፡፡ አስቦም አልቀረ የተጎዳ ሰው መስሎ፣ ራሱን ፈንክቶ፣ ከጎዳና ላይ ቆሞ አብርሃም ቤት ለሚመጡ እንግዶች “ወዴት ትሄዳላችሁ? እያለ ይጠይቃቸው ጀመር፡፡ እነርሱም ወደ አብርሃም ቤት እንደሚሄዱ በገለጹለት ጊዜ አብርሃም እንግዳ መቀበል እንደተወ፣ ልብሱን ገፎ እንደመለሰው ነገራቸው፡፡ እንግዶቹም እውነት መስሏቸው እያዘኑ ይመለሱ ነበር፡፡ በዚህ የተሣም እንግዳ ወደ አብርሃም ቤት መምጣት ቀረ፡፡ አብርሃምም ማዕደ እግዚአብሔር ያለ እንግዳ አይበላምና ሦስት ቀን ሳይመገብ ጾሙን አደረ፡፡
በሦስተኛው ቀንም ይህን ደግነቱ እግዚአብሔር ተመልክቶ በኦሪት ዘፍጥረት ፲፰፥፩-፲፱ ተጽፎ እንደምናገኘው አጋእዝተ ዓለም ሥላሴ በሦስት ሰዎች አምሳል በመምሬ አድባር ዛፍ ተገለጡለት፡፡ አብርሃምም ከድንኳን ደጃፍ ተነሥቶ ወደ እነርሱ ሰገደና “አቤቱ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደሆነ ባርያህን አትለፈው” አለ፡፡ እነርሱም “ስለ ደከመን አዝለህ ውሰደን” አሉት፡፡ አንዱን አዝሎ ከገባ በኋላ በአምላካዊ ግብር ሁለቱም ገብተው ተገኙ፡፡ አብርሃምም ወደ ድንኳን ወደ ሚስቱ ሣራ ፈጥኖ ገባና “ሦስት መስፈሪያ የተሰለቀ ዱቄት ፈጥነሽ ለውሺ፤ እንጎቻም አድርጊ” አላት፡፡ አብርሃምም ወደ ላሞቹ ሮጠ፤ የሰባም ታናሽ ጥጃ ያዘና ለብላቴናው ሰጠው፤ ያዘጋጅም ዘንድ ተቻኮለ፡፡ እርጎና ማር፣ ያን ያዘጋጀውንም ጥጃ አመጣ፤ በፊታቸውም አቀረበው፤ እርሱም በፊታቸው ቆሞ ያሳልፍላቸው ነበር፤ እነርሱም በሉ።
መብላታቸውም አጋእዝተ ዓለም ሥላሴ በሰው አምሳል ስለ ተገለጡና ለአብርሃምም የበሉ መስለው ስለታዩት ተመግበዋል ተባለ እንጂ ለሥላሴ መብል መጠጥ የሚስማማቸው ሆኖ አይደለም፡፡ ሥላሴ ምግብ በሉ ማለት ቅቤ ከእሳት ገብቶ አልቀለጠም እንደ ማለት ነው፡፡ ከዚያም የታረደው ጥጃ ተነሥቶ “ስብሐት ለአብ፣ ስብሐት ለወልድ፣ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ” ብሎ አምላክን አመስግኗል፡፡
ሊሄዱም ሲሉ ከሦስቱ አንዱ እግዚአብሔር ቃል “የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ወደ አንተ ተመልሼ እመጣለሁ፤ ሚስትህ ሣራም ልጅ ታገኛለች” አለ፡፡ ለጊዜው ስለ ልጁ ይስሐቅ ሲሆን ፍጻሜው ግን እግዚአብሔር ወልድ ሰው ሆኖ እንደሚያድነው ሲነግረው ነው፡፡ ይህ ታሪክ የተፈጸመው ከ፳፻-፲፰፻፶ (2000-1850) ዓ.ዓ. አካባቢ ነው፡፡ ከዚህ ብዙ ትምህርት እንማራለን፡፡ ለምሳሌ ያህልም የሚከተሉትን እንጠቅሳለን፡፡
ሀ. የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት
አንድነቱና ሦስትነቱ እንዴት ነው? ቢሉ በዘፍጥረት ፲፰፥፪-፭ ላይ ያለውን ኃይለ ቃል መመልከት አስፈላጊ ይሆናል፡፡ “ዓይኑንም ባነሣ ጊዜ እነሆ ሦስት ሰዎች በፊቱ ቆመው አየ፤ ባያቸውም ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳን ደጃፍ ተነሥቶ ሮጠ፤ ወደ ምድርም ሰገደ፤ እንዲህም አለ፤ “አቤቱ በፊትህስ ባለሟልነትን አግኝቼ እንደሆነ ባርያህን አትለፈው፤ ውኃ ላምጣላችሁ እግራችሁንም ታጠቡ” የሚለው ኃይለ ቃል ሦስትነቱ “ሦስት ሰዎች… ሊቀበላቸው፣ ወደ እነርሱ” የሚሉት ሐረጋት ሦስተነቱን ሲገልጽ “በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደሆነ ባርያህን አትለፈኝ” የሚለው ዓረፍተ ነገር ደግሞ አንድነቱን ይገልጻል፡፡ እንዲሁም ሦስት መስፈሪያ የሦስትነት፣ እንጎቻው (ዳቦ) አንድ መሆኑ የአንድነቱ ምሳሌ ነው፡፡
ለ. እግዚአብሔር ለአብርሃም ልጅ እንደሚወልድ ያበሠረበት ቀን ነው፡፡
አባታችን ጻድቁ አብርሃም እግዚአብሔር ብዙ ጊዜ አበ ብዙኀን (የብዙዎች አባት) እንደሚሆን ቢነግረውም ልጅ ግን አልነበረውም፡፡ በዚህ እንግዳ ተቀባይነቱና መልካም ሥራው እግዚአብሔር በእንግድነቱ ከቤቱ በገባ ጊዜ በእርጅናው ልጅ እንደሚወልድ (ልጅ እንደሚሰጠው) አበሠረው፡፡
እግዚአብሔር እንደ አብርሃም ቅን ልቡና ያላቸውና ለጋሾች ለሆኑ፣ ምጽዋት መስጠትና እንግዳ መቀበል የዘወትር ልማዳቸው አድርገው በሚኖሩ ሰዎች ቤት እንደሚገኝ እንዲሁም ሲገባም የተዘጋ ማኅፀን እንደሚከፍት፣ ቤትንም በበረከት እንደሚሞላ እንዲሁም የተሠወረ ምሥጢር እንደሚገልጽ እንረዳለን፡፡
ሐ. የአብርሃም ድንኳን
አባቶቻችን ሊቃውንት እንደተረጎሙልን የአብርሃም ድንኳን የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት፡፡ በአብርሃም ድንኳን አላፊ አግዳሚ ያርፍበት፣ ይመገብበት እንደነበር ሁሉ እመቤታችን የነፍስም የሥጋም መድኃኒት፣ የዘለዓለም ማረፊያ፣ እውነተኛ መብልና መጠጥ የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን የወለደች እርሷ ናትና በአብርሃም ድንኳን ትመሰላለች፡፡ ቀትር በሆነ ጊዜም በስድስት ሰዓት አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ በአብርሃም ድንኳን እንደገቡ፣ በስድስተኛው ወርም ቅዱስ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እመቤታችን ተልኳልና፡፡ (ሉቃ.፩፥፳፮)
በሐምሌ ሰባት (፯) ቀን እግዚአብሔር አምላክ በአብርሃም ቤት ተገኝቶ እንደባረከው ቅን ልቡና ያላቸውን፣ ለጋሾች ለሆኑ፣ ምጽዋትን ለሚያቀርቡ፣ እንግዳ መቀበል የዘወትር ልማዳቸው ላደረጉ ሰዎች በቤታቸው ይገባል፡፡ የተዘጋውንም ማኅፀን እንደከፈተ ቤቱንም እንደባረከ አይተናል፡፡ ዛሬም እኛም ለተራቡ በማብላት፣ ለተጠሙ በማጠጣት፣ ለታረዙ በማልበስ፣ በመመጽወትና በመሳሰለው ተግባር መኖር፣ በቀና አስተሳሰብ መጓዝ እንዳለብን መጽሐፍ ይነግረናል፡፡
የአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ ቸርነታቸውና ምሕረታቸው አይለየን፤ አሜን!!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር!!! | 10 399 |
| 11 | ክርስትና እና ቁሳዊ ብልጽግና
👉 አጭር ምልከታዎች
👉 የክርስትና ግቡ እና መለኪያው ምንድን ነው?
👉 የብልጽግና ወንጌል
👉 መጽሀፍ ቅዱስ ስለ ገንዘብ እና ስለ ቁሳዊ ብልጽግና ምን ይላል?
#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
#መድሎተ_ጽድቅ | 7 733 |
| 12 | ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የመጀመሪያውን ጉዞ ያደረገው ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ ከተመለሰ በኋላ በልዑል እግዚአብሔር ጥሪ በአሕዛብ ሀገር ወንጌልን ለመስበክ ከበርናባስ ነው።
በዚህ ጉዞአቸው በጠቅላላ ወደ ፪፼ (ሁለት ሺህ) ኪሎ ሜትር የሚደርስ መንገድ በእግር ተጉዟል። ይህም ጉዞ የተከናወነው በ፵፮ ዓ.ም. አካባቢ ነው።
ሁለተኛው ጉዞ የተከናወነው በ፶ ዓ.ም. ገደማ ነው። በመጀመሪያው ጉዞ ማርቆስ አብሮ ተጉዞ ነበር። ነገር ግን ጵንፍልያ ከተማ ሲደርስ እናቱ ስለናፈቀችው መመለስ በመፈለጉ በርናባስ ወደ ኢየሩሳሌም ይዞት መጣ።
ስለዚህም በሁለተኛው ጉዞ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሲላስን ይዞ ወደ ኪልቂያ ሶርያ ሲጓዝ በርናባስ ደግሞ ማርቆስን አስከትሎ ወደ ቆጵሮስ ሄደ።
በዚህ ጉዞው ቅዱስ ጳውሎስ እስከ ግሪክ ደርሶአል።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የመንፈስ ልጁ ጢሞቴዎስን ያገኘው በዚሁ ጉዞው በልስጥራ ከተማ ነው።
ሦስተኛው ጉዞ የተከናወነው በ፶፬ ዓ.ም. ነው።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ከልዩ ልዩ ሀገሮች ክርስቲያኖች የሰበሰበውን ዕርዳታ ለኢየሩሳሌም ቤተ ክርስቲያን በመያዝ ሦስተኛውን ጉዞ አጠናቅቆ ኢየሩሳሌም ገባ።
ነገር ግን ኢየሩሳሌም የገባበት ጊዜ የፋሲካ በዓል ስለነበር ከልዩ ልዩ ሀገሮች የተሰበሰቡ አይሁድ በከተማዋ ነበሩ።
እነዚህ በዝርወት የሚኖሩ አይሁድ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን በየሀገራቸው በትምህርቱ የተነሣ ሲቃወሙት የነበሩ ናቸው።
እኒህ አይሁድ ቅዱስ ጳውሎስን በኢየሩሳሌም ሲያዩት ታላቅ ተቃውሞ አነሡበት።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ተቃውሞ አነሡበት። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ተቃውሞአቸውን ለመግታት እንደ አይሁድ ሕግ በቤተ መቅደስ የመንጻት ሥርዓት መፈጸም ጀመረ።
ነገር ግን ከኤፌሶን የተከተለውን ጥሮፊሞስን ወደ መቅደስ ያስገባው ስለመሰላቸው ተቃውሞአቸው በረታ።
ከተማውንም አወኩት፤ ይህ ቅዱስ ጳውሎስን በ፶፰ ዓ.ም. ለሮም እሥር ዳረገው። ከብዙ መከራና ስቃይ በኋላ ታስሮ ሮም ገባ።
በዚያም በቁም እሥር ለሁለት ዓመታት ያህል ወንጌልን ሰበከ። የሁለቱን ዓመት የቁም እሥር እንደጨረሰ ወደ ኔሮን ፍርድ ቤት ቀረበ።
ይህም በ፷ዎቹ ዓ.ም ነው። በፍርድ ቤቱ በተደረገው ምርመራ የሮሜን ሕግ የሚቃወም ምንም ወንጀል ስላልተገኘበት በነፃ ተለቀቀ፤
ከዚህ በኋላ ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ አራተኛውንና የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ያልመዘገበውን ጉዞውን ያደረገው።
ይህ ጉዞው በመታሠሩ አዝነው ተክዘው የነበሩ ክርስቲያኖችን ለማጽናናት የጀመራቸውን ሥራዎች ፍጻሜ ለማየት የተደረገ ጉዞ ነው።
በመጨረሻ በ፷፬ ዓ.ም. ኔሮን በጥጋቡ የሮማ ከተማ ስትቃጠል ምን እንደምትመስል ማየት እፈልጋለሁ ብሎ አቃጠላት።
የሮም ሕዝብ በከተማው መቃጠል በማዘኑና በማመፁ ነገሩን ሁሉ በክርስቲያኖች ላይ አሳበበ።
በዚህም የተነሣ ክርስቲያን የተባለ ሁሉ መሰደድ፣ መሠየፍ፣ መታረድ እጣ ፈንታው ሆነ።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም በኒቆጵልዮን ከተማ ሲያስተምር በ፷፭ ዓ.ም. ተይዞ ወደ ወኅኒ ገባ።
ለሁለት ዓመት ከስድስት ወር በጨለማ ቤት ታሥሮ ከቆየ በኋላ በ፸፬ ዓመት ዕድሜው በሮም ከተማ በኦስትያ መንገድ አንገቱን ተሰይፎ በ፷፯ ዓ.ም. ሐምሌ ፭ ቀን በሰማዕትነት ዐረፈ።
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ሁለት፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ ዐስራ አራት መልእክታትን ጽፈዋል።
የቅዱሳኑ ሐዋርያት ረድኤትና በረከታቸው ከሁላችን ጋር ይሁን፤ አሜን።
ምንጭ፦
✔መጽሐፈ ስንክሳር ዘወርኃ ሐምሌ ፭፤
✔መጽሐፍ ቅዱስ-ሐዲስ ኪዳን፣
✔ቤተ ክርስቲያንህን ዕወቅ ቁጥር ፩፤ በማኅበረ ቅዱሳን | 10 714 |
| 13 | የሮም ሕዝብ በደረሰው አደጋ እጅጉን ተቆጣ። ኔሮንም በክርስቲያኖች አመካኘ። በዚህም የተነሣ በሮማ ከተማ ሁለት ዓይነት ወሬ መናፈስ ጀመረ።
የሮማ አማልክት በክርስቲያኖች ሃይማኖት ስለተቆጡ በከተማዋ እሳት አዘነቡባት የሚለው የመጀመሪያው ሲሆን ክርስቲያኖች ሆን ብለው ከተማዋን አቃጥለዋታል የሚለው ደግሞ ሁለተኛው ወሬ ነበር።
የከተማው መጋየት ያበሳጨው የሮማ ሕዝብ፣ ክርስቲያን የሆነውን ሁሉ እያወጣ መግደሉን ተያያዘው።
ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ሰዓት በእሥር ነበርና ተሠይፎ ዐረፈ። ይህን የሰሙት የአግቢኖስና የአግሪጳ ሚስቶች (የሮም ባለሟሎች ነበሩ) «ባይሆን አንተ ትረፍልን» ብለው በከተማዋ ግንብ በገመድ አሥረው በቅርጫት በማውረድ ቅፅረ ሮማን ለቅቆ እንዲወጣ አደረጉት።
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በኦፒየም ጎዳና ጉዞውን ቀጠለ። ሮማን ለቀቀ። እያዘገመ በሸመገለ ጉልበቱ ሲጓዝ አንድ ቀይ ጐልማሳ ወደ እርሱ ሲመጣ አየ።
እየቀረበ ሲመጣ ጌታችን መሆኑን ተረዳ። ወዲያው በፊቱ ተደፋና «ጌታዬ ወዴት እየተጓዝክ ነው?» አለና ጠየቀው። «ዳግም በሮም ልሰቀል» አለው።
በዚህ ሰዓት ቅዱስ ጴጥሮስ አዘነና እንደገና ወደ ሮማ ተመለሰ። የኔሮን ወታደሮች እየፈለጉት ነበር። «እነሆኝ ስቀሉኝ» አለ ቅዱስ ጴጥሮስ።
ያን ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስን ይዘው አሠሩት። ከጥቂት ቀናት በኋላም ሮማውያን የመስቀያውን እንጨት አቀረቡለት።
ያን ጊዜ «እኔ እንደ ጌታዬ ልሰቀል አይገባኝም» በማለት ቁልቁል እንዲሰቅሉት ለመነ። ያለውንም አደረጉለት። ሐምሌ ፭ ቀን ፷፯ ዓ.ም. በሰማዕትነት ዐረፈ።
ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወ ቅዱስ ጳውሎስ
ክፍል ፪
፪. ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ዘሩ ከዕብራዊያን፣ ከብንያም ነገድ ሲሆን የተወለደውም በጠርሴስ ከተማ ነው።
ጠርሴስ በንግድዋ የታወቀች የኪልቂያ ዋና ከተማ ናት። በከተማዋ እስከ አምስት መቶ ሺህ የሚገመቱ ከየሀገሩ የተሰባሰቡ ሕዝቦች ነበሩባት።
ሮማውያን በሥራቸው ለሚተዳደሩት ሕዝቦች ሮማዊ ዜግነትን ይሰጡ ስለነበር፥ የቅዱስ ጳውሎስ አባት በዜግነት ሮማዊ ነበር። ይህም ለቅዱስ ጳውሎስ ተላልፎለታል።
ቅዱስ ጳውሎስ በ፲፭ ዓመት ዕድሜው ወደ ትውልድ ሀገሩ በመመለስ በኢየሩሳሌም ከነበረው የታወቀው የገማልያል ትምህርት ቤት ገባ።
በዚያም የአይሁድን ሕግና ሥርዓት እየተማረ እስከ ፴ ዓመቱ ቆየ። ገማልያል ፈሪሳዊ ስለነበር ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ይህን ተቀብሎታል። በ፴ ዓመቱ የአይሁድ ሸንጎ አካል ሆኖ ተቆጠረ።
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ዘመን ቅዱስ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም ስለነበረ ሁኔታዎቹን ሁሉ ያውቃል።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በአይሁድ ሸንጎ አባልነት ለሁለት ዓመታት በሠራበት ወቅት ለኦሪታዊ እምነቱ ቀናተኛ ፈሪሳዊ በመሆኑ ክርስቲያኖችን በማናቸውም አጋጣሚ ይቃወም ነበር።
እንዲያውም ሊቀዲያቆናት እስጢፋኖስን በማስተማሩ ምክንያት ተከሶ ለአይሁድ ሸንጎ በቀረበ ጊዜ የተከራከረው እርሱ ነበር።
በድንጋይ ተወግሮ በሰማዕትነት ሲያርፍም የወጋሪዎችን ልብስ ይጠብቅ የነበረው እርሱ ነው።
በ፴፪ ዓመት እድሜው ከኢየሩሳሌም ፪፻፳፫ (ሁለት መቶ ሃያ ሦስት) ኪ.ሜ. ርቀት በስተሰሜን በኩል በምትገኘው የደማስቆ ከተማ ብዙ ክርስቲያኖች መኖራቸውን ሲሰማ ወደ ሊቀ ካህናቱ ቀርቦ ክርስቲያኖችን ለማጥፋት የሚያስችለውን የፈቃድ ደብዳቤ አገኘ።
ከዚህም በኋላ ጭፍሮችን አስከትሎ ወደ ደማስቆ አመራ።
ሐዋርያው ጳውሎስ ወደ ከተማዋ ለመድረስ ጥቂት ሲቀረው ነበር ከሰማይ የወረደው ብርሃን አካባቢውን ያለበሰውና «ሳውል ሳውል ለምን ታሳድደኛለህ?» የሚለውን ድምፅ የሰማው።
ሐዋርያው ጳውሎስም «ጌታ ሆይ ማን ነህ?» ብሎ ጠየቀ። «አንተ የምታሳድደኝ እኔ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ። የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል» ሲል መድኃኒታችን ተናገረው።
ያን ጊዜም በወደቀበት ሆኖ እየተንቀጠቀጠ «ጌታ ሆይ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ?» ሲል ጠየቀ።
ከዚህ በኋላ ተነሥቶ ወደ ደማስቆ እንዲገባ ተነገረው። (የሐዋ. ፱፥፩)
የሐዋርያው ዓይኖች ለማየት አልቻሉም። እየተመራ ወደ ደማስቆ ገባ።
ለሦስት ቀናት ያህልም እህል ሳይቀምስ ቆየ።
በዚያች ዕለት እግዚአብሔር አምላክ በደማስቆ ለሚገኘው እና ሐናንያ ለተባለው አባት በራእይ ተገለጠለት።
ቅዱስ ጳውሎስም ያለበትን አድራሻ ነገረውና ሄዶ እንዲያጠምቀው አዘዘው። ሐናንያ አስቀድሞ የቅዱስ ጳውሎስን ማንነት ያውቃል።
አብዛኞቹ በደማስቆ የሚገኙት የቅዱስ ጳውሎስን ማንነት ያውቃል።
አብዛኞቹ በደማስቆ የሚገኙት ክርስቲያኖች ከኢየሩሳሌም በስደት የመጡ ናቸው።
ያን ስደት ያስነሣው ደግሞ በቅዱስ እስጢፋኖስ ላይ የደረሰው መከራ ነው።
በዚህ የቅዱስ እስጢፋኖስ ሰማዕትነት ደግሞ ዋናው ተዋናይ ሐዋርያው ጳውሎስ ነበር።
ይህን የሚያውቀው ሐናንያ በቅድሚያ ከእግዚአብሔር ጋር መከራከር ጀምሮ ነበር። እግዚአብሔር አያውቀው ይመስል ስለ ቅዱስ ጳውሎስ ማስረዳት ጀመረ።
በመጨረሻ ግን «ይህ በአሕዛብም በነገሥታትም በእሥራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፤ ስለ ስሜ ስንት መከራ ሊቀበል እንዲያስፈልገው እኔ አመለክተዋለሁና» በማለት እግዚአብሔር ሐናንያን ላከው።
ሐናንያ ቅዱስ ጳውሎስን ካጠመቀውና ካስተማረው በኋላ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ዓረብ ሀገር መሄዱን ራሱ ተናግሮአል። (ገላ ፩፥፲፯)
ለ፫ ዓመታት በዓረቢያ በረሃ ከቆየ በኋላ ወደ ደማስቆ ከተማ ተመለሰ።
በዚያም በነበሩ አይሁድ መካከል በፊት ያሳድደው የነበረውን ኢየሱስ ክርስቶስን መስበክ ጀመረ።
ከዚያ በፊት በፈሪሳዊነቱና ለአይሁድ ሕግ በነበረው ቅንዓት የሚታወቀው ጳውሎስ ዛሬ ወንጌል ሲሰበክ በማየታቸው አይሁድ ተነሡበት።
በዚህም የተነሣ የደማስቆ ክርስቲያኖች በቅርጫት አውርደው ወደ ኢየሩሳሌም ላኩት።
ቅዱስ ጳውሎስ ኢየሩሳሌም ሲደርስ የገጠመው ሁለት ችግር ነበር። በቅድሚያ አይሁድ ጳውሎስን እንደሚያውቁት እና እንደለመዱት ሆኖ ስላላገኙት ሊገድሉት ተነሡ።
በሌላ በኲል ደግሞ ክርስቲያኖች የቅዱስ ጳውሎስን መመለስ ሊያምኑ አልቻሉም።
በመጨረሻ ግን በርናባስ ወደ ሐዋርያት ዘንድ ወስዶ የጳውሎስን መመለስ በመተረክ እንዲያምኑት አደረጋቸው።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም በድፍረት በማስተማሩ አይሁድ ስለተቃወሙት ከተማዋን ትቶ በቂሳርያ በኲል ወደ ትውልድ ሀገሩ ጠርሴስ ተመለሰ።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በጠርሴስ ከተማ ለዘጠኝ ዓመታት ቆይቷል።
ከኢየሩሳሌም ውጭ የአሕዛብ ከተማ በነበረችው በአንጾኪያ የክርስትና ሃይማኖት ተስፋፋ።
ከኢየሩሳሌም የተሰደዱት ክርስቲያኖች የአንጾኪያን ሕዝብ ተግተው በማስተማራቸው ዝናው እስከ ኢየሩሳሌም ደረሰ።
በዚህም ምክንያት በኢየሩሳሌም የነበሩት አበው በርናባስን ወደ አንጾኪያ ላኩት።
በርናባስ የግሪክ ቋንቋ ችሎታ ያለውን፣ ከማንኛውም ሰው ጋር መግባብ የሚችለውን፣ ደግሞም እግዚአብሔር ለአሕዛብ ሐዋርያ እንዲሆን የመረጠውን ቅዱስ ጳውሎስን ከጠርሴስ በማምጣት በአንጾኪያ ሥራቸውን ጀመሩ።
በገላትያ መልእክቱ ምዕራፍ ፪ ላይ ራሱ እንደገለጠው ከአሥራ አራት ዓመት በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ከአንጾኪያ ክርስቲያኖች የሰበሰበውን ርዳታ ይዞ ወጣ።
በዚህም በአይሁድና በአሕዛብ መካከል የነበረውን መለያየት ክርስትና አንድ እንዳደረገው አስመሰክሯል። | 9 331 |
| 14 | ፩. ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ የተወለደው በገሊላ ባሕር ዳር በምትገኘው በቤተሳይዳ ነው።
የአባቱ ስም ዮና ይባላል። ከአምስት ዓመቱ ጀምሮ ያደገው በቅፍርናሆም ከተማ ሲሆን በጐልማሳነቱ ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር በገሊላ ባሕር ዓሳ ማሥገር ጀመረ።
ለደቀመዛሙርነት ሲመረጥ ዕድሜው ፶፭ ዓመት እንደነበረ ይነገራ፤ ወደ ጌታችን ያመጣውም ወንድሙ እንድርያስ ነው።
ቅዱስ ጴጥሮስ በርናባስና ወንጌላዊው ማርቆስ ቤተ ዘመድ ናቸው። የማርቆስ አባት አርስጦቡሎስና በርናባስ በእናት የሚገናኙ ወንድማማች ናቸው።
ቅዱስ ጴጥሮስ ያገባው የበርናባስና የአርስጦቡሎስን እኅት ስለነበር በጋብቻ ይዛመዳሉ።
ቅዱስ ጴጥሮስ ለሐዋርያነት ሲጠራ መተዳደሪያው የነበረውን መረቡንና ታንኳውን እንዲሁም አባቱን እርግፍ አድርጐ ትቶ ጌታውን የተከተለ ሐዋርያ ነው።
የቅዱስ ጴጥሮስ በመጀመሪያ ስሙን ስምዖን ብላ እናቱ የጠራችው በነገዷ ስም እንደሆነ ይነገራል።
በቂሳርያ ከተማ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «ማን ትሉኛላችሁ?» ብሎ በጠየቀ ጊዜ «አንተ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ» ብሎ ለአይሁድ ሊቃውንት የተሰወረውን ምሥጢረ ተዋሕዶ ገልጦ በመመስከሩ ጌታችን «አንተ ጴጥሮስ ነህ» ብሎታል ይህም በላቲን ቋንቋ ዐለት ማለት ነው፤ በአርማይክ ደግሞ ኬፋ ይባላል።
ቅዱስ ጴጥሮስ ከአዕማድ ወይንም የምሥጢር ሐዋርያት ከእነ ዮሐንስ እና ያዕቆብ ጋር የሚቆጠር ነው።
ከሐዋርያት ሁሉ ቀደም ቀደም የማለት ባሕርይ ነበረው። ጌታ በጥብርያዶስ ባሕር ላይ ሌሊት በእግሩ ሲመጣ ቢመለከት ወደ አንተ እመጣ ዘንድ እዘዘኝ በማለት ካስፈቀደ በኋላ ወደ ጌታ ለመምጣት መንገድ ጀምሮ በመሐል ቤት ጥርጣሬ ገባውና መስጠም ስለጀመረ ጌታችን «ያመንክ እንጂ ያላመንክ አትሁን» ብሎ ገስፆ ከመስጠም አድኖታል። (ማቴ ፲፬፥፳፪-፴፫)
በቅፍርናሆም ጉባኤ ጌታን ምሥጢረ ቁርባንን ሲያስተምር፣ አይሁድ ስላልገባቸው ወደ ኋላ አፈገፈጉ። ከደቀ መዛሙርቱም «ብዙዎቹ ወደ ኋላ ተመለሱ» በዚህን ጊዜ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «እናንተ ደግሞ ልትሄዱ ትወዳላችሁ?» ብሎ ሐዋርያትን ጠየቃቸው።
በዚህ ሰዓት «ጌታ ሆይ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘላለም የሕይወት ቃል አለህ። እኛስ አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ እንደሆንክ እናምናለን» በማለት ሐዋርያትን ወክሎ የመለሰ እርሱ ነው። (ዮሐ ፮፥፷፮-፷፰)
ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታን ይወድ ነበር። ፍቅሩ ግን ቅንዓት የተቀላቀለበት በመሆኑ ጌታችን ለደቀ መዛሙርቱ የሞቱን ነገር ቀድሞ ሲነግራቸው አይሁንብህ በማለት ተከራክሯል። (ማቴ ፲፮፥፳፫)
በኋላም «ሁሉም በአንተ ቢሰናከሉ እኔ ከቶ አልሰናከልም» ብሎ በራሱ ቅንዓት ተማምኖ ተናግሮ ነበር። ጌታችን «ዶሮ ሳይጮህ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ» እያለው እንኳን «ከአንተ ጋር መሞት እንኳን የሚያስፈልገኝ ቢሆን ከቶ አልክድህም» በማለት የተናገረ ሰው ነው። (ማቴ ፳፮፥፴፬)
ቅዱስ ጴጥሮስ አስቀድሞ የተናገረውን ቃል ለመጠበቅ ሞክሮ ነበር። ጌታ ዛሬ «የሰው ልጅ አሳልፎ ይሰጣል» ብሎ አስተምሮአቸው ነበርና መከላከያ ይሆነኛል ብሎ ሠይፍ ደብቆ ይዞ ነበር።
የሮም ጭፎሮችም ጌታን ለመያዝ ሲጠጉ የሊቀ ካህናቱን ባርያ (ማልኰስን) በሠይፍ ጆሮውን ቆረጠው። ጌታችን ግን ሞቱ በፍቃዱ ለድኅነተ ዓለም ነውና «ሠይፍህን ወደ ሰገባው» መልስ ሲል ገሠፀው።
ቅዱስ ጴጥሮስ የሚታወቅበት ሌላው ትልቁ ነገር ንስሐው ነው። ጌታው የነገረው መድረሱን፣ ቃል የገባለትን አምላኩን መበደሉን እንዳወቀ ከግቢው ወጥቶ አለቀሰ።
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በዕድሜው ታላቅነት በሐዋርያት ዘንድ እንደ አባት ይታይ ስለነበር ጌታ በተለያቸው ጊዜ ሐዋርያቱን ሊመግብ ወደሚያውቀው ሙያ ዓሳ ወደ ማሥገሩ ተሠማራ።
ጌታም አስቀድሞ የመረጠው እርሱ ነውና ቢክደው እንኳን በንስሐ በመመለሱ ንስሐውን መቀበሉን፤ ዛሬም እንደሚወደው ይገልጽለትም ዘንድ በጥብርያዶስ ባሕር ተገለጠለት። (ዮሐ ፲፰፥፲)
ሦስት ጊዜ ክዶት ነበርና ቀኖና ሰጠው። አሁን ቅዱስ ጴጥሮስ በራስ መተማመኑ እንዳላዋጣው ዐውቆአልና «ትወደኛለህን?» ተብሎ ሲጠየቅ «አንተ ታውቃለህ» ነበረ መልሱ።
የራሱ ዕውቀት የት እንዳደረሰው ያውቃልና ጌታችንም ኅዳጌ በቀል (በቀልን የሚተው) ነውና ዛሬም እንደሚወደው፣ በንስሐ ተመልሶአልና ዛሬም ለእርሱ የሰጠውን ክብር እንደማያጐድልበት ሲነግረው ግልገሎቼን አሠማራ፣ ጠቦቶቼን ጠብቅ፣ በጐቼን አሠማራ» በማለት አደራውን አስረከበው። ከዚያም በሞቱ እንደምን አድርጐ እግዚአብሔርን አንደሚያከብረው ነግሮት ወደ ሰማያት ዐረገ። (ዮሐ ፳፩፥፲፭-፲፯)
ቅዱስ ጴጥሮስ በአራቱም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ላይ በተቀመጡት የሐዋርያት ዝርዝር ቀዳሚውን ሥፍራ ይዞ ይገኛል።
ይህም፦
፩. በሽምግልና አባትነቱ፣
፪. ጌታ በቂሳርያ በሰጠው ቃል ኪዳን፣
፫. የሐዋርያት አፈ ጉባዔ ሆኖ ይናገር ስለነበር፣
፬. በጥብርያዶስ ባሕር በተሰጠው ቃል መሠረት ነው።
በዚህም የተነሣ በይሁዳ ምትክ ሌላ ሐዋርያ እንዲመረጥ ሐሳብ ያቀረበ እርሱ ነበር።
በበዓለ ሃምሳም ለደቀመዛሙርቱ መንፈስ ቅዱስ በወረደላቸው ጊዜ ለተሰበሰቡት አይሁድ አፈ ጉባዔ ሆኖ ወንጌልን የሰበከ ፫፼ (ሦስት ሺህ) ምእመናንንም አሳምኖ የመጀመሪያዋን አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በኢየሩሳሌም የመሠረተ እርሱ ነው። (የሐዋ. ፩፥፲፮-፳፫፣ ፪፥፲፬-፴)
አስቀድሞ ፈሪ የነበረውና በሊቀ ካህናት ቀያፋ ግቢ ጌታውን የካደው ቅዱስ ጴጥሮስ፣ የመንፈስ ቅዱስን ኃይል ካገኘ በኋላ ግን በአይሁድ ሸንጐ ድውይ ፈወስክ ተብሎ በተከሰሰ ጊዜ በድፍረት ስለ መድኃኔዓለም ክርስቶስ መሰከረ።
ቆርነሌዎስን በማጥመቅ ወንጌልን ለአሕዛብ አስቀድሞ የሰበከው ሐዋርያ ነው። ይህ ሐዋርያ ልዑል እግዚአብሔር ባደለው ጸጋ ጥላው እንኳን ድውያንን ይፈውስ ነበር። የሐዋ ፭፥፲፭።
በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ፲፭ ላይ በ፶ ዓ.ም. አካባቢ በኢየሩሳሌም በተደረገው የሐዋርያት ሲኖዶስ ከአንጾኪያ ክርስቲያኖች ለቀረበው ጥያቄ የመጀመሪያውን መልስ የሰጠው እርሱ ነበር።
ስለ ቅዱስ ጴጥሮስ መልክና ቁመና ጥንታዊያን መዛግብት እንደሚከተለው ያቀርቡታል። «ፊቱ ሰፋ ያለ ሲሆን ሪዛምና መካከለኛ ቁመት የነበረው ራሰ በራ ሰው ነው። በማናቸውም ነገር ፈጣንና ቀልጣፋ ነበር።»
በቤተ ክርስቲያን ታሪክ መሠረት ቅዱስ ጴጥሮስ በፍልስጥኤም፣ በሶርያ፣ በጳንጦን፣ በገላትያ፣ በቀጰዶቅያ፣ በቢታንያ እና በሮሜ ሰብኳል።
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በሮሜ አንድ ዓመት ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር ካስተማረ በኋላ የሮሜ ክርስቲያኖች እየበዙ ከመምጣታቸውም በላይ የክርስትናው ጉዞ እስከ ሮማ ባለሥልጣናት ደረሰ።
የኔሮን የቅርብ ባለሥልጣናት የሆኑት የአልቢኖስና የአግሪጳ ሚስቶች ወደ ክርስትናው ገቡ። በዚህን ጊዜ ኔሮን ንጉሠ ሮማ በቅንዓት ተነሣባቸው።
ኔሮን በሮም የነገሠው በ፶፬ ዓ.ም. ነው። በመንግሥቱ መጀመሪያ ደግ ሰው ነበረ። ነገር ግን በነገሠ በዓመቱ የጨካኝነት ዐመሉ ብቅ ማለት ጀመረ እና የአባቱን ልጅ አስገደለ።
በ፶፱ ዓ.ም. ደግሞ እናቱን በመርዝ ገደለ። በ፷፫ ዓ.ም. እያስተማረ ያሰደገውን መምህሩን ፣ በ፷፪ ዓ.ም. የልጅነት ሚስቱን አግታሺያን አስገደለ።
ከእርስዋ በኋላ ያገባትን ሚስቱንም ፓፒያን በርግጫ ብሎ ገደላት።
ኔሮን በ፷፬ ዓ.ም. እርሱ ከከተማው ወጣ ብሎ በሚገኘው ቤተ መንግሥቱ ተቀምጦ የሮማን ከተማ እሳት ለቀቀባት። | 7 026 |
| 15 | ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወቅዱስ ጳውሎስ
የቅዱሳን ሐዋርያት ታሪክ ገድልና ሥራ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ በሙሉ አልሰፈረም።
አርባዕቱ ወንጌላት ሐዋርያት እንዴት እንደተጠሩና እስከ ዕርገት ድረስ የነበራቸውን ሁኔታ ሲጽፉ፤ ወንጌላዊው ሉቃስ ደግሞ የሐዋርያትን ታሪክ እስከ ፷ዎቹ መጀመሪያ ያለውን ጽፏል።
ከዚህ በመለስ ያለውን የሐዋርያት ታሪክ ለማወቅ ግን ዋናው ምንጩ የቤተ ክርስቲያን የታሪክ መጻሕፍት ናቸው።
የሐዋርያት ደቀመዛሙርት እነ ፓፒያስ፣ ፖሊካርፐስ፣ አግናጥዮስ፣ ቀሌምንጦስ ዘሮም ወዘተ. የአባቶቻቸውን ታሪክ ጽፈው አቆይተውልናል።
ከዚህ በኋላ ጊዜም በ፪ኛውና በ፫ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተነሱት የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፍት እነ አውሳብዮስ፣ ሩፊኖስ፣ ጄሮም፣ ወዘተ. በትውፊት የተቀበሉትን መዝግበው አልፈዋል።
ቅዱሳን ሐዋርያት ገድላቸው የተጻፈላቸው፣ በዓላቸው የተከበረላቸው የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ናቸው።
በቤተ ክርስቲያናችን በሐምሌ ፭ ቀን በታላቅ ድምቀት በዓላቸው ከሚከበረው ሐዋርያት መካከል የሐዋርያው የቅዱስ ጴጥሮስና የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስ ታሪክ እንደሚከተለው ነው። | 7 566 |
| 16 | መጽሀፍ ቅዱስ እንዴት ይተርጎም (እንዴት እንረዳው)?
👉 መጽሀፍ ቅዱስ ግለሰባዊ ትርጉምን በተመለከተ (private or personal interpretation) ምን ይላል?
👉 ቤተ ክርስቲያናዊ የመጽሀፍ ቅዱስ አረዳድ
👉 በጥንቷ ቤተ ክርስቲያን ተነስቶ የነበረውና የአረዳድ (አተረጓጎም) ጉዳይ (hemeneutical question)
#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
#መድሎተ_ጽድቅ | 9 192 |
| 17 | بدون متن... | 9 314 |
| 18 | ወዳጄ ሆይ! ገንዘብ የለህምን? ፈሪሐ እግዚአብሔርን ገንዘብ አድርግ፡፡ ፈሪሐ እግዚአብሔርን ገንዘብ የምታደርግ ከኾነ ገንዘብ ካላቸው በላይ ባለጠጋ ነህ፡፡ “እንዴት?” ትለኝ ይኾናል፡፡ እኔም እንዲህ ብዬ እመልስልሃለሁ፡- የእነዚያ (የባለጠጐቹ) ገንዘብ ያልቃል፡፡ ያንተ ግን ብል አይበላውም፡፡ ጊዜ አይለውጠዉም፡፡ አያልቅም፡፡ ወደ ሰማያት፣ ወደ ሰማየ ሰማያት፣ ወደ ምድር፣ ወደ አየራት፣ ወደ እንስሳቱ ዓይነት፣ ብዙ የብዙ ብዙ ወደሚኾኑት ዕፅዋት፣ ወደ ደቂቀ አዳም በጠቅላላው፣ ወደ መላዕክት፣ ወደ መላዕክት አለቆች፣ ወደ ኀይላት ተመልከት፡፡ እነዚህ ኹሉ የአምላክህ ፍጥረቶች ናቸው፡፡ የእነዚህን አምላክና መጋቢ ባሪያ መኾን ድኻ መኾን አይደለምና ድኻ አይደለህም ብዬ እነግርሃለሁ፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ-ሰማዕትነት አያምለጣችሁ ገጽ 13-19 ) | 11 437 |
| 19 | https://youtu.be/rIF95U0-kKE?si=Jx7HOsESDMEQ8sa2 | 8 721 |
| 20 | https://youtu.be/SAMLOqGCNqk?si=XO2xedk54Ti_0ONN | 8 370 |
